TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"... የ2ኛው ዓመት የውሃ ሙሌት #ነሃሴ መጨረሻ ላይ ይጠናቀቃል" -ኢንጅነር ጌዲዮን አስፋው

የህዳሴ ግድብ ተደራዳሪና የባለሙያዎች ቡድን ሰብሳቢ ኢ/ር ጌዲዮን አስፋው ለኢዜአ በሰጡት ቃል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 2ኛው ዙር የውሃ ሙሌት እየተከናወነ ያለው ሶስቱ አገሮች በፈረሙት የመርህ ስምምነት መሰረት መሆኑን አሳውቀዋል።

ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን እ.ኤ.አ. በ2015 በመሪዎቻቸው አማካኝነት በሱዳን ካርቱም የህዳሴ ግድቡን ድርድር አስመልክቶ የመርሆች ስምምነት ተፈራርመዋል።

የመርህ ስምምነቱ አስር አንቀጾችን ያካተተ ሲሆን የሶስቱንም አገሮች ፍትሃዊና ምክንያታዊ የውሃ አጠቃቀም ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑ ይታወቃል።

በዚህም ኢትዮጵያ ፣ ግብጽ እና ሱዳን በተስማሙት የመርህ ስምምነት መሰረት ሁለተኛው ዙር የግድቡ የውሃ ሙሌት እየተከናወነ ኢንጅነር ጌዲዮን አስፋው ገልፀዋል።

በታላቁ ህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት ላይ የሶስቱ አገሮች ባለሙያዎች የተስማሙባቸው ነጥቦች የተቀመጡ መሆኑን አስታውሰው አገሮቹ በዚሁ መሰረት መስማማታቸውን አስረድተዋል።

ግብጽና ሱዳን በመርሆች ስምምነት ውስጥ ሁለት ጥናቶች እንዲካሄዱ የሚያስቀምጥ ቢሆንም ግብጽ እና ሱዳን ጥናቱ እንዳይካሄድ ሲያስተጓጉሉ ነበር ብለዋል።

አገሮቹ ስምምነቱን ከተፈራረሙ በ15 ወር ውስጥ ሁለት (2) ጥናቶችን ማከናወን እንዳለባቸው ቢያስቀምጥም ጥናቶቹ እንዳይካሄዱ ግብጽና ሱዳን በያዙት ግትር አቋም ሳይሳካ ቀርቷል ነው ያሉት።

አለም አቀፉ ማህበረሰብ ግብጽ እንዲሁም ሱዳን የግድቡን ውሃ ሙሌት በተመለከተ የሚሰጡትን የተዛባ መረጃ ሊመረምር እንደሚገባም ገልጸዋል።

ያንብቡ : telegra.ph/ENA-07-07

#ኢዜአ

@tikvahethiopia
"...ሰዎቹን በህይወት የማግኘት እድሉ ጠባብ ነው" - ፖሊስ

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምስራቅ ደንቢያ ወረዳ 13 የሚደርሱ ሰዎችን አሳፍራ በጣና ሃይቅ ጉዞ የጀመረች አነስተኛ ጀልባ ተሰወረች።

የወረዳው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ምክትል ኮማንደር ቸርነት አስማረ ጀልባዋ የተሰወረችው በወረዳው አዲሰጌ ድንጌ ተብሎ ከሚጠራ ቀበሌ አባን ላይ ጎጥ መነሻቸውን በማድረግ ወደ ጎርጎራ ወደብ ጉዞ ከጀመረች በኋላ ነው ብለዋል።

ተጓዥቹ ሐምሌ 9 ቀን 2013 ዓም ለሊት ድንች ጭነው ጉዞ መጀመራቸውን ከቤተሰቦቻቸው መረጃው ለፖሊስ መድረሱን ገልፀዋል።

ተሳፋሪዎቹ ከ10 እስከ 13 እንደሚደርሱና አብዛኞቹም በስም ዝርዝር መለየታቸውን የገለፁት ምክትል ኮማንደሩ ተሳፋሪዎቹ ከመዳረሻው ጎርጎራ ወደብ እንዳልደረሱ መረጋገጡን ተናግረዋል።

ከትናንት እኩለ ቀን ጀምሮ በሁለት ቡድን የተዋቀረ የፖሊስና የባለሙያዎች ቡድን ፍለጋ እያካሄደ መሆኑን አመልክተው እስካሁን ምንም አይነት ፍንጭ ማግኘት እንዳልተቻለ አስታውቀዋል።

በዛሬው እለት ፍለጋው መቀጠሉን ጠቁመው ተጓዦቹ ክረምት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ወይ በማዕበል ተወስደዋል፤ አለበለዚያም ከአቅም በላይ በሆነ ጭነት ጀልባዋ ሰምጣለች የሚል ድምዳሜ ላይ መደረሱን አብራርተዋል።

ተጓዦቹ የተነሱበት ሰዓት ለሊት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ፍለጋውን አስቸጋሪ እንዳደረገው ጠቅሰው ከዚህ በኋላ ሰዎችን በህይወት የማግኘት እድሉ ጠባብ እንደሆነም አመልክተዋል።

ከመነሻው እስከ መዳረሻው ድረስ ያለው የውሀ ላይ ጉዞ የ15 ኪሎ ሜትር ርቀት እንዳለው አመልክትው በፍለጋው የሚገኘውን ዝርዝር ውጤት በቀጣይ ህዝቡ እንዲያውቀው እንደሚደረግ አስታውቀዋል። #ኢዜአ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል። ዶ/ር ለገሰ ፥ መንግስት ለያዘው ሀገራዊ ምክክርና ብሄራዊ መግባባት ለመፍጠር ሁሉን አካታች የሆነ ውይይት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል ብለዋል። ይህን ሀገራዊ አንድነት ለማምጣትም ብዙ ተከታይ ያላቸውን እስረኞች ክስ ማቋረጥ ማስፈለጉን ነው የተናገሩት። በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት ፣ የተመቻቸ…
#DrLegesseTulu

የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ምን አሉ ?

ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ፦

" ... በኢትዮጵያ የሚስተዋሉ ችግሮችን ከስር መሰረቱ ለመፍታት የእስረኞችን ክስ ማቋረጥ አስፈልጓል።

የክሱ መቋረጥ ማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት እና ዋስትና ያለው የዴሞክራሲ ስርዓት በመገንባት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስቀጠል ከማሰብ የመነጨ መሰረታዊ ጉዳይ ነው።

በእነ አቶ ጃዋር መሃመድና አቶ እስክንድር ነጋ ስር የነበሩ ተከሳሾች ክስ መቋረጥ በስራቸው በርካታ ተከታይ ያላቸው መሆናቸውን ከግንዛቤ በማስገባት ለብሔራዊ አካታች ምክክሩ ጉልህ ሚና እንዳላቸው በመገንዘብ ነው።

በሽብር ቡዱኑ መሪ ደብረፂዮን ገብረ ሚካኤል ስር ያሉ የክስ ሂደት መቋረጥ ከጤና እና እድሜ መግፋት ጋር የተያያዘ ነው።

ኢትዮጵያዊያን ክሳቸው የተቋረጡ ዜጎችን በሚመለከት ህዝብና መንግስትን በማጋጨት እራሳቸውን ደብቀው የሚያራግቡ አካላትን በቃቹህ በማለት ለዘላቂ ብሔራዊ ጥቅም ዘብ መሆን ይገባል "

#ኢዜአ

@tikvahethiopia
#Safaricom

" ሳፋሪኮም በፈረንጆቹ 2022 በኢትዮጵያ የቴሌኮም ዘርፍ 300 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ወጪ ያደርጋል " - አንዋር ሱሳ

የኬንያው የቴሌኮም ኩባንያ ሳፋሪኮም በፈረንጆቹ 2022 በኢትዮጵያ የቴሌኮም ዘርፍ 300 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ወጪ መዋዕለ ነዋይ እንደሚያፈስ ገልጿል።

የሳፋሪኮም የኢትዮጵያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አንዋር ሱሳ ኩባንያው በተያዘው የፈረንጆቹ 2022 ወደ 300 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ በኢትዮጵያ ፈሰስ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

ኩባንያው በኢትዮጵያ ስራውን ለመጀመር የኔትወርክ ዝርጋታ እያካሄደ መሆኑንና የመጀመሪያ የመረጃ ማዕከሉን በ100 ሚሊዮን ዶላር ወጪ መዘርጋቱን ተናግረዋል።

ሳፋሪኮም በመጪዎቹ ጥቂት ወራት ውስጥ አገልግሎቱን በይፋ ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል።

#ኢዜአ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#GeneralDagallo ጄነራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር እንዲሁም ከሌሎች አመራሮች ጋር መገናኘታቸውን ገልፀዋል። ጄነራሉ ባጋሩት ፎቶ : ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፣ ከኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና ከሀገር መከላከያ ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ ጋር መገናኘታቸውን ያሳያል። …
" ከሱዳን ጋር ተቀራርበን መስራት እንደሚገባን መግባባት ላይ ደርሰናል " - ዶ/ር አብርሃም በላይ

ከሱዳን ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ተቀራርበን መስራት እንደሚገባን መግባባት ላይ ደርሰናል ሲሉ የአገር መከላከያ ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ ገልፀዋል።

የሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት ጄኔራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ በኢትዮጵያ የነበራቸውን የሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት አጠናቀው ዛሬ ወደ አገራቸው ሲመለሱ ዶክተር አብርሃም አሸኛኘት አድርገውላቸዋል።

የጄኔራል ዳጋሎን የኢትዮጵያ ቆይታን በተመለከተ ዶክተር አብርሃም ለኢዜአ እንደገለጹት ፤ በኢትዮጵያ እና በሱዳን የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሂዷል።

“አብረንና ተቀራርበን መስራት እንደሚገባን ተግባብተናል” ሲሉም ገልጸዋል።

ትናንት አዲስ አበባ የገቡት ጄኔራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አቢይ አህመድ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረጋቸው ተገልጿል።

ጄኔራሉ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ በተጨማሪ ከአገር መከላከያ ሚኒስትሩ ዶክተር አብርሃም በላይ እና ከኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋር መወያየታቸው ይታወሳል።

#ኢዜአ

@tikvahethiopia
#AU

የአፍሪካ ህብረት ሰንደቅዓላማ ...

የአፍሪካ የራሱ ሰንደቅዓላማ ያልነበረው ሲሆን በ2004 ግን መለያ ሰንደቅዓላማ አዘጋጅቶ ነበር።

በ8ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እኤአ ጥር 29 እና 30 ቀን 2007 በአዲስ አበባ ሲካሄድ ነባሩን ሰንደቅዓላማ የሚተካ አዲስ የህብረቱ ሰንደቅዓላማ እንዲዘጋጅ ውሳኔ ተላለፈ።

በወቅቱ የሊቢያ መሪና የህብረቱ ሊቀመንበር ሙአመር ጋዳፊ የሚመራው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ኃላፊነቱን ወስዶ ለህብረቱ ሰንደቅዓላማ ንድፍ መስራት ለሚፈልጉ ጥሪ አቀረበ።

የኮሚሽኑን ጥሪ ተከትሎ ከ19 የአፍሪካ ሀገራት ከ100 በላይ ግለሰቦች፣ ከዳያስፖራ 2 ግለሰቦች ከ100 በላይ ንድፎችን አስገቡ።

የሰንደቅዓላማ ንድፎቹ በባለሙያዎች ተመዘኑ። በትውልድ ኢትዮጵያዊ በዜግነት አሜሪካዊ የሆነው የግራፊክ ጠቢብ ያዴሳ ቦጂያ ያቀረበው ንድፍ አሸናፊ ሆነ።

ያሸነፈው የያዴሳ ንድፍ ሰንደቅዓላማ እንዲሆን እኤአ ጥር 31 ቀን 2010 በአዲስ አበባ በተካሄደው 14ኛው መደበኛ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ተወሰነ።

ያዴሳ ቦጂያ ያረቀቀውና አሁን በስራ ላይ ያለው የህብረቱ ሰንደቅዓላማ አረንጓዴ መደብ፣ በ55 ወርቃማ ኮከቦች የተከበበችና በነጭ የፀሐይ ጨረሮች ላይ ያረፈች አረንጓዴ የአፍሪካ ካርታን የያዘ ነው።

የአፍሪካ ካርታ በአረንጓዴ መወከሉ አህጉራዊ ተስፋን ለማሳየት ሲሆን፣ ነጭ የፀሐይ ጨረሮች ደግሞ አፍሪካውያንን ከተቀረው ዓለም ጋር በወዳጅነት፣ በጋራ የመኖር ግልፅ ፍላጎትን የሚያሳይ ነው።

አረንጓዴው የአፍሪካ ካርታ በ55 ወርቃማ ኮከቦች የተከበበ ሲሆን ተምሳሌትነቱ 55ቱን የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራትን፥ የአፍሪካን ፀጋዎችና ብሩህ ተስፋን የሚያሳይ ነው።

Credit : #ኢዜአ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ዶሮ እና የዶሮ ውጤቶችን ያለ ስጋት መጠቀም ይቻላል " - የኢትዮጵያ የዶሮ አርቢዎች እና አቀናባሪዎች ተከስቶ የነበረው የዶሮ በሽታ በቁጥጥር ስር መዋሉን ተከትሎ ተጥሎ የነበረው ገደብ ተነሳ። በኢትዮጵያ በተከሰተው የዶሮ በሽታ ምክንያት በዶሮና የዶሮ ውጤቶች ላይ ተጥሎ የቆየው ገደብ መነሳቱን የኢትዮጵያ የዶሮ አርቢዎች እና አቀናባሪዎች ማህበር ዛሬ ባወጣው መግለጫ አሳውቋል። ባለፉት…
" ዶሮና እንቁላል ያለስጋት መመገብ ይችላል " ግብርና ሚኒስቴር

ግብርና ሚኒስቴር በቅርቡ የተከሰተው የዶሮ በሽታ በቁጥጥር ሥር በመዋሉ ሕብረተሰቡ ያለምንም ስጋት ዶሮና እንቁላል መመገብ እንደሚችል አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ ይህን ያሳወቀው ከኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመሆን ለኢዜአ በሰጠው መግለጫ ነው።

ባሳለፍነው ሰኔ ወር መባቻ በቢሾፍቱና በምዕራብ አዲስ አበባ የተከሰተው የዶሮ በሽታ ወረርሽኝ በዶሮ እርባታ ቦታዎች ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል ያለው ግብርና ሚኒስቴር በሽታው እንደተከሰተ ከግብርና ሚኒስቴር፣ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትና ሌሎች ባለድርሻ ተቋማት የተውጣጣ ግብረ-ኃይል ተሰማርቶ የበሽታውን ሥርጭት የመግታት አፋጣኝ ምላሽ መውሰዱን አሳውቋል።

በወቅቱ ለዶሮ እርባታ አገልግሎት ከውጭ የሚገባው የለማ እንቁላልና ዶሮና የዶሮ ውጤቶች ዝውውር ባለበት እንዲገታ የጥንቃቄ መመሪያዎች ለሚመለከታቸው አካላት መተላለፉንም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስታውሷል።

በተጨማሪ ዶሮና እንቁላል አመጋገብ ላይ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጥሪ መተላለፉን ገልጾ በሂደት የጥንቃቄ መመሪያዎች እየተሻሻሉ መሄዳቸውን አሳውቋል።

በሽታውን ለመከላከል በተከናወኑ ተግባራት ምክንያት በሽታውን በቁጥጥር ሥር ማዋል ተችሏል ያለው ግብርና ሚኒስቴር አሁን ላይ ምንም አይነት የበሽታ ስጋት ባለመኖሩ ሕብረተሰቡ ዶሮና እንቁላል ያለስጋት በማብሰል እንዲጠቀም፤ ዶሮ አርቢዎችም በሙሉ አቅማቸው ዶሮ በማርባት ለገበያ እንዲያቀርቡ መወሰኑን ገልጿል።

በዶሮ እርባታ የተሰማሩ ዜጎች ግን በማንኛውም ጊዜ የሚያደርጉትን ‘ባዮ-ሴኪዩሪቲ’ የተሰኘውን የዶሮ እርባታ ጥንቃቄ ሥርዓትን ባጠናከረ አግባብ መንቀሳቀስ እንዳለባቸው ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

ተጨማሪ : telegra.ph/MoA-07-29

#ኢዜአ

@tikvahethiopia
#መታወቂያ

በአዲስ አበባ ታግዶ የቆየው የመታወቂያ እድሳት በተያዘው ጥቅምት ወር መጨረሻ እንደሚጀመር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ ዋና ስራ አስኪያጅ ጥራቱ በየነ ገልፀዋል።

አቶ ጥራቱ በየነ ለኢዜአ የሰጡት ቃል፦

- በመታወቂያ አሰጣጥና እድሳት ዙሪያ ለተስተዋሉ ብልሹ አሰራሮች ዘላቂ እልባት በመስጠት ችግሩን ለመፍታት አገልግሎቱ በጊዜያዊነት እንዲቆም ተደርጎ ነበር።

- በብልሹ ተግባሩ ላይ ተሳታፊ የነበሩ አመራሮችና ሰራተኞችን በመለየት ተጠያቂ የማድረግ ስራ ተከናውኗል።

- በሁሉም ክፍለ ከተሞች በተለይም ችግሩ ጎልቶ በታየባቸው 37 ወረዳዎች በተደረገ ክትትል 90 አመራሮችና ባለሙያዎችን ተጠያቂ ተደርጓል።

- ታግዶ የቆየው #የመታወቂያ_እድሳት ህጋዊ አሰራሩን ተከትሎ በተያዘው ጥቅምት ወር መጨረሻ ይጀመራል። ከዚህ ጎን ለጎን የከተማዋ ነዋሪዎች የዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ እንዲሆንኑአሰራሩን የማዘመን ስራ ይቀጥላል ነው የተባለው፡፡

- በአሁኑ ወቅት የራሳቸው መለያና ምሥጥራዊነት ያላቸው መታወቂያ ለመስጠት የሚያገለግሉ ወረቀቶች በመታተም ላይ መሆናቸውን ገልጸው በቀጣይ ለነዋሪው የመስጠት ተግባር ይከናወናል ብለዋል።

#ኢዜአ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የዩኒቨርሲቲ መምህራን እና ቴክኒካል ረዳቶች ጥያቄ ምንድነው ? ፤ የትምህርት ሚኒስቴር ምላሽስ ? • " እንደዚህ ዓይት ውሳኔ ላይ የተደረሰው አጠቃላይ የዩኒቨርሲቲ መምህራን ኃላፊዎች ውይይት ካደረጉ በኋላ ነው " - የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበር ፕሬዘዳንት ፍቅረስላሴ አካሉ (ለአዲስ ስታንዳርድ) • " ማህበራችን የሥራ ማቆም አድማ እንዲደረግ ጥሪ አላቀረበም " - ዶ/ር በፍቃዱ ዘለቀ (ለዶቼ…
" የተሰራጨውን የአቋም መግለጫ አላውቀውም " - የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ፤ በኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራንና ቴክኒካል ረዳቶች ስም የተሰራጨውን አቋም አላውቀውም ብሏል።

ማህበሩ ይህን ያለው #ለኢዜአ በላከው መግለጫ ነው።

ማህበሩ ፤ ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ ትምሀርት ድረስ መምህራንና የትምህርት ባለሙያዎችን በማደራጀት በአምስት ዓላማዎች እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ ገልጿል።

ከአምስቱ ዓላማዎች መካከል አንዱ የመምህራን መብትና ጥቅም ማስከበር ነው ያለ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የዩኒቨርሲቲ መምራን ያነሱትን ጥያቄዎች ለትምህርት ሚኒስቴርና ለሚመለክታቸው የፌዴራል መንግስት አካላት እያቀረበ ለመፍትሄው እየሰራ መሆኑን አመልክቷል።

" አንዳንድ ጥያቄዎች በፍጥነት ምላሽ ማግኘት የሚገባቸው መሆኑን " እናምናለን ያለው ማህበሩ " አንዳንዶቹ ደግሞ ጊዜ የሚፈልጉ መሆናቸው ሊታወቅ ይገባል " ብሏል።

ማህበሩ ከሰሞኑን " የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራንና ቴክኒካል ረዳቶች የአቋም መግለጫ "  በሚል ርዕስ  " ከህዳር 26/2015 ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የሥራ ማቆም አድማ እናደርጋለን " በሚል በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨውን መረጃ አላውቀውም ብሏል።

እውቅና ያለው የማህበሩ መዋቅር ስም  " የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ማህበር "  መሆኑን የገለፀው ማህበሩ ፤ መምህራን ማህበራቸው ጉዳዩን በጥብቅ ይዞ እየሰራ መሆኑን አውቀው የተለመደውን የማስተማር የምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎት በሙያዊ ኃላፊነታቸው እንዲቀጥሉ ጥሪውን አቅርቧል።

#ኢዜአ

ማስታወሻ : https://t.me/tikvahethiopia/74911

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray

በሽረ ከተማ የሚገኘው መናኸሪያ መቐለ ጨምሮ ወደ ተለያዩ የትግራይ ክልል ከተሞች የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ተገልጋዮችን እና የመናኸሪያውን የስራ ኃላፊዎች ዋቢ በማድረግ ኢዜአ ዘግቧል።

ተጓዦች በጦርነቱ ምክንያት የትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጦ በመቆየቱ ለከፍተኛ ችግር ተጋልጠው እንደነበር ገልጸዋል።

የፌደራል መንግስት ከህወሓት ጋር የሰላም ስምምነት መድረሱን ተከትሎ ግን መቐለን ጨምሮ ወደ ተለያዩ የትግራይ ክልል ከተሞች የትራንስፖርት እንቅስቃሴ መጀመሩን አስረድተዋል።

የተፈጠረው ሰላም ከፍተኛ እፎይታና ደስታ እንደፈጠረላቸው ጠቁመዋል።

የሽረ ከተማ መናኸሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ተክላይ ገብረየሱስ  በበኩለቸው ፤ የሽረ መናኸሪያ መቐለን ጨምሮ ወደ ተለያዩ የትግራይ ክልል ከተሞች ለሚንቀሳቀሱ የህዝብ ማመላለሻ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ መኪኖች ስምሪት እየሰጠ ነው ብለዋል።

የትራንስፖርት እንቅስቃሴ መጀመሩ አሽከርካሪዎች ወደ ስራ እንዲመለሱ፣ ተሳፋሪዎች ደግሞ ወደ ሚፈልጉት ከተማ እንዲንቀሳቀሱ ማስቻሉን አንስተዋል።

የትራንስፖርት አገልግሎቱን ለማሳለጥ መንግስት ነዳጅ እያቀረበ መሆኑን ጠቁመው፥ በቀጣይ ለህብረተሰቡ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የጀመሩትን ስራ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ይደረጋል ሲሉ ለኢዜአ ተናግረዋል።

#ኢዜአ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ነዳጅ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በማደያዎች የነዳጅ ግብይትን በዲጂታል የማካሄድ የሙከራ ትግበራ  ሥራ መጀመሩን አሳውቋል። ግንቦት 1 ቀን 2015 ዓ.ም ደግሞ በመላ ሀገሪቱ የዲጂታል የነዳጅ ግብይት ይጀመራል ተብሏል። ዛሬ በአዲስ አበባ ለሙከራ የተጀመረው የዲጂታል ግብይት በሁሉም ተሽከርካሪዎች እና በሁሉም ማደያዎች ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል። ግብይቱ በዲጂታል መሆኑ ምርት እንዳይባክን…
#ነዳጅ

" ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት #በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈፀማል " - የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን

ከሚያዚያ 16 ጀምሮ አዲስ አበባ ውስጥ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ #በኤሌክትሮኒክስ_የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገልጿል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ገልጾ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት #በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም አሳውቋል።

በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ #ከሐምሌ_አንድ ጀምሮ #በአስገዳጅነት እንደሚተገበር ተጠቁሟል።

ኢትዮ ቴሌኮም በበኩሉ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በ " ቴሌ ብር " ውጤታማ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ገልጿል።

ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በ " ቴሌ ብር " ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አመልክቷል።

የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ ቴክኖሎጂ መገንባቱንም አስረድቷል።

የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር ደግሞ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ያለ ሲሆን በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን ይፈታል ብሏል።

ከዚህ በተጨማሪ መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ሲል አሳውቋል።

#ኢዜአ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba በአዲስ አበባ ከአራት ዓመታት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ የመሬት ሊዝ ጨረታ መውጣቱን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከአራት ዓመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የመሬት ሊዝ ጨረታ ያወጣ ሲሆን ለጨረታ የቀረቡት ይዞታዎች መነሻ ዋጋ ከፍተኛው 2,213 ብር መሆኑ ታውቋል። የአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ዛሬ ግንቦት 7 ቀን 2015 ዓም…
#Update #የመሬት_ሊዝ_ጨረታ

" በ7 ክ/ከተሞች የመሬት ሊዝ ጨረታ አሸናፊዎች ከአፍታ ቆይታ በኃላ ይለያሉ " - የአ/አ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ላለፉት አምስት ዓመታት ተቋርጦ የነበረውን የመሬት ሊዝ ጨረታ ዛሬ አስጀምሯል።

ይህንንም ተከትሎ ቢሮው በሁሉም ክፍለ ከተሞች 14 ነጥብ 13 ሄክታር መሬት በሊዝ ለማጫረት ማዘጋጀቱን ገልጿል።

በጨረታ የቀረበው መሬት አገራዊ ፋይዳ ላላቸው ለተለያዩ ዓላማዎች የሚውል ነው ተብሏል።

በአስራ አንዱ ክፍለ ከተሞች 24 ሺህ የጨረታ ሰነዶችን በማዘጋጀት ባለፋት አስር ቀናት 21 ሺህ 636 የሚሆኑት የጨረታ ሰነዶች መሸጥ መቻሉም ተጠቁሟል።

የመጀመሪያው ጨረታ #በዛሬው ዕለት በ7 ክፍለ ከተሞች ፦
👉 በቦሌ፣
👉 በንፋስ ስልክ ላፍቶ፣
👉 በልደታ፣
👉 በአዲስ ከተማ፣
👉 በቂርቆስ፣
👉 በጉለሌና በየካ ክፍለ ከተሞች ተጀምሯል።

በእነዚህ ክፍለ ከተሞች 2 ሺህ 852 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዶቻቸውን ወደ ጨረታ ሳጥኑ አስገብተዋል።

የጨረታ ሂደቱ አሁን በመካሄድ ላይ ሲሆን አሸናፊዎች ከአፍታ ቆይታ በኋላ የሚለዩ ይሆናል።

በቀጣዮች ቀናት የጨረታ ሒደቱ በሌሎች ክ/ከተሞች እንደሚቀጥል ታውቋል።

#ኢዜአ

@tikvahethiopia
#AAU

አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤ በትግራይ ክልል ለሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መልሶ ማቋቋሚያ ከ12 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጉን አሳውቋል።

ይኸው ድጋፍ ዛሬ ወደ ክልሉ መላኩን ተቋሙ ገልጿል።

ድጋፉ 11 ሚሊዮን ብር በጥሬ ገንዘብ ሲሆን ቀሪው አንድ ሚሊዮን ብር የሚያወጡ ኮምፒዩተሮችና የህክምና መሳሪያ ቁሳቁሶች መሆናቸው ተገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው መሰል ድጋፎችን በቀጣይነት ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አሳውቆ በምርምርና ቴክኖሎጂዎች ረገድም በመልሶ ማቋቋሚያ ስራዎች ላይ የራሱን እገዛ እንደሚያደርግም ገልጿል።

#ኢዜአ

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
" ዝግጅቱ ተጠናቋል " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ዝግጅት #መጠናቀቁን አስታወቀ።

ፈተናው ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል።

በሚኒስቴሩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ እዮብ አየነው (ዶ/ር) ለኢዜአ በሰጡት ቃል ፤ " የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂ ተማሪዎችን እውቀትና ብቃት ለመለካት የሚሰጠው የመውጫ ፈተና ዝግጅት ተጠናቋል " ብለዋል።

የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የትክክለኛ ተፈታኞችን ቁጥር እንዲያጣራ በማድረግ ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት 95 ሺህ 755 እንዲሁም ከመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች 74 ሺህ 776 ተማሪዎች ለፈተና ይቀመጣሉ ሲሉ ገልጸዋል።

ፈተናውን ያላለፉ ተማሪዎቸ ዲግሪ እንደማይሰጣቸው እና የትምህርት ሚኒስቴር በሚያዘጋጀው የፈተና ጊዜ መሰረት ድጋሚ እንደሚፈተኑ አመልክተዋል።

ተማሪዎች በትምህርት ቆይታቸው ከተማሯቸው የትምህርት ዓይነቶች መካከል መሰረታዊ የሚባሉ ከ12 እስከ 17 የትምህርት ዓይነቶች ፈተና እንደሚወጣ ገልጸዋል፡፡

ለዚህም የፈተና ንድፍና የብቃት መመዘኛ መስፈርቶች መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል፡፡

ከግንቦት 15 ጀምሮ ለ211 የትምህርት ፕሮግራሞች የፈተና ጥያቄዎች በማውጣት ለፈተናው ሙሉ ለሙሉ ዝግጁ እንዲሆን መደረጉን ተናግረዋል።

ፈተናው በኦንላየን የሚሰጥ በመሆኑም አስፈላጊ የቴሌኮም እና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን ዝግጁ ለማድረግ እየተሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል።

በሀገሪቱ ካሉ 325 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት 161 እና ከመንግስት ደግሞ 44 ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እንደሚያስፈትኑ ጠቅሰዋል።

ዶ/ር እዮብ ፤ " ገበያው የሚፈልገውን ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት የመውጫ ፈተናው ከ2015 ጀምሮ በሁሉም የትምህርት መስኮችና መርሐ ግብሮች መስጠት እንዲቻል ስራዎች ከአንድ ዓመት በላይ ሲሰሩ ቆይቷል " ሲሉ አስታውሰዋል።

#ኢዜአ

@tikvahethiopia
#ቁልቢ

ዓመታዊው የቁልቢ ገብርኤል የንግስ በዓልን ለማክበር ወደ ስፍራው የሚመጡ ምዕመናንና እንግዶችን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ ዝግጅት ማድረጉን ፖሊስ አሳውቋል።

የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ እና የበዓሉ የጸጥታ ኮማንድ በመጪው ረቡዕ በሚከበረው ዓመታዊ የቁልቢ ንግስ በዓል ላይ ከተለያየ የውጭ እና የሀገር ውስጥ ብዛት ያላቸው ምዕመናን፣ ቱሪስቶችና ሌሎችም እንግዶች ወደ ስፍራው እንደሚመጡ ይጠበቃል ብለዋል።

የምዕመናኑን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅም ከምዕራብ ሐረርጌ ዞን ፣ከድሬዳዋ አስተዳደር፣ ከሐረሪ ክልል እና ከፌዴራል ፖሊስ እንዲሁም ከመከላከያ ሠራዊት፣ ብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት ጋር በመቀናጀት ዝግጅት መደረጉ ተገልጿል።

የበዓሉ ታዳሚዎች የግል ንብረቶቻቸውን እንዳይሰረቅ በጥንቃቄ በመያዝና የወንጀል ድርጊት ሲመለከቱ በማጋለጥ የድርሻቸውን መወጣት አለባቸው ተብሏል።

በንግስ በዓሉ ላይ ሶስት ጊዜያዊ ፖሊስ ጣቢያና ተጠርጣሪ ወንጀለኞችም ሲያዙ ውሳኔ ለመሰጠት ዐቃቤ ህግና ጊዜያዊ ፍርድ ቤት ተቋቁሟል።

ወደ ስፍራው በሚያመራው መንገድ አልፎ አልፎ ያለው አካባቢ የመሬቱ አቀማመጥ ዳገታማ፣ ቁልቁለታማና ጠመዝማዛ በመሆኑ አሽከርካሪዎች የትራፊክ ህግና ደንብ በማክበር አደጋን ለመከላከል የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው መልዕክት ተላልፏል።

ከዛሬ ሐምሌ 17 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ከጨለንቆ ከተማ እስከ ቀርሳ ከተማ ባለው ዋናው የተሸከርካሪ መንገድ ላይ #ከባድ_መኪና ማለፍ የተከለከለ መሆኑንም ተገልጿል።

ምዕመናን ወደ ንግስ ስፍራው በሚመጡበት ወቅት ተገቢነት የሌላቸው አርማና ምልክቶችን ይዘው መገኘት እንደሌለባቸውም ፖሊስ አሳስቧል። #ኢዜአ

@tikvahethiopia
" የትምህርት ሚኒስቴር በዋናነት ለተገኘው ውጤት የኔ ውድቀት ነው ብሎ ኃላፊነቱን ሊወስድ ይገባል " - ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ

የትምህርት ሚኒስቴር ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝቅተኛ ውጤት መመዝገብ ምክንያት የሆኑ ችግሮችን በጥናት ለይቶ እንዲያቀርብ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰዉ ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጠየቀ።

በይህ የተጠየቀው በምክር ቤቱ የሰዉ ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የትምህርት ሚኒስቴርን የ2016 እቅድና የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ዛሬ ሲገመግም ነው።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ " ቀደም ሲል ሲሰጡ የነበሩ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤቶች የተማሪዎችን ትክክለኛ ችሎታ ያሳዩ አልነበሩም " ብለዋል።

የፈተና አሰጣጡን በመቀየር የተመዘገበው የተማሪዎች ውጤት በዘርፉ ከዚህ ቀደም የነበሩ ችግሮች ማሳያ መሆናቸውን ጠቁመው ለዚህም ከወላጆች ጀምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተጠያቂ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የትምህርት ጥራት ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑን ጠቅሰው እየተካሄዱ ያሉ የትምህርት ቤቶች ማሻሻያ መርኃ ግብሮችና የመምህራን አቅም ግንባታ ሥራዎችን ለአብነት አንስተዋል።

በምክር ቤቱ የሰዉ ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶክተር ነገሪ ሌንጮ ፤ " ሚኒስቴሩ ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝቅተኛ ውጤት መምጣት ሁሉንም ተጠያቂ ማድረግ አይቻልም " ብለዋል።

በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር የማስተማርና ፈተና የማስፈተን ተልዕኮ ተሰጥቶት እንደሚሰራ ተቋም በዋናነት ለተገኘው ውጤት ኃላፊነቱን ሊወስድ ይገባዋል ነው ያሉት።

ትምህርት ሚኒስቴርን ጨምሮ ተጠሪ ተቋማትና የትምህርቱ ዘርፍ ተዋንያን ለውጤቱ የነበራቸው ድርሻ ተለይቶ መቅረብ እንዳለበትም አሳስበዋል።

ለተማሪዎች ዝቅተኛ ውጤት ማጣት ምክንያት የሆኑ ሌሎች ችግሮችም በጥናት ተለይተው ሊቀርቡ እንደሚገባም ዶክተር ነገሪ ተናግረዋል። #ኢዜአ

@tikvahethiopia
#አሁን #ሲዳማ

የሲዳማ ክልል ም/ ቤት አስቸኳይ ጉባዔ በሀዋሳ እያካሄደ ነው።

ምክር ቤቱ 6ኛ ዙር 3ኛ የስራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ነው እያካሄደ ያለው።

ለአንድ ቀን ብቻ ይካሄዳል በተባለው በዚህ አስቸኳይ ጉባኤ በሶሰት የተለያዩ አጃንዳዎች ላይ ውይይት ይደረጋል ተብሏል።

- ለጉባኤው ሞሽን ቀርቦ ይጸድቃል።

- የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ የስራ ሃላፊዎች ሹመት ለምክር ቤቱ አቅርበው ያፀድቃሉ።

- የምክር ቤቱ አባላት #የህግ_ከለላ ማንሳት ላይ ተወያይተው ውሳኔ ይሰጣሉ።

#ኢዜአ

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ በቀላል ባቡር እና ቀለበት መንገዶች 30 የእግረኛ ማቋረጫ ተሻጋሪ ድልድዮችና መተላለፊያዎች ሊገነቡ መሆኑን የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን አስታውቋል።

በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር በሚያልፍባቸውና ውስጠኛው ቀለበት መንገድ ተብለው በሚጠሩ ቦታዎች ላይ መሸጋገሪያ ድልድዮችና መተላለፊያዎች ባለመኖራቸው እግረኞች ለትራፊክ አደጋ እየተጋለጡና መንገድ ለማቋረጥ ረዥም ርቀት ለመጓዝ እንደሚገደዱ ባለስልጣን መ/ቤቱ ገልጿል።

በመሆኑም ፤ 30 የእግረኛ ማቋረጫ ተሻጋሪ ድልድዮችና መተላለፊያዎች እንደሚገነቡ ይፋ አድርጓል።

ተሻጋሪ ድልድዮቹና መተላለፊያ መስመሮቹ ከመሬት በላይ እንዲሁም በመሬት ውስጥ እንደሚገነቡ ጠቁሟል።

የእግረኛ ተሻጋሪ ድልድዮቹ ፦
- ሐና ማርያም፣
- ኃይሌ ጋርመንት፣
- ሳሪስ ሐኪም ማሞ ሰፈር፣
- አደይ አበባ፣
- ጉርድ ሾላ፣
- አውቶቡስ ተራና አብነት አካባቢ እንዲሁም በሌሎችም አካባቢዎች ነው የሚገነቡት ብሏል። #ኢዜአ

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

" ፈተናው በሰኔ ወር መጀመሪያ ይሰጣል " - የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ

በአዲስ አበባ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የ2016 ዓ.ም ከተማ አቀፍ ፈተና በሰኔ ወር መጀመሪያ ይሰጣል፡፡

ከተማ አቀፍ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ፈተና ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰጠው አቅጣጫ መሰረት በዚህ ዓመት በሰኔ ወር መጀመሪያ ላይ እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ገልጿል።

በዚህም በአዲስ አበባ ለ6ኛ ክፍል 86,691 ተማሪዎች እንዲሁም ለ8ኛ ክፍል 88,028 ተማሪዎች በከተማ አቀፍ ፈተናው ይቀመጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አሳውቋል። #ኢዜአ

@tikvahuniversity
#Ethiopia

በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ መርሐ ግብር ሊጀምር ነው።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከመጪው #መስከረም_ወር ጀምሮ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ መርሐግብር እንደሚጀምር አስታውቋል።

ዩኒቨርሲቲው በቅደመ ምረቃና ድህረ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራሞች ተመርቀው የስራ ዓለም ውስጥ ለሚገቡ ተመራቂዎች ራሱን የቻለ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ እንደሚሰጥ ገልጿል።

ፕሮግራሙ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና የገበያውን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ነው ያለው ዩኒቨርሲቲው " ይህ መርሐ ግብር በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጥ ነው " ብሏል።

" የፕሮግራሙ መጀመር በሥራ ገበያው ውስጥ ብቁ ሙያተኞችን ለማግኘትና የዩኒቨርሲቲውን አቅምና ብቃት ያለው ባለሙያ የማፍራት ተልዕኮ የሚያሳካ ነው " ሲል ገልጿል።

የሙያ ብቃት ማረጋገጫው #በሁሉም_ዘርፎች ላይ የሚሰጥ ሲሆን ይህ የሚመራበት አሰራር ይዘረጋል ተብሏል።

በትምህርት ስርዓት ውስጥ ያሉ #ተማሪዎችም ሆኑ በስራ ገበያ ያሉ ሰራተኞችና ምሁራን ለተማሩበት ሙያ የብቃት ማረጋገጫ ወይም #ፕሮፌሽናል_ሰርትፊኬት መውሰድ እንደሚችሉ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አሳውቋል። #ኢዜአ

@tikvahethiopia