TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
የኮቪድ - 19 ወረርሽኝ እጅግ አስከፊ በነበረበት ወቅት በኮንትራንት ተቀጥረው ሀገራቸውን እና ህዝባቸውን ሲያገለግሉ የነበሩ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት የጤና ባለሞያዎች ፦ " እኛ በጤና ሚኒስትር በኩል በኮቪድ ላይ በኮንትራት ተቀጥረን የምንሰራ ባለሙያዎች ነን። ኮቪድ ከጀመረ አንስቶ እስከ አሁን ድረስ በተለያዩ ሆስፒታሎች ስናገለግል ቆይተናል። የጤና ሚኒሰትር እና ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በቋሚነት…
" ከታህሳስ 30 በኃላ ከስራ ገበታችን ልንሰናበት ነው " ያሉ የጤና ባለሞያዎች ለሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ደብዳቤ ፃፉ።

ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ግልፅ ደብዳቤ የፃፉት በCOVID-19 ወረርሽኝ ግዜ በጤና ሚኒስቴር በኮንትራት ተቀጥረው እየሰሩ የሚገኙ የጤና ባለሞያዎች ናቸው።

ጉዳዩን ያስረዱት የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ፤ " ጤና ሚኒስቴር ከሲቪል ሰርቪስ ጋር በመነጋገር  ከሐምሌ 1 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ለኮቪድ 19 ወረርሽኝ ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በኮንትራት ከቀጠረን መካከል 1407 የጤና ባለሞያዎች ቋሚ እንደሆንን በደብዳቤ አሳውቆናል፤ ከ1000 በላይ የጤና ባለሞያዎች ቋሚ ከሆኑ  በኋላ ግን የተቀረነውን ከ350 - 400 የምንሆን የጤና ባለሞያዎች በተስፋ ከነገ ዛሬ ቋሚ ያርጉናል ብለን ሰንጠብቅ ከነአካቴው ከስራ ሊያሰናብቱን ነው " ብለዋል።

የጤና ባለሞያዎቹ ከታህሳስ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ከስራ እንደሚሰናበቱ በማሰብ ከፍተኛ ጭንቀት ዉስጥ መሆናቸውን ገልጸዋል።

እነዚህ በቁጥር ከ300 በላይ እንደሆነ ያመለከቱት የጤና ባለሞያዎች ለጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በፃፉት ደብዳቤ ፤ ጉዳዩን በተመለከተ መፍትሄ ለመፈለግ ከታች የጤና ሚኒስቴር ሰው ሀብት ክፍል እስከ ጤና ሚኒስትሯ ድረስ ብንጠይቅም መፍትሄ ቀርቶ የሚያፅናና ቃል ሊሰጠን አልቻለም ብለዋል።

" 3 አመት ሙሉ ህዝብንና ሃገርን ያገለገልን ጤና ባለሙያዎች በዚ መልኩ #ሞራልን_ጎድቶ መግፋት ለሙያውም ለስርአቱም ገፅታ ጥሩ አደለም ብቻ ሳይሆን ትልቅ ጠባሳን የሚጥል ነው "  ያሉት የጤና ባለሞያዎቹ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጡን ሲሉ ጠይቀዋል።

(ለጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ የፃፉት ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia