TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ETHIOPIA #AU #AddisAbaba

አዲስ አበባ ከአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ጋር በተያያዘ እንግዶቿን ተቀብላ እያስተናገደች ትገኛለች።

የጸጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ሃይል፤ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት አድርጌያለሁ፤ ስምሪትም በመውሰድ ስራ ላይ እገኛለሁ ብሏል።

በጉባኤው ለመሳተፍ ከተለያዩ ሀገራት የመጡና አሁንም የሚመጡ መሪዎችን እና ዲፕሎማቶችን ደህንነት  ለመጠበቅ በቂ ዝግጅት ማድረጉን አመልክቷል።

- በሆቴሎች፣
- በመዝናኛ እና በገበያ ስፍራዎች
- እንግዶቹ ከቦታ ቦታ በሚንቀሳቀሱባቸው አካባቢዎች ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሆነም አሳውቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ወንጀሎች እንዳይፈፀሙ እና ምንም አይነት የደህንነት ስጋት እንዳይኖር ከፀጥታ አካላቱ ጋር ተቀናጅተው በመስራት እንደወትሮው ሁሉ አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር እንዲያደርጉ የጋራ ግብረኃይሉ ጠይቋል፡፡

በተለይ #መንገዶች_ዝግ በሚደረጉበት ወቅት አሽከርካሪዎች እና እግረኞች #በትዕግስት በመጠበቅ ወይም ሌሎች አማራጭ መንገዶችን በመጠቀም ለሀገር ገፅታ ግንባታ ላይ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርቧል።

አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙና የፖሊስ አገልግሎት ለማግኘት በስልክ ቁጥር ፦
👉 011-111-01-11፣
👉 011-552-63-03፣
👉 011-552-40-77፣
👉 011-554-36-78
👉 011-5-54-36-81 እንዲሁም በ987፣ 991 እና 816 ነፃ የስልክ መስመሮች ጥቆማ መስጠት ይቻላል ተብሏል።

@tikvahethiopia