TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ATTENTION

ሠመራ እና ዱብቲ ከተሞች ላይ ከፍተኛ የሆነ ንፋስ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ ምክንያት ፦
- ሠመራ፣
- ዱብቲ፣
- አይሳኢታ፣
- ሎጊያ እና ሚሌ ከተሞች ላይ ዛሬ በ23/12/2013 ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋርጧል።

የአፋር ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተቋረጠውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመመለስ የጥገና ሰራተኞች ርብርብ እያደረጉ እንደሚገኙ ጠቁሟል።

በሠመራና ዱብቲ ከተሞች የሚገኙ ዜጎች የወደቀ የኤሌክትሪክ ምሰሶ እና የተበጠሰ የኤሌክትሪክ ገመድ በአካባቢያቸው ካለ ጉዳት እንዳያደርስ በስልክ ቁጥር 0910123048 ጥቆማ እንዲሰጡ ተጠይቋል።

#SHARE #ሼር

@tikvahethiopia
#AddisAbaba : ነገ የሚዘጉ መንገዶች !

መሰከረም 16/2014 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ የሚከበረው የደመራ በዓል ተጀምሮ አስከሚጠናቀቅ ከዚህ በታች የተገለፁትን መንገዶች ዝግ ስለሚሆኑ አሽከርካሪዎች ሌሎች አማራጮችን እንዲጠቀሙ ከአ/አ ፖሊስ ማሳሰቢያ ተላፍሏል።

የሚዘጉት መንገዶች ፦

• ከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒየም አዳራሽ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ደንበል ሲቲ ሴንተር ኦሎምፒያ አደባባይ አከባቢ፤
• ከመገናኛ ፣ በሃያ ሁለት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቦሌ መድሃኒያለም፣ በአትላስ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያ አካባቢ፤
• ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ባሻወልዴ ችሎት ወይም ፓርላማ መብራት፤
• ከፒያሣ አካባቢ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቸርችር ጎዳና ቴዎድሮስ አደባባይ፤
• ከተክለ ሀይማኖት በሜትሮሎጂ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መስሪያ ቤት አካባቢ፤
• ከተክለ ሀይማኖት ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ የኋላ በር አካባቢ፤
• ከሲኒማ ራስ በጎላ ሚካኤል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኢምግሬሽን የኋላ በር መግቢያ፤
• ከጌጃ ሰፈር ፣ ጤና ጥበቃ፣ ብሄራዊ ቲያትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ፤
• ከባሻ ወልዴ ችሎት በኦርማ ጋራዥ ወደፉል ውኋ መስኪድ የሚወስደው መንገድ ንግድ ማተሚያ ቤት ፤
• ከጎፋ በቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ወደ ለገሐር አዲሱ መንገድ የመወስደው መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ መስቀለኛው ላይ
• ከጦር ኃይሎች ፣ ልደታ ፣ ፖሊስ ሆስፒታል ሜክሲኮ አደባባይ
• ከሳሪስ በጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የቀድሞ አራተኛ ክፍለ ጦር አካባቢ ናቸው።

ስንት ሰዓት ነው የሚዘጋው ?

ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ሁሉ ዝግ ነው።

*** ሌላው ፦
ደመራው የሚደመርበት መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ወደ ስታዲዬም እንዲሁም ከሃራምቤ ሆቴል ወደ ሴንጅ ዮሴፍ የሚያቋርጠው መስቀለኛ መንገዱ ለበዓሉ በሚደረገው ዝግጅት ምክንያት ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ዝግ የሚደረግ ይሆናል፡፡

በተጨማሪም ከሳሪስ እና ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ከባድ ተሸከርካሪዎች መንገዱ አጎና ሲኒማ ጋር የሚዘጋ ይሆናል፡፡

#ሼር ያድርጉት !

@tikvahethiopia
#AddisAbaba - ማስታወሻ !

ዛሬ በመስቀል አደባባይ የሚከበረው የደመራ በዓል ተጀምሮ አስከሚጠናቀቅ ከዚህ በታች የተገለፁትን መንገዶች ዝግ ይሆናሉ።

የሚዘጉት መንገዶች ፦

• ከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒየም አዳራሽ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ደንበል ሲቲ ሴንተር ኦሎምፒያ አደባባይ አከባቢ፤
• ከመገናኛ ፣ በሃያ ሁለት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቦሌ መድሃኒያለም፣ በአትላስ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያ አካባቢ፤
• ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ባሻወልዴ ችሎት ወይም ፓርላማ መብራት፤
• ከፒያሣ አካባቢ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቸርችር ጎዳና ቴዎድሮስ አደባባይ፤
• ከተክለ ሀይማኖት በሜትሮሎጂ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መስሪያ ቤት አካባቢ፤
• ከተክለ ሀይማኖት ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ የኋላ በር አካባቢ፤
• ከሲኒማ ራስ በጎላ ሚካኤል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኢምግሬሽን የኋላ በር መግቢያ፤
• ከጌጃ ሰፈር ፣ ጤና ጥበቃ፣ ብሄራዊ ቲያትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ፤
• ከባሻ ወልዴ ችሎት በኦርማ ጋራዥ ወደፉል ውኋ መስኪድ የሚወስደው መንገድ ንግድ ማተሚያ ቤት ፤
• ከጎፋ በቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ወደ ለገሐር አዲሱ መንገድ የመወስደው መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ መስቀለኛው ላይ
• ከጦር ኃይሎች ፣ ልደታ ፣ ፖሊስ ሆስፒታል ሜክሲኮ አደባባይ
• ከሳሪስ በጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የቀድሞ አራተኛ ክፍለ ጦር አካባቢ ናቸው።

ስንት ሰዓት ነው የሚዘጋው ?

ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ሁሉ ዝግ ነው።

*** ሌላው ፦
ደመራው የሚደመርበት መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ወደ ስታዲዬም እንዲሁም ከሃራምቤ ሆቴል ወደ ሴንጅ ዮሴፍ የሚያቋርጠው መስቀለኛ መንገዱ ለበዓሉ በሚደረገው ዝግጅት ምክንያት ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ዝግ የሚደረግ ይሆናል፡፡

በተጨማሪም ከሳሪስ እና ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ከባድ ተሸከርካሪዎች መንገዱ አጎና ሲኒማ ጋር የሚዘጋ ይሆናል፡፡

#ሼር ያድርጉት !

@tikvahethiopia
#ማስጠንቀቂያ

" ሲሪስ አፕል ጁይስ " 100% የተሰኘው ጭማቂ በውስጡ ጎጂ የሆነ ከሻጋታ የመነጨ መርዛማ ኬሚካል ስለተገኘበት ምርቱን ህብረተሰቡ እንዳይጠቀም የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን ማሳሰቡን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

በፍራፍሬዎች ላይ የሚከሰት ማይኮቶክሲን የተሰኘው ከሻጋታ የሚመነጭ መርዛማ ኬሚካል በሲሪስ አፕል ጁይስ ውስጥ 100% ስለተገኘ ህብረተሰቡ እንዳይጠቀም ማስጠንቀቂያ ተላልፏል።

ምርቱ የዓለም አቀፍ የምግብ ደህንነት ማስጠንቀቂያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ምርቱ ጥቅም ላይ እንዳይውል ባለስልጣን መ/ቤቱ ያስጠነቀቀ ሲሆን፥ በተመሳሳይ የሲሪስ አፕል ጁይስ አምራች የሆነው የደቡብ አፍሪካ የምግብና የመጠጥ አምራች ምርቱ ማይኮቶክሲን የተሰኘው ከሻጋታ የሚመነጭ መርዛማ ኬሚካል በውስጡ በእንዳለ በመግለጽ ህብረተሰቡ እንዳይጠቀመው ነው ያሳሰበው፡፡

የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን ፥ ህብረተሰቡ የሲሪስ አፕል ጁይስ 100% ምርት በሀገራች ገበያ ውስጥ እንዳለ በመገንዘብ ምርቱን እንዳይጠቀም አስጠንቅቆ ÷ ምርቱን በማንኛውም አጋጣሚ ገበያ ላይ ሲገኝ በፌዴራል ደረጃ በነጻ ስልክ መስመር በ8482 እንዲሁም በአቅራቢያ ለሚገኙ የክልል ተቆጣጣሪ አካላት ጥቆማ እንዲሰጥ መልዕክት ማስተላልፏል።

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
#GONDAR

" ለመንገድ ስራ ደማሚት ይፈነዳል፤ እንዳትደናገጡ " - የጎንደር ፖሊስ

ከዛሬ ጥቅምት 8 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት ከኮሌጅ ብሪጋታ የመንገድ ስራ ለመስራት ደማሚት ይፈነዳል፡፡

ነዋሪዎች ጉዳዩን አውቀው ያለ ምንም መደናገጥ የዕለት ከዕለት ተግባራቸውን እንዲያከናውኑ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ መልእክት አስተላልፏል።

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
አዲስ አበባ !

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ማንኛውም አጠራጣሪ ጉዳዮችን ሲመለከቱ የሚያመለክቱበት ነፃ የስልክ መስመር ይፋ ሆነ።

ነዋሪዎች አጠራጣሪ ጉዳዮችን ሲመለከቱ የሚያሳውቁበት ነፃ የስልክ መስመር " 9977 " ነው።

#ሼር #SHARE

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA

ማንኛውም የፀጥታ ችግር እንቅስቃሴ ሲመለከቱ ወይም ደግሞ ጥቆማ ለመስጠት ከፈለጉ ከላይ በተቀመጡት የስልክ መስመሮች ፈጥነው እንዲደውሉ የፌዴራል ፖሊስ መልዕክት አስተላልፏል።

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ተጨማሪ አዳዲስ የደንብ ልብሶችን ስራ ላይ ማዋሉን ዛሬ አሳውቋል።

ነባሩን የደንብ ልብስ መጠቀም ማቆሙን ተቋሙ ገልጿል፡፡

ከዛሬ ጥቅምት 25 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ አዳዲሶቹ የደንብ አልባሳትን ብቻ መጠቀም እንደሚገባ እና ነባሩ የደንብ ልብስ ሙሉ በሙሉ መቀየሩ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ አሮጌውን የደንብ ልብስ ለብሶ የተገኘ አመራር እና አባል ላይ ጠንከር ያለ የዲስፕሊን እርምጃ ይወሰድበታል ተብሏል።

ህብረተሰቡ እና ባለድርሻ አካላት አሮጌው የደንብ ልብስ ሙሉ በሙሉ በአዳዲሶቹ መቀየሩን ተገንዝበው አሮጌውን የደንብ ልብስ የለበሰ የፖሊስ አባል ሲያጋጥማቸው መረጃ በመስጠት እንዲተባበሩ ጥሪ ቀርቧል።

በተጨማሪም የአዲስ አበባ ፖሊስ ስራ ላይ ካዋላቸው አዳዲስ የደንብ አልባሳት ጋር ወይም ከሌሎች የፀጥታ አካላት የደንብ ልብስ ጋር ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ ዩኒፎርም መጠቀም ክልክል መሆኑ በህግ የተደገገ ስለሆነ ከአ/አ ፖሊስ የደንብ ልብስ ጋር ተመሳሳይ ዩኒፎርም የሚጠቀሙ አካላት ማስተካከያ እንዲያደርጉ ተቋሙ መልዕክቱን አስተላልፏል።

#AddisAbabaPolice

#Share #ሼር

@tikvahethiopia
#SNNPRS

ከፌደራል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ መምሪያ የሚተላለፉ መመሪያወች እንደተጠበቁ ሆነው÷ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት በክልሉ ውስጥ ተግባራዊ የሚደረጉ የክልከላ መመሪያዎች አውጥቷል፡፡

ክልከላዎቹም ፦

1. በክልሉ ውስጥ ባሉ አካባቢወች ማንኛውም ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ከቀኑ 12፡00 ሰዓት በኋላ እንቅስቃሴ ማድረግ የተከለከለ ነው።

2. ማንኛውም የህዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪ ባለ ሶስት እግርን ጨምሮ ከምሽቱ 2፡00 በኃላ ማንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

3. የምርት ዕንቅስቃሴ እንዳይስተጓጎል የጭነት መኪኖች በየኬላው ጥብቅ ፍተሻ እየተደረገባቸው እንዲንቀሳቀሱ የፈቀድላቸው ሆኖ ከረዳቱና ካሽከርካሪው ውጪ መጫን የተከለከለ ነው።

4. ከፀጥታ አካላት ውጪ ማንኛውም እግረኛ በክልሉ ውስጥ ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት በኋላ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

5. ከጤና ተቋማት፣ከነዳጅ ማደያዎች፤ከፖሊስ ጣብያ ውጪ ማንኛውም አገልግሎት ሰጪ ተቋም ከምሽቱ 3፡00 በኋላ አገልግሎት መስጠት አይችሉም።

6. ማንኛውም ባለ ሁለት እግር ተሸከርካሪ እና አሽከርካሪ የመንግስትን ጨምሮ ከቀን 29/2/2014 ጀምሮ እስከ 3/3/2014 ዓ.ም ድረስ በአቅራብያቸው ባለው የፖሊስ ተቋም ቀርበው መመዝገብ አለባቸው።

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
#Harari

ከፌደራል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ መምሪያ የሚተላለፉ መመሪያዎች እንደተጠበቁ ሆነው÷ የሀረሪ ክልል አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መምሪያ እዝ በክልሉ ውስጥ ከጥቅምት 29 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረጉ የክልከላ መመሪያዎች አውጥቷል።

ክልከላዎቹም ፦

1. ከፀጥታ አካላት ውጪ ማንኛውም እግረኛ በክልሉ ውስጥ ከምሽቱ 4:00 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 11:00 ሰዓት ድረስ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

2. ከአምቡላንስ እና ከጸጥታ አካላት ተሽከርካሪ ውጪ ማንኛውም ተሸከርካሪ ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 11:00 ሰዓት ድረስ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

በዚህ የጊዜ ገደብ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ከባድ ተሽከርካሪዎችና ሀገር አቋራጭ ተሽከርካሪዎች ከከተማው በስተጀርባ ያለውን መንገድ ወይም ባይ ፓስ መጠቀም ይችላሉ።

3. የክልሉ ሰሌዳ የሌላቸው ማናቸውም ታክሲዎች (ባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪናዎች ጨምሮ) ወደ ክልሉ መግባት አይችሉም፤ የክልሉ ሰሌዳ ያላቸው ታክሲዎችም ወደ ሌላ ክልል መውጣት የተከለከለ ነው።

4. ከህክምና ተቋማትና የመድኃኒት ቤቶች በስተቀር ማንኛውም የንግድ ተቋማት ከምሽቱ 4:00 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 11:00 ሰዓት አገልግሎት መስጠት አይችሉም።

#Share #ሼር

@tikvahethiopia
#Amhara

የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን የገና በዓል እና የጥምቀት በዓል በሰላምና ያለምንም የፀጥታ ስጋት እንዲከበር በቂ ዝግጅት ማድረጉን አሳውቋል።

የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን ከሌሎች የፌዴራል እና የክልል የጸጥታ እና የደህንነት አካላት ጋር በጥምረት በመሆን በዓሉ በሰላም ተከብሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ እና የፀጥታ ኃይሉ ስነምግባርን ተላብሶ ተግባራትን እንዲከዉን ዝርዝር ዕቅድ ታቅዶ በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮችና አባላት በቂ ኦረንቴሽን በመስጠት ዝግጅት ተደርጓል።

በተለይ ደግሞ በዓሉ በከፍተኛ ሁኔታ በሚከበርባቸው አካባቢዎች ተንቀሳቃሽ እና ቋሚ ጥበቃ ተመድቧል። በዚህም ህዝቡ በዓሉን ያለምንም የፀጥታ ስጋት ሊያከብር ይገባል ተብሏል።

ህዝቡ ከፀጥታ ኀይሎች ጎን በመሆን በዓላቱ በሰላም እንዲከበር የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ ተገልጿል።

ነዋሪዎች በአማራ ክልል ማንኛውም አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥም በአቅራቢያቸው ለሚገኝ የፀጥታ ኀይል እንዲጠቁሙ መልዕክት ተለልፏል።

(የዞኖች ፣ የብሄረሰብ አስተዳደሮች እና ከተሞች የፖሊስ ስልክ ከላይ ተያይዟል - በምትኖሩበት አካባቢ ሁሌም የፀጥታ ኃይሎችን ስልክ ቁጥር መመዝገብ እንዳትዘነጉ)

እባክዎትን ስልክ ቁጥሮቹን #Share #ሼር ያድርጉ !

#AmharaPoliceCommission

@tikvahethiopia
#WANTED #ተፈላጊ

በምስራቅ ጎጃም ዞን በ ' ሁለት እጁ እነሴ ወረዳ ' በቀራንዮ ንዑስ ከተማ ታህሳስ 18 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 አካባቢ የፍቅር ጥያቄ አቅርቦ አለመግባባት በመፈጠሩ ምክንያት ተጠርጣሪው አቶ ይኸነው ፈንታ ይሁኔ የተባለ ግለሰብ የፍቅር ጥያቄ ባቀረበላት ወጣት ፊት እና ሌሎች የሰውነት ክፍሏ ላይ አሲድ በመድፋት ከፍተኛ አካላዊ ጉዳት በማድረስ ከአካባቢው ተሰውሯል፡፡

የወረዳው ፖሊስም ወንጀሉ ከተፈፀመበት ሰዓት ጀምሮ ተጠረጣሪ ወንጀለኛውን ለመያዝ ክትትል እያደረገ የሚገኝ ቢሆንም አሁንም በቁጥጥር ሥር አልዋለም።

ስለሆነም ተጠረጣሪ ግልሰቡ ያለበትን አካባቢ ለፖሊስ ትብብርና ጥቆማ በመስጠት በህግ ቁጥጥር ሥር እንዲውል ህዝቡ እገዛ እንዲያደርግ ጥብቅ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

ስልክ ቁጥር ፡ 058 661 02 01

" ወንጀል ሠርቶ ከተጠያቂነት ማምለጥ አይቻልም "

( በምስራቅ ጎጃም ዞን የሁለት እጁ እነሴ ወረዳ ፖሊሲ ጽህፈት ቤት )

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
#ተወዳደሩ #GenerationUnlimitedEthiopia

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የጀነሬሽን አንሊሚትድ መፍትሔ አምጪ የሥራ ሃሳቦችን ማወዳደር ጀምሯል።

ሚኒስቴሩ የወጣቶችን የሥራ ፈጠራ ሃሳቦች ለማበረታታት ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ጋር የሚያከናውነው የ 2014 ዓ.ም የጀነሬሽን አንሊሚትድ ለውጥ አምጪ የወጣቶች ውድድር ይፋ ሆኗል።

የዚህ ውድድር ተልዕኮ በዓለም አቀፍ ደረጃ 1.8 ቢሊዮን ወጣቶችን ከተለያዩ ዕድሎች ጋር ማገናኘት መሆኑ ተገልጿል።

አቶ ጥዑመዝጊ በርሔ በሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የአጋርነት እና ፈንድ ዳይሬክተር ፥ " ወጣቶችን የማገናኘት እና አቅማቸውን የማሳደግ እንቅስቃሴ በቀድሞ ሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን ተጀምረው በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከቀጠሉት አንዱ ሆኖ ይህ ዓለማቀፍ መሆኑ ይለየዋል " ብለዋል።

አክለውም ፤ " 35 በሚጠጉ አገራት መካከል የሚካሄድ፣ በአገራችን 5 ከተሞች ተከናውኖ በ 8 ሳምንታት የሚጠናቀቅ ፣ ሁለት ተወዳዳሪ ቡድኖችን ለዓለማቀፍ ውድድር የሚያዘጋጅ፣ ለአገራችን ወጣቶች ትልቅ መነቃቃት የሚፈጥር መሆኑን ገልፀው ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች ዕድሉን ይጠቀሙበት " ሲል መልዕክት አስተላልፈዋል።

የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) ተወካይ ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች ልዩ ሃሳቦቻቸውን አዳብረው የማኅበረሰባቸውን ችግር በመፍታት ተፅዕኖ ማሳደር እንዲችሉ ድጋፍ በማድረጋችን ኩራት ይሰማናል ብለዋል።

ውድድሩ ኢትዮጵያዊ ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች ዘላቂ የልማት ግቦችን ስኬት ለማፋጠን የሚቀርቡ የፈጠራ ሃሳቦች ላይ አትኩሮ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ ሃሳባቸውን ተግባራዊ ለማድረግ መነሻ ገንዘብ ይመድባል።

የውድድር የማመልከቻ መቀበያው ጥር 17 ቀን 2014 ዓ.ም ሆኖ የካቲት 1 ቀን 2014 ዓ.ም ይጠናቀቅና ውድድሩ ይቀጥላል።

ይህንን ውድድር የተለያዩ ዓለማቀፍ ተቋማት የደገፉት ሲሆን ሥራው በፈርስት ኮንሰልት አማካኝነት ይከናወናል።

በኦላይን ለመመዝገብ 👉 https://bit.ly/3rQOERQ

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
#Share #ሼር

ለጠቅላላ ሀኪሞች የወጣ የኮንትራት ቅጥር ፦

የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ በዞን ጤና መምሪያ እና በልዩ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት ክፍት የስራ መደብ ላይ ተፈላጊውን ችሎታ የሚያሟሉ ሀኪሞችን በኮንትራት ቅጥር አወዳድሮ መመደብ እንደሚፈልግ አሳውቋል።

👉 የስራው መደቡ መጠሪያ - ጠቅላላ ሀኪም
👉 የሙያ መስመር /ተፈላጊ ችሎታ - በጠቅላላ ህክምና በዲግሪ የተመረቀ/ች
👉 የስራ ልምድ- #ዜሮ_ዓመት
👉 ብዛት - 379 (#ሶስት_መቶ_ሰባ_ዘጠኝ )
👉 ደመወዝ - 9,056
👉 የስራ ቦታ - በእጣ ነው የሚለየው

ማሳሰቢያ ፦

1ኛ. በደቡብ ክልል ጤና ቢሮ በሚመደብበት በማንኛውም ዞን / ልዩ ወረዳ ሄደው ለመስራት ፍቃደኛ የሆነ /የሆነች።

2ኛ. በዕጣ ከጤና ቢሮ ለዞን/ልዩ ወረዳ ሲመደቡ ዞን/ልዩ ወረዳ በሚሰጠው በማንኛውም ጤና ተቋማ /ምደባ / ቦታ ሄደው ለመስራት ፍቃደኛ የሆነ/የሆነች።

3ኛ. በማንኛውም የመንግስት ተቋም ውስጥ ያልተቀጠረ /ያልተቀጠረች

የመመዝግቢያ ጊዜ ፦ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት። (ከተሰጠው ቀን ውጭ የሚመጣ አይስተናገድም)

የመመዝገቢያ ቦታ ፡ በደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ሰው ሀብት አስተዳደርና ልማት ዳይሬክቶሬት በአካል በመቅረብ ሲሆን ኦርጂናል የትምህርት እና የሙያ ፍቃድ ማስረጃ ከማይመለስ ፎቶ ኮፒ ጋር መያዝ እንዳትዘነጉ።

የፈተናው ቀን : በቀጣይ ይገለፃል።

@tikvahethiopia
አስተያየት ስጡበት !

የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን የዕጩ ኮሚሽነሮች ላይ ህዝቡ አስተያየት እንዲሰጥባቸው ምክር ቤቱ ዝርዝራቸውን ዛሬ ይፋ አድርጓል።

በተለያዩ አግባቦች በተጠቆሙት 42 የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን እጩ ኮሚሽነሮች ላይ ከዛሬ ጀምሮ የህዝብ አስተያየት ይሰበሰባል።

ይህን 👉http://www.hopr.gov.et/am/web/guest/dialog-candidate ማስፈንጠሪያ በመጫን አስተያየት መስጠት እንደሚቻል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሳውቋል።

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
#AmharaRegion

የጠቅላላ ሀኪም የቋሚ ቅጥር ፦

የአማራ ክልል ጤና ቢሮ በክልሉ ስር ባሉ ጤና ተቋማት ጠቅላላ ሀኪሞችን መድቦ ማሰራት ይፈልጋል።

👉 የስራ መደቡ መጠሪያ - ጠቅላላ ሀኪም
👉 ደመወዝ - 9,056 ብር (ዘጠኝ ሺ ሃምሳ ስድስት ብር)
👉 ብዛት - 631 (#ስድስት_መቶ_ሰላሳ_አንድ)
👉 የስራ ቦታ - በክልሉ ባሉ የጤና ተቋማት ክፍት ቦታዎች
👉 ተፈላጊ የትምህርት ዝግጅት - በጠቅላላ ሀኪም የመጀመሪያ ዲግሪ እና 0 (#ዜሮ) ዓመት የስራ ልምድ
👉 የሞያ ፍቃድ ያለው / ያላት

የመመዝገቢያ ቦታ በአብክመ ጤና ቢሮ እና በሁሉም ዞን ጤና መምሪያዎች ማስረጃዎቻችሁን ዋናውንና የማይመለስ ኮፒ በመያዝ መመዝገብ ትችላላችሁ ተብሏል።

የዞን ጤና መምሪያዎች ምዝገባው ከተጠናቀቀበት ቀን ጀምሮ ባሉት 3 ተከታታይ ቀናት ውስጥ በሶፍት ኮፒ እና በሃርድ ኮፒ እንዲልኩ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

ማሳሰቢያ ፦

1ኛ. በማንኛውም ጤና ተቋም ዕጣ በደረሰው ቦታ ላይ ለመስራት ፍቃደኛ የሆነ/የሆነች
2ኛ. ከዚህ በፊት በመንግስት ጤና ተቋም በቋሚ ቅጥር ያልተቀጠረ/ያልተቀጠረች

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
የግል_ከፍተኛ_ትምህርት_ተቋማትና_እውቅና_ፈቃድ_የተሰጣቸው_የትምህርት_መስኮች.pdf
6 MB
#ETA

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን እስከ የካቲት 2014 ዓ.ም ድረስ ያጠናቀራቸውን አጠቃላይ የ350 ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን እና የትምህርት መስኮቻቸውን የእውቅና ፈቃድ የሚገልጽ የተሟላ መረጃ ይፋ አድርጓል፡፡

ከ350ው 330ዎቹ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሲሆኑ 20 ተቋማት በርቀት ትምህርት እውቅና የተሰጣቸው የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና በክልል መንግስታት የሚተዳደሩ ተቋማት ይገኙበታል።

የእውቅና ፈቃድ ባልታደሰባቸው የትምህርት መስኮች #አዲስ_ተማሪ_መቀበል_እንዳይችሉ ተደርጎ የተዘጋጀ ነው፡፡

ይፋ የተደረገው መረጃ እስከ የካቲት ወር ድረስ ያለውን የእውቅና ፈቃድ መሆኑን ባለስልጣኑ ገልጿል።

በሂደት ላይ ያሉ የእውቅና ፈቃድ እና የእውቅና ፈቃድ እድሳት ጥያቄዎች ውሳኔ ሲያገኙ እንዲሁም በተለያዩ ምክንያቶች የእውቅና ፈቃድ ሲሰረዝና በሌሎች ምክንያቶች የውሳኔ ለውጦች በሚኖሩበት ወቅት የመረጃ ለውጥ ሊኖር እንደሚችል አሳውቋል።

በመሆኑም ፦
- ተማሪዎች፣
- ወላጆች፣
- ቀጣሪና የሙያ ፈቃድ የሚሰጡ ድርጅቶች ፣
- የሚዲያና ማስታወቂያ ተቋማት ፣ እንዲሁም መላው ህብረተሰብ የተቋማቱን ወቅታዊ መረጃ በመከታተል ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ባለሥልጣኑ በጥብቅ አሳስቧል።

ተቋማት ይፋ ከተደረገው የእውቅና ፈቃድ መረጃ ውጪ ተማሪ ተቀብለው ቢያስተምሩ ህጋዊ እና አስተዳደራዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ባለስልጣኑ አሳውቋል፡፡

ይፋ በተደረገው መረጃ የማስተካከያ ጥቆማ የሚኖራቸው ተቋማት በህጋዊ ተወካዮቻቸው በኩል ለባለስልጣኑ ማሳወቅ የሚችሉ መሆኑ ተገልጿል።

[ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና እውቅና ፈቃድ የተሰጣቸው የትምህርት መስኮች ከላይ በ #PDF ተያይዟል ]

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
#መልዕክት

ከሰዓታት በኃላ 2ኛው " የታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር በኢትዮጵያ " መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

ለታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር 2 ለመታደም ሲመጡ ፦

👉 የራሳችሁን መስገጃ ይዛችሁ ኑ።

👉 አዘጋጆች የሚዘጋጁት ምግብ ቢኖርም ሁሉም የቻለውን ያህል ለሰዎች ጭምር የሚሆን ምግብ ይዞ ይምጣ።

👉 ሁሉም የተመገበበትን እቃ የሚያነሳበትን ፌስታል መያዝ እንዳይዘነጋ።

👉 በመሃል ሌባ ሊኖር ስለሚችል ከፍተኛ ጥንቃቄ ይደረግ።

👉 አቅመ ዳካማዎችን፣ታላላቆችንና ሴቶች የተሻለ ቦታ እንዲያገኙ አድርጉ።

👉 ለአስተናጋጆች፣ ለኻዲሞችና ለፀጥታ አካላት ፍፁም ታዛዥ ይሁኑ።

👉 በጦርነትና በድርቅ የተጎዱ ወገኖችን ለማገዝ ለሚንቀሳቀሱ አስተባባሪዎች ድጋፍ ያድርጉ።

👉 እርስ በእርስ በመከባበር እና በመተዛዘን እጅግ የሰለጠነና ምስኪኖችን ታሳቢ ያደረገ ኢፍጣር እንዲሆን ሁላችንም ባለቤቶች እንደሆንን በማሰብ ተግባራዊ ያድርጉ።

📞 ማንኛውም አይነት አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ በቦታው ለሚገኙ የፀጥታ አካላትና አስተባባሪዎች ወይም በፖሊስ የመረጃ ስልኮች 0111110111 እና ነፃ የስልክ መስመር 991 ላይ በመደወልና መረጃ በመስጠት ይተባበሩ።

(ከአዘጋጆች)

መልካም የኢፍጣር ስነስርዓት !

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
#ጥንቃቄ

በህገወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ሦስት መድኃኒቶችን ህብረተሰቡ እናዳይጠቀም ማሳሰቢያ ተላልፏል።

በህገወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ጥራታቸው፣ ደህንነታቸውና ፈዋሽነታቸው ያልተረጋገጠ እና በጤና ላይ ከቀላል እስከ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርሱ የሚችሉ ፦

👉 Titan gel፣
👉 Mara Moja
👉 Relief የተባሉ መድኃኒቶችን ህብረተሰቡ እንዳይጠቀም የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን አሳስቧል።

መድኃኒቶቹ በኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ያልተመዘገቡና በህጋዊ መንገድም ወደ አገር ዉስጥ ያልገቡ ናቸው።

Titan gel የተባለው መድኃኒት በሐኪም ብቻ በመታዘዝ ጥቅም ላይ መዋል ያለበት ሲሆን ነገር ግን በድብቅና በህገወጥ መንገድ ገበያ ላይ አንደሚገኝ ታውቋቃ።

መድኃኒቶቹን ማንኛውም ግለሰብ ወይም አካል በህጋዊ ተቋማት ሆነ በህገወጥ መንገድ ሲያገኛቸው እንዳይጠቀማቸውና በባለስልጣን መስሪያቤቱ ነጻ የስልክ መስመር 8482 በአቅሪያባቸው ለሚገኙ የክልል ተቆጣጠሪዎች ወይም ለጸጥታ አካላት በመጠቆም አስፈላጊዉን ትብብር እንዲያደርግ ተጠይቋል።

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ዛሬ በአዲስ አበባ ሀርመኒ ሆቴል ለዓለም ዓቀፉ የቁርዓን ውድድር ማጣሪያ ሲካሄድ ውሏል። የፊታችን እሁድ በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ ዓለም አቀፍ የቁርኣን ሂፍዝ ውድድር እንደሚካሄድ ይታወቃል። በዚህ ልዩ ውድድር ላይ ከተለያዩ የአለም ክፍሎች የመጡ ተወዳዳሪዎች መካከል ዛሬ የማጣሪያ ውድድሩ እየተካሄደ ሲሆን ውድድሩ በዓለም ዓቀፍ ዳኞች የተመራ ነበር። በእሁዱ ውድድር የሶማሌ ክልሉ ተወላጅ…
#እጅግ_በጣም_አስቸኳይ

በነገው ዕለት የዓለምዓቀፍ የቁርዓን ሂፍዝ ውድድር መዝጊያ ፕሮግራም በስታድየም ይደረጋል ተብሎ የተገለጸ መሆኑ ይታወቃል።

ይሁንና አንዳንድ ዶክመንቶች በጊዜ ባለማሟላታቸው እንዲሁም አዲስ አበባ ስታዲየም በእድሳት ምክንያት የተቆፋፈረና ምቹ ባለመሆኑ የመዝጊያው ፕሮግራም ከስታዲየም ውጪ እንዲደረግ ተወስኗል።

ስለዚህም ህዝቡን ይቅርታ እየጠየቅን ከዚህ ጋር የተያያዙ ዝርዝር ጉዳዮችን በቀጣይ ጊዜያት የምናሳውቅ ይሆናል።

ማሳሰቢያ ፦ ከሀገሪቱ ጫፍ እስከ ጫፍ ወደ አዲስ አበባ እየመጣችሁ ያላችሁ እንግዶች እና የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ይህንን በመገንዘብ ሳትለፉ ባላችሁበት እንድትከታታሉ እንጠይቃለን።

(አዘጋጅ ፦ ዘይድ እብን ሳቢት የቁርዓን ማህበር)

የነገውን ፕሮግራም ተካፋይ ለመሆን ስትጠብቁ የነበራችሁ ውድ ቤተሰቦቻችን የአዘጋጆቹን መልዕክት ያልሰሙ ካሉ #ሼር አድርጓቸው / ላኩላቸው።

@tikvahethiopia