TIKVAH-ETHIOPIA
1.41M subscribers
55K photos
1.37K videos
199 files
3.67K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
FXD012024-FOREIGN-EXCHANGE-1-1.pdf
22.8 MB
NATIONAL BANK OF ETHIOPIA FOREIGN EXCHANGE DIRECTIVE NO. FXD/01/2024

በዚህ መመሪያ መሰረት የውጭ ምንዛሪ ማግኘት የሚችሉት እነማን ናቸው ?

➡️ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት የተፈቀደላቸው የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ከኢትዮጵያ ውጭ የሚጓዙ ኢትዮጵያዊውያን ወይም በአገሪቱ ውስጥ የሚኖር የውጭ ዜጎች ናቸው።

➡️ ምንዛሪ ለማግኘት የሚፈልጉ ግለሰቦች ለበዓል ፣ ለትምህርት ፣ ለህክምና ጉዞዎች እና ሌሎች የግል ጉዳዮች እንደሚጓዙ የሚያሳይ ፓስፖርት፣ ሕጋዊ የመግቢያ ቪዛ እና የአየር ትኬት የማቅረብ ግዴታ ተጥሎባቸዋል።

➡️ ተጓዦች ከምንዛሪ ቢሮዎች እስከ 5 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ወይም የዚህ አቻ የሆነ የሌላ አገር ገንዘብ በጥሬ ወይም በክፍያ መፈጸሚያ ካርድ (debit card) አማካኝነት ማግኘት ይችላሉ።

➡️ የውጭ ምንዛሪ የባንክ ሂሳብ ያላቸው ተጓዦች እስከ 10 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ድረስ ማግኘት ተፈቅዶላቸዋል።

በብሔራዊ ባንክ ካልተፈቀደ በስተቀር ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ነዋሪ በአንድ ጉዞ ላይ ከ10,000 የአሜሪካን ዶላር ወይም ተመጣጣኝ ገንዘብ በካሽ መያዝ አይችልም።

➡️ ለንግድ የሚጓዙ ግለሰቦችም የውጭ ምንዛሪ ማግኘት ይችላሉ።

➡️ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ፣ ፓስፖርት እና የአየር ትኬት ለሚያቀርቡ ለንግድ ድርጅት ተወካዮች የውጭ ምንዛሪ መሸጥ እንዲችሉ ተፈቅዷል። እነዚሁ ቢሮዎች ፦
- ለንግድ ድርጅቶች፣
- ለበጎ አድራጎት ተቋማት
- ለሃይማኖት ማኅበራት፣
- ለንግድ ትርኢቶች፣
- ለቱሪዝም
- ለባህል እና ለስፖርቶች አዘጋጆች የውጭ ምንዛሪ መሸጥ ይችላሉ።

➡️ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ለመንግሥት ተጓዦች ለምግብ፣ ለማረፊያ እና ሌሎች ተያያዥ ወጪዎች ከ10 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ወይም ተመጣጣኝ ገንዘብ የማይበልጥ የውጭ ምንዛሬ ሊሸጡ ይችላሉ።

➡️ ነዋሪ ላልሆኑ የውጭ አገር ዜጎች እና ቱሪስቶች ብርን ወደ ውጭ ምንዛሬ ሊለውጡ የሚችሉበት አሠራርም አለ። ፓስፖርት፣ ትክክለኛ ቪዛ እና የአየር ትኬት የሚያቀርቡ ሰዎች ያለማስረጃ እስከ 500 የአሜሪካን ዶላር መለወጥ ይችላሉ። ከ500 ዶላር በላይ መለወጥ የሚፈልጉ ከሆነ ፓስፖርት፣ ሕጋዊ ቪዛ፣ የአየር ትኬት እና ተመጣጣኝ የሆነው የውጭ ምንዛሪ በሕጋዊ መንገድ ወደ አገር ውስጥ ገንዘብ መቀየሩን የሚያሳይ የተረጋገጠ የባንክ ማስረጃ ማቅርብ ይጠበቅባቸዋል።

ተጨማሪ ከላይ ተያያዘውን ፋይል ከፍተው ያንብቡ !

#NBE #BBC #Ethiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Ethiopia

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቀደም ሲል በ38 የገቢ ንግድ ሸቀጦች ላይ ተጥሎ የነበረው እግድ መነሳቱን በዛሬው ዕለት አሳውቋል።

ወደ ውጭ የሚደረግ የካፒታል ሂሳብ ፍስት እንደ በፊቱ የተገደበ እንደሆነ የውጭ ምንዛሪ ገበያው ለገቢ ሸቀጦችና አገልግሎቶች ነጻ መሆኑንም ገልጿል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዚህ ቀደም " ቅድሚያ የማይሰጣቸው " ተብለው የተለዩ 38 ዓይነት ምርቶች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ እግድ ጥሎ የነበረው የህገወጥ የምንዛሬ ገበያውን ይበልጥ ለማውረድ በማሰብ እንደነበር መገለጹ የሚዘነጋ አይደለም።

በወቅቱ 2014 ዓ/ም ላይ የአንድ የአሜሪካ ዶላር በባንክ ምንዛሬ 50 ብር ነበር ፤ አሁን ከ76 ብር ተሻግሯል።

አሁን እገዳው ተነስቶላቸዋል ከተባሉት 38ቱ የገቢ ንግድ ሸቀጦች ውስጥ ፦
➡️ የተገጣጠሙ የቤት አውቶሞቢሎች እና ባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎች (የነዳጅ)
➡️ የተገጣጠሙ የሞተር ሳይክሎች
➡️ አርቴፊሻል ጌጣጌጦች
➡️ የታሸጉ ምግቦች
➡️ የተለያዩ የጸጉር ጌጣጌጦች
➡️ ከሴራሚክ እና ፖርስሊን የተዘጋጁ የቤት እቃዎች
➡️ የውበት ወይም የመኳካያ ዝግጅቶች
➡️ ሽቶዎች
➡️ የቤት እና የቢሮ እቃዎች ይገኙበታል።

(ወደ ሀገር እንዳይገቡ እግድ ተጥሎባቸው የነበሩ የገቢ ንግድ ሸቀጦችን ዝርዝር ከላይ ይመልከቱ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ውሎ ማደር፣ ወጥቶ መግባት በአንዳንድ የሀገራችን አካባቢዎች ስጋት ከሆነ ሰነባብቷል ! " - ቋሚ ሲኖዶስ ቋሚ ሲኖዶስ ፥ ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት የምሕላ ጸሎት እንዲፈጸም አወጀ። በሀገር አስተማማኝ ሰላም ሲጠፋ በጾም በጸሎት በመወሰን ፣ ምሕላ ይታወጃል። ምሕላ የሚታወጀው ልባዊ በሆነ ተማሕጽኖ ሁሉን ማድረግ…
🔈#ማስታወሻ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ

" ሁሉም የቤተክርስቲያናችን አገልጋዮችና ምእመናን ሀገራዊ ፦
- ሰላምን፣ 
- መረጋጋትን
- ፍቅርን
- አንድነትን ለማስፈን ጾም እና ጸሎት በታወጀበት የምሕላ ሳምንት ለገዳማውያኑ ፀጥታ ሲባል ወደ ገዳማት የምታደርጉትን ጉዞ ለጊዜው እንዲቆይ አድርጋችሁ መደበኛ ሥራችሁን በያላችሁበት ቦታ እየሠራችሁ እግዚአብሔር የገዳማውያኑን ጸሎት ሰምቶ ለሀገራችንና ለሕዝባችን ምሕረትን እንዲሰጥ በኅሊና ዝግጅት፣ በሐሳብ አንድነት ሆናችሁ በጾም በጸሎት እንድተጉ ቋሚ ሲኖዶስ መንፈሳዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ "


ቋሚ ሲኖዶስ ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት የምሕላ ጸሎት እንዲፈጸም ማወጁ አይዘነጋም።

#ኢትዮጵያ🙏

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#IMF : የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ሥራ አስፈፃሚ ቦርድ ኢትዮጵያ በጠየቀችው ብድር ላይ ለመወያየት ነገ ሰኞ ሐምሌ 22 / 2016 ይሰበሰባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ብሎምበርግ ድረገጽ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የመረጃ ምንጮችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና ከዓለም ባንክ ጋር የምታደርገው ድርድር ከተሳካ በቀጣይ አመታት 10.5 ቢሊዮን ዶላር ልታገኝ እንደምትችል…
#Update

የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) አስፈጻሚ ቦርድ ለኢትዮጵያ የሚሆንና መጠኑ 2.556 ቢሊዮን SDR (የኮታው 850% ወይም ወደ 3.4 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ) የሆነ የ4 ዓመት የተራዘመ የብድር አገልግሎት አቅርቦት ዛሬ አጽድቋል።

ይህ የ4 ዓመት ፓኬጅ፦
- የማክሮ ኢኮኖሚ ሚዛን መፋለስን መፍታትን
- በግል ዘርፉ ለሚመራ እድገት መሠረት መጣልን
- የመንግሥትን የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ አፈጻጸምን የሚደግፍ ነው ተብሏል።

ውሳኔው ኢትዮጵያ ከባላንስ ኦፍ ፓይመንት ጋር የተያያዙ ፍላጎቶቿን እንድታሟላ ይረዳታት ተብሏል።

በተጨማሪ በጀቷን የሚደግፈውን የ766.75 ሚሊዮን SDR ወይም 1 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር አካባቢ የሚሆን ገንዘብ ክፍያ ወዲያውኑ እንዲለቀቅ የሚያስችል እንደሆነ ተጠቁሟል።

(ዝርዝር መረጃ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የIMF የፕሬስ መግለጫ ፦ የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ቦርድ ለኢትዮጵያ የ2.556 ቢሊዮን SDR ወይም ወደ 3.4 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ የተራዘመ የብድር አገልግሎት አቅርቦትን አጽድቋል። ይህም ውሳኔ 766.75 ሚሊዮን SDR ወይም 1 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር አካባቢ የሚሆን ገንዘብ ክፍያ ወዲያውኑ እንዲለቀቅ የሚያስችል ይሆናል።

@TIKVAHETHIOPIA
#አቢሲንያ_ባንክ

ኤቲኤም ካርድ ያዝኩ አልያዝኩ ብሎ ሐሳብ ቀረ!

የአቢሲንያ ዲጂታል ቪዛ ካርድዎን በመጠቀም ስልክዎን በማስጠጋት ፖስ ላይ ክፍያ መፈጸም እንዲሁም ከአቢሲንያ ኤቲኤም ገንዘብ ማውጣት ይችላሉ።
ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ! https://t.me/BoAEth

አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!

#Apollodigitalbank #Apollodigitalproduct #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
Hey Mobile !

•Playstaion 5 Slim, 76,000 Birr

•PlayStation 4 Slim, 35,000 Birr
•PlayStation 4 Pro, 42,000 Birr

•Meta Quest 2, 45,000 Birr
•Meta Quest 3, 78,000 Birr

Contact
0953964175 @heymobile
0925927457 @eBRO4

@heyonlinemarket
#AddisAbaba

ዛሬ ንጋት 11 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ሰፈራ አካባቢ በደረሰ  የትራፊክ አደጋ 3 ሰዎች መሞታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ፣ ከሟቾች በተጨማሪ 4 ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።

አደጋው የደረሰው 7 ሰዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ  አንድ ደብል ፒካአፕ ተሽከርካሪ ከቆመ ከባድ ተሽከርካሪ ጋር ተጋጭቶ መሆኑን አስረድተዋል።

የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎችን ከተሽከርካሪው በማውጣት ወደ ህክምና ተቋም እንደላኩ ያወሱት አቶ ንጋቱ ፣ ህይወታቸው ያጡትን ሰዎች አስከሬን ለፖሊስ እንዳስረከቡ፣ ዝርዝር የአደጋ ምክንያት ደግሞ በፖሊስ እየተጣራ እንደሆነ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል፣ ትላንት ምሽት 4 ሰዓት ከ43 ደቂቃ ላይ በን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ወረዳ 10 አደይ አበባ አካባቢ በሚገኝ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ላይ እስት አደጋ እንደደረሰ ተናግረዋል።

➡️ አደጋው የደረሰበት ፋብሪካ ፦ DN የጨረቃ ጨርቅ ፋብሪካ
➡️ ሰው ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።
➡️ በመጋዘን ውስጥ የነበረ የጥጥ ክምችት ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል።
➡️ የእሳት አደጋው ወደ ፋብሪካው ማሽነሪዎችና ሌሎች ጨርቃ ጨርቆች ላይ ተዛምቶ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ እሳቱን መቆጣጠር ተችሏል።
➡️ አደጋውን ለመቆጣጠር 3 ሰዓት ከ10 ደቂቃ ፈጅቷል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በሲዳማ ክልል በወንሾ ወረዳ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ የሞቱ ወገኖቻችን ቁጥር 9 ደርሷል። 6 ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በይርጋለም ሆስፒታል ይገኛሉ። በሌላ በኩል ፤ በዛው ሲዳማ ክልል በቡራ ወረዳ በድንገተኛ ውኃ ሙላት የሁለት ሕጻናት ሕይወት አልፏል። #ኤፍቢሲ @tikvahethiopia
#Sidama

በሲዳማ ክልል፣ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት እና የውሀ ሙላት አደጋ የሞቱ ዜጎች 11 መሆኑን የሲዳማ ክልል አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አበራ ዊላ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ከዚህ ውስጥ ዘጠኙ የሁለት አባወራ ቤተሰቦች ሲሆኑ አንዱ 5 አንዱ ደግሞ 3 ቤተሰቦቻቸዉን ማጣታቸውን ገልጸዋል።

አንድ ግለሰብ ከገበያ ሲመለስ ከተራራ የወረደ ናዳ ላዩ ላይ በማረፉ ለህልፈት እንደዳረገው ገልጸዋል።

ከዚህም በተጨማሪ ደግሞ በቡራ ወረዳ ወንዝ ሞልቶ ከአቅጣጫው ውጭ በመፍሰስ በአካባቢዉ ያለ ቤት ውስጥ በመግባት 2 ልጆችን ህይወት መቅጠፉን ተናግረዋል።


ከአካባቢው ተራራማነትና ያለማቋረጥ ከዘነበው ዝናብ ጋር ተያይዞ አሁን ላይ ተጨማሪ አደጋዎች ይከሰታሉ ተብሎ ስጋት አለ።

ይህንንም ተከትሎ ከክልሉ የጸጥታ ቢሮ ፣ የጤና ቢሮና ሌሎች ተቋማት የተወጣጣ ግብረሀይል ተቋቁሞ ወደስራ ተገብቷል ብለዋል።

" ስጋት ያለባቸው አካባቢዎች ናቸው " ተብለው ከተለዩ ስድስት ወረዳዎች የሚኖሩ ዜጎችን የማውጣት ስራ መጀመሩን ጠቁመዋል።

ከቀያቸዉ ከተነሱትን ራቅ ያለ ቦታ ዘመድ ያለው ወደዛ ሲሄድ ሌሎች በት/ቤቶች ፣ በቤተእምነቶችና መሰል ቦታዎች እየተጠለሉ መሆኑን ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የዛሬው የምንዛሬ ዋጋ ስንት ነው ? 💵 US Dollar #CASH Buying ➡️ 74.7364 Selling ➡️ 76.2311 #TRANSACTION Buying ➡️ 74.7364 Selling ➡️ 76.2311 💷 Pound Sterling #CASH Buying ➡️ 91.8787 Selling ➡️ 93.7162 #TRANSACTION Buying ➡️ 96.2081 Selling ➡️ 98.1322 💶 Euro #CASH…
#ዕለታዊ

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዛሬው የምንዛሬ ዋጋ ስንት ነው ?

💵 US Dollar
#CASH
Buying ➡️ 74.7364
Selling ➡️ 76.2311

#TRANSACTION
Buying ➡️ 74.7364
Selling ➡️ 76.2311

💷 Pound Sterling
#CASH
Buying ➡️ 91.5537
Selling ➡️ 93.3848

#TRANSACTION
Buying ➡️ 96.0811
Selling ➡️ 98.0027

💶 Euro
#CASH
Buying ➡️ 80.8797
Selling ➡️ 82.4973

#TRANSACTION
Buying ➡️ 80.8797
Selling ➡️ 82.4973

ተጨማሪ ከላይ ይመልከቱ።

@tikvahethiopia
ግብር ለመክፈል መጉላላት ሳይጠበቅብዎ በቴሌብር ሱፐርአፕ onelink.to/fpgu4m ወይም *127# ባሉበት ቦታ ሆነው በስልክዎ ይክፈሉ!

ሁለቱን የከተማ መስተዳድሮች ጨምሮ የአብዛኛዎቹ የክልል ገቢዎች ግብር በቴሌብር መክፈል ተችሏል፡፡

ሥራን በክብር
ግብርዎን በቴሌብር !

ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ !

ለማንኛውም ጥያቄ ወይም አስተያየት በ https://t.me/EthiotelecomChatBot 24/7 ያግኙን!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia