TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.4K photos
1.39K videos
199 files
3.72K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሩዋንዳ ዛሬ የሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ (ጄኖሳይድ) 30ኛ ዓመት መታሰቢያ ነው። በ1994 እ.አ.አ ሩዋንዳ ውስጥ በቱትሲ ጎሣ ላይ የደረሰው የዘር ማጥፋት ዘመቻ በሰው ልጆች ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ከደረሱት አሰቃቂ የዘር ጭፍጨፋዎች አንዱ ነው። በ100 ቀናት ገደማ ውስጥ ብቻ ከ800,000 እስከ 1,000,000 የሚሆኑ ሰዎች እንዳለቁ ይገመታል። ከተገደሉት ሰዎች መካከል አብዛኞቹ ቱትሲዎች ናቸው፤ ሆኖም…
በሩዋንዳው #ጄኖሳይድ ወቅት የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ምን አደረገ ?

ከ800 ሺህ እስከ 1 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች ባለቁበት የሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ ወቅት የዓለም መሪዎች ምንም እንኳን ስለ ዘር ጭፍጨፋው (ጄኖሳይድ) ቢያውቁም ጣልቃ አልገቡም ነበር።

ለረጅም ጊዜ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ' ጄኖሳይድ ' የሚለውን ቃል ከመጠቀም ተቆጥቦ ነበር ፤ ይህም #በአሜሪካ ጫና እንደሆነ ይነገራል።

አሜሪካም ወታደሮቿን ወደ ሩዋንዳ ለመላክ ያልፈለገች ሀገር ናት።

የቀድሞ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ሃላፊ ባን ኪሙን በ20ኛው ዓመት የዘር ጭፍጨፋው መታሰቢያ ወቅት " ድርጅቱ የዘር ማጥፋት ወንጀሉ  መከላከል ባለመቻሉ አሁንም ድረስ ያፍራል " ሲሉ ተናግረው ነበር።

ጭፍጨፋው ከመጀመሩ በፊት (እኤአ በ1994 መጀመሪያ ላይ) ተመድ ወደ ሩዋንዳ የላከው ኃይል UNAMIR አዛዥ ጄኔራል ሮሜዮ ዳላይር ስለ ግድያው / ጭፍጨፋው በቂ የደህንነት መረጃ ደርሶት ነበር። በሁቱዎቹ የተከማቸ ሚስጥራዊ የጦር መሳሪያ (እንደ ገጀራዎች) እንዳለ አውቆ ነበር። 

ከጥር እስከ መጋቢት ወር ድረስ 5 መልዕክቶችን ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ልከዋል።

በዚህም በሩዋንዳ ያላቸው ተልእኳቸው እንዲሰፋ ሁቱዎች ያከማቿቸው መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ እና የተመድ የሰራዊት ቁጥር እንዲጨምር ቢጠይቁም እዛ ያሉት ሰዎች ግን ማስጠንቀቂያዎቹን ችለ ብለው ትተዋቸዋል።

ግድያው ሲጀመር ተመድ እና የቤልጂየም መንግሥት የUNAMIR ሰላም አስከባሪዎችን አስወጡ።

የፈረንሳይ እና የቤልጂየም ሰላም አስከባሪዎች ቱትሲዎችን ለመርዳት ፍቃደኛ ሳይሆኑ በመቅረት በተሽከርካሪ የነበሩ የሌላ ሀገር ዜጎችን አስወጥተዋል።

ሳይወጡ የቀሩና ትንሽ የተረፉ የተመድ ኃይሎች በኪጋሊ ውስጥ እንደ " ሆቴል ዴ ሚሌ ኮሊንስ " እና " አማሆሮ ስታዲየም " ባሉ ቦታዎች የተሸሸጉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ጥበቃ አድርገዋል።

በአንድ አጋጣሚ ግን በኪጋሊ ኢኮሌ ቴክኒክ ኦፊሴሌ (የቴክኒክ ት/ቤት) የተጠለሉ 2,000 ሰዎችን የሚጠብቁ ወታደሮች ቦታቸውን የውጭ ዜጎችን ለማስወጣት ሲሉ ቦታቸውን ለወቀው ሲወጡ በትምህርት ቤቱ እልቂት / ጭፍጨፋ ተፈፅሟል።

ቱትሲዎችን ለማጥፋት እቅድ እንዳለው እያወቀች የፕሬዝዳንት ሃብያሪማናን መንግሥት ስታስታጥቅ የከረመችው ፈረንሳይ በግድያዎቹ የመጀመሪያ ቀናት ጭምር ከሁቱ መንግስት ጋር መተባበሯን ቀጥላ ነበር። RPFንም ለፍራንስ አፍሪካ ግንኙነት ጠንቅ ነው ብላ ታስብ ነበር።

በመጨረሻ ተመድ ግንቦት 17/1994 በሩዋንዳ ላይ የጦር መሳሪያ እገዳ ጣለ፣ UNAMIRን ለማጠናከር ውሳኔ አሳለፈ። እስከ ሰኔ ድረስ ግን አዲስ ወታደሮች ሩዋንዳ መግባት አልጀመሩም ነበር።

ይህ ሁሉ እስኪሆን አብዛኛው ግድያ ተፈጽሞ ነበር።

የምዕራቡ ዓለም የሚዲያዎችም ጭፍጨፋውን “ የእርስ በርስ ” ወይም “ የጎሳ ” ጦርነት በማለት ነው ሲገልጹ የቆዩት።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
Rwandan genocide
Apr 7, 1994 – Jul 15, 1994
Al Jazeera

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በሩዋንዳው #ጄኖሳይድ ወቅት የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ምን አደረገ ? ከ800 ሺህ እስከ 1 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች ባለቁበት የሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ ወቅት የዓለም መሪዎች ምንም እንኳን ስለ ዘር ጭፍጨፋው (ጄኖሳይድ) ቢያውቁም ጣልቃ አልገቡም ነበር። ለረጅም ጊዜ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ' ጄኖሳይድ ' የሚለውን ቃል ከመጠቀም ተቆጥቦ ነበር ፤ ይህም #በአሜሪካ ጫና እንደሆነ ይነገራል። አሜሪካም…
ሚዲያ የሩዋንዳውን የዘር ጭፍጨፋ (ጄኖሳይድ) እንዴት አቀጣጠለ ?

በ100 ቀናት ከ800,000 እስከ 1,000,000 ቱትሲዎችና ለዘብተኛ የሚባሉ ሁቱዎች ባለቁበት የሩዋንዳው የዘር ጭፍጨፋ/ጄኖሳይድ ሚዲያዎች ከፍተኛ ድርሻ ነበራቸው።

እንዴት ?

- ራዲዮ-ቴሌቭዥን ሊብሬስ ዴስ ሚልስ ኮሊንስ (RTML) እንዲሁም መንግታዊው ' ሬድዮ ሩዋንዳ ' በቱትሲዎች ላይ በመላ ሀገሪቱ ጥላቻ እንዲፈጠርና የሩዋንዳ ጄኖሳይድ እንዲፈፀም ዋና አቀጣጣይ ነበሩ።

- RTML ሚዲያ በወቅቱ በብዙ ወጣቶች ዘንድ ተደማጭነት የነበረው ነው። ጣቢያው በወጣቶች ዘንድ እጅግ የሚወደዱ ሙዚቃዎችን እያስተላለፈ #በመሃል ያቋርጠውና ቱትሲዎችን በመጥቀስ " እነዚያ ሰዎች እጅግ ቆሻሻ ቡድን ናቸው " የሚሉ አዋራጅና ቀስቃሽ መልዕክቶችን ያስተላልፋል። በስርጭቶቹ ውስጥ "#በረሮዎች" እና "#እባቦች" የሚሉ ቃላት በተደጋጋሚ ጥቅም ላይ ያውላል።

- RTML ሚያዚያ 6 /1994 ፕሬዜዳንት ጁቬናል ሃብያሪማና የነበሩበት አውሮፕላን ተመቶ ሲወድቅ በቅድሚያ ድርጊቱን የፈፀመው RPF ነው ብሎ የፈረጀ እና ንፁሃንን ለጭፍጨፋ ያመቻቸ ሚዲያ ነው።

- በጭፍጨፋው ወቅት ጨፍጫፊዎቹ በአንድ እጃቸው ሬድዮ በአንድ እጃቸው ደግሞ #ቆንጨራ ይዘው ነበር ሲንቀሳቀሱ የነበሩት። በዚህም ወቅት RTML እና ሬድዮ ሩዋንዳ ቱትሲዎች እና እነሱን የሚሸሽጉ ሁቱዎች እንዲገደሉ ያሉበትን አድራሻ ጭምር ሲገልጹ ነበር።

- ሚዲያዎቹ ጎረቤት በጎረቤቱ ላይ እንዲነሳ እና ቱትሲ የሚባሉትን በጠቅላላ እንዲያጠፏቸው ሲሰብኩ ነበር። በዚህም ብዙዎቹ ሁቱዎች የገዛ ጎረቤታቸውን አንዳንዶቹ ከቱትሲ ጋር የተዛመዱ #ዘመዶቻቸውን ጭምር ጨፍጭፈዋል።

- ሚዲያዎቹ የተለያዩ አነሳሽ ቃላቶች በመጠቀም ቱትሲዎች #እንዲጠሉ#እንዲገደሉ ሰዎችን ሲያበረታቱ ነበር። ትንንሽ ልጆች ፣ ታዳጊዎች ሳይቀሩ በራሳቸው ወገን #ጥላቻ እንዲሞሉ አድርገዋል።

- የሁቱ ሚዲያዎች በቀደመው ጊዜ #ቱትሲዎች ሀገሪቱ ውስጥ ትልቅ ስፍራ ይዘው በነበረበት ወቅት " በደል ፈፅመዋል " በማለትና " የሀገሪቱ ችግሮች እነሱናቸው እስከመጨረሻ ካልጠፉ በቀር ምንም መፍትሄ የለም " በማለት ሁቱዎችን ይቀሰቅሱ ነበር።

በነገራችን ላይ ከጭፍጨፋው ጅማሮ #በፊትም የሀገሪቱ መንግሥት ሚዲያዎችን በመጠቀም ሰፊ የሆነ የጥላቻ ፕሮፖጋዳንዳ ሲሰራ ቆይቷል።

በተለይ ቱትሲዎችን ከRPF ኃይል ጋር በማገናኘት ሁቱዎች ውስጣቸው በከፍተኛ ጥላቻ ታውሮ የገዛ ወገናቸውን እንዲጨፈጭፉ ሰርቷል።

አጠቃላይ በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ የታየ እጅግ  አስከፊው የዘር ጭፍጨፋ የአንድ ሌሊት ውጤት አልነበረም፤ በሂደት የመጣ እንጂ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
Rwandan genocide
Apr 7, 1994 – Jul 15, 1994

@tikvahethiopia
ገንዘባችንን ከየትኛውም ባንክ ወደ M-PESA ፤ ከM-PESA ወደ የትኛውም ባንክ በመላክ ቀላል እና የተቀላጠፈ ክፍያ እንፈጽም!

M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ!

🔗 የM-PESA ሳፋሪኮምን መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፡ https://bit.ly/M-PESA_SafaricomEthiopia

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://t.me/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom #TerekBeMPESA #FurtherAheadTogether
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቅሬታ “ እኔ 1.5 ሚሊዮን ብር ነው #የተጨመረብኝ። እውነት ድርጅቱ ጨምሮበት ነው ወይስ የድሃ እንባ ፈልጎ ነው ? ”- እያለቀሱ ቅሬታ ያቀረቡ ቆጣቢ እናት 2012 ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ በኦክሎክ ጀነራል ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኀበር አማካኝነት መኪና ለማስመጣት ገንዘብ ሲቆጥቡ የነበሩ ከ40 በላይ በሆኑ ማኀበራት ሥር የሚገኙ ከ2 ሺህ 800 በላይ ቆጣቢዎች፣ ውል የገባላቸውን መኪና አስመጪ…
#Update

ኦክሎክ ሞተርስ ኃ/የተ/የግ/ማሕበር “ ገንዘብ ተጨምሮብናል ” በማለት እያለቀሱ ቅሬታ ላቀረቡ የታክሲ ቆጣቢዎች ምን ምላሽ ሰጠ ?

የመኪና ቆጣቢዎች በ " ኦኮሎክ ሞተርስ " ላይ ያላቸውን ቅሬታ በገለጹበት ወቅት እያለቀሱ መንግሥት መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

አንዲት እናት፣ “ እኔ 1.5 ሚሊዮን ብር ነው #የተጨመረብኝ። እውነት ድርጅቱ ጨምሮበት ነው ወይስ የድሃ እንባ ፈልጎ ነው? ” ሲሉ እያለቀሱ መናገራቸው መረጃ አድረሰናችሁ ነበር።

ሌሎች እናቶች፣ አባቶች እያለቀሱ ያላቸውን ቅሬታ አሰምተዋል።

ቆጣቢዎች ፦

➡️ " ኦክሎክ ጀነራል ትሬዲንግ ኃላ/የተ/የግ/ማኀበር (ኦክሎክ ሞተርስ) መኪናውን በወቅቱ አላስረከበንም "

➡️ " የገንዘብ ጭማሪ አደረገብን " ላሉት ቅሬታ ምላሻችሁ ምንድነው ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የኦክሎክ ሞተርስ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ታመነ ካሳሁንን ጠይቋል።

የኦክሎክ ሞተርስ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ታመነ ካሳሁን ፦

“ እኔ እዚህ ላይ ትኩረት አድርጌ መልስ መስጠት እፈልጋለሁ፣ ምክንያቱም ' በእናንተ ድርጅት እዳለቀሱ ነው ' የሚለው የተሳሳተ ግንዛቤ ነው የሚል ሙሉ አቋም አለን። 

በውላችን መሠረት 35 ፐርሰንት ለእኛ ይከፍላሉ ውሉን ሲዋዋሉ። ከዚያ መኪናው ከመምጣቱ ከአንድ ወር በፊት 65 ፐርሰንት ከፍሎ 100 ፐርሰንት ሲሞላ መኪናውን ይወስዳል።

ስለዚህ አልቅሰዋል የተባሉት እናትም ይሁኑ አባት 35 ፐርሰንት ለድርጅታችን ከፍለው፣ 65 ፐርሰንትም ወይ ከአበዳሪ ድርጅት ወይ ከራሳቸው ካሽ ከፍለው መኪና ሳንሰጥ ቀርተን ነው ወይ ያለቀሱት ? ወይስ 35 ፐርሰንት ወይም 20 ፐርሰንት ከፍያቸሁና ስጡኝ ነው ጥያቄው ? ”

ይሄ ነው ትክክለኛ ያልሆነው። ያለቀሰ ሰው ሁሉ ትክክለኛ ነው ማለት አይደለም። ያላለቀሰ ሰው አይ ተስማምቷል ማለት እንዳልሆነው ሁሉ” ብለዋል።

1.5 ሚሊዮን ተጨሞሮብኛል ያሉትን ቅሬታ አቅራቢ ቆጣቢ እናትን በተመለከተም ፦ “ እኝህ እናት 1.5 ሚሊዮን ብር ተጨመረብኝ ካሉ እንግዲህ እኔ ደጋግሜ ነው የምናገረው ወይ መኪና ቀይረዋል ” ሲሉ መልሰዋል።

ያሉት 1,500 ተመዝጋቢዎች እንደሆኑ ፣ ከዚህ ውስጥ 400 የሚሆኑት 35 ፐርሰንት እንደከፈሉ፣ አሁንም 200 መኪናዎች እንዳሉት ማኀበራቱ ቀሪውን ከፍለው መውሰድ እንደሚችሉ ኦክሎክ ሞተርስ አስታውቋል።

#TikvahaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ ታጋቹ ከ3 ወር መሰወር በኃላ የማስለቀቂያ ክፍያ ተጠየቀባቸው።  "አጋቾች ነን" ባዮች የጠየቁት ገንዘብ በ1 ሳምንት ጊዜ ካልተከፈላቸው ታጋቹን እንደሚገድሉት እንደዛቱ የታጋች ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። እገታው እንዴት እና መቼ ተፈፀመ ?  የሰዎች እገታ ከህፃናት አልፎ እድሜያቸው በገፉት ላይም በመቀጠል በህብረተሰቡ ውስጥ ቀውስን ማቀጣጠል መቀጠሉ እየተገለፀ ይገኛል። ታጋቹ…
#Update

ታግታ ከተወሰደች በኃላ ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር የተጠየቀባት ታጋዲዋ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ታግታ ከተወሰደች 20 ቀናት ሆኗታል።

ቤተሰቦቿ " ልጃችንን አፋልጉን " ሲሉ በፈጣሪ ስም ተማጽነዋል። መላው ኢትዮጵያ ህዝብ እና የፀጥታ ኃይል ልጃቸውን እንዲፈልግላቸው ጥሪ አቅርበዋል።

የታዳጊ ተማሪ ማህሌት ቤተሰቦች ከትግራይ ዓድዋ ከተማ ያስተላለፉት የአፋልጉን የተማፅኖ ጥሪ ምን ይላል ?

የማህሌት ተኽላይ ቤተሰቦች ፦

" ታዳጊ ልጃችን ተማሪ ማህሌት ተኽላይ መጋቢት 10/2016 ዓ.ም ከ 11:00 ሰዓት በኃላ ወደ ቋንቋ ትምህርት ቤት በመሄድ ሳለች በትግራይ ዓድዋ ከተማ ዓዲ ማሕለኻ ተብሎ ከሚጠራ ልዩ ቦታ ለጊዜው ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታፍና ተወስዳለች።

አጋቾቹ በወሰዱዋት ቀን በራስዋ ሞባይል ስልክ ወደኛ በመወደወል ለማስለቀቅያ 3 ሚሊዮን ብር እንድንከፍላቸው ጠይቀውናል።  ከዛ በኃላ ግን በደውሉበት የልጃችን የሞባይል ቁጥር ብንደውልም አናገኛቸውም፤ በሌላ የሞባይል ቁጥር ደውለውም ያሉን ነገር የለም።

ስለሆነም እኛ የታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ወላጆች በከፍተኛ ጭንቅና ሃዘን ውስጥ እንገኛለን። ስለዚህ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብና የፀጥታ አካላት የአፋልጉን የተማፅኖ ጥሪ እናቀርባለን። "

ማህሌት ተኽላይ የሚመለከት ማንኛውም አይነት መረጃ ለመስጠት ፦
+251938819844 ሙሴ ተኽላይ
+251992733943 ደጀን ተኽላይ 
+251935036100/
+251962529287 ሚልዮን ተኽላይ
በሚሉ የሞባይል ቁጥሮች እንድትጠቀሙ በትህትና እንጠይቃለን። "

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሁኔታውን እንዲያብራሩ የታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ቤተሰቦችን ጠይቆ ፥ " የዓድዋ ፓሊስ እኛን መልሶ ምን አዲስ ነገር አለ ብሎ ይጠይቀናል ? " ሲሉ መልሰዋል።

የመቐለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ስለ ጉዳዩ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ወደ #ዓድዋ እና #አክሱም ያደረገው ጉዞ በፓሊስ አመራሮች ስብሰባ ምክንያት አልተሳካም።

#TikvahFamilyMekelle
                                            
@tikvahethiopia            
#ባህርዳር

በአማራ ክልል መዲና በባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 14 ትላንት መጋቢት 29 የመግሪብ ሰላት ሰግደው ሲመለሱ የነበሩ አባት ከ3 ልጆቹ እንዲሁም አንድ ጎረቤታቸውን ጨምሮ አጠቃላይ 5 ሰዎች በተከፈተባቸው የጥይት እሩምታ መገደላቸው ተነግሯል።

ትላንትና ምሽት በግፍ የተገደሉት ፥ አቶ ሙሄ ፣ ልጃቸው አበባዉ ሙሄ ፣ ሽኩር ሙሄ ፣ ሙላት ሙሄ እና ጎረቤታቸው አቶ እንድሪስ የተባሉ ሲሆኑ ስርዓት ቀብራቸው በዛሬው ዕለት ተፈፅሟል።

እስካሁን ገዳዮች ስለመያዛቸው የተባለ ነገር የለም።

በከተማዋ ከተገደሉት ሰዎች ባሻገር ባህርዳር ከተማ አባይ ማዶ የሚገኘው መስጂድ ከፍተኛ የመሳሪያ ድብደባ እንደተፈፀመበት ተገልጿል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዛሬ የባህር ዳር ሙስሊሞች በክልሉ በሙስሊሞች ላይ አነጣጥረዋል ያሉትን ግድያ እና እገታ በመቃወም ሰልፍ ማድረጋቸውን " ሀሩን ሚዲያ " ዘግቧል።

እስካሁን በአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤትም ሆነ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተሰጠ አስተያየት የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በክልሉ ተፈፅመዋል ስለተባሉ ግድያዎች ፣ ጥቃቶች ፣ ዘረፋና እገታዎች የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት እና የሚመለከታቸው አካላትን ለማነጋገር ጥረት እያደረገ ይገኛል፤ ምላሽ እንዳገኘ ተጨማሪ መረጃዎችን ያቀርባል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ መንግስት ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች/startups እንዲያብቡ በርካታ የፖሊሲ ለውጦችን ለማድረግ መወሰኑ ተሰማ። ከነዚህም መካከል ፦ - ከስራ ፈቃድ፣ - ከግብር፣ - ከቢሮ ኪራይ፣ - ከፋይናንስ አቅርቦት፣ - ከጉምሩክ አሰራር ጋር በተያያዘ ወሳኝ ለውጥ የሚደረግባቸው ይሆናሉ ተብሏል። ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ በተገኙበት ዛሬ ይፋ የተደረጉ ለውጦች በተለይ ስራ ፈጣሪዎች ከውጭ ለሚኖራቸው…
' ስታርት አፕ '

በኢትዮጵያ ለ ‘ስታርት አፕ’ ዘርፍ ዕድገት መሠረት የሚጥሉ የተለያዩ የሕግና የፋይናንስ አሠራር ማሻሻያዎች መደረጋቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አሳውቀዋል።

ምንድነው የተደረጉት ማሻሻያዎች / የተዘረጉት አዳዲስ አሰራሮችስ ምንድናቸው ?

- የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች ሃሳባቸውን ወደ ተግባር ለማዋል በሚፈልጉበት ወቅት ያለምንም የንግድ ቤት ኪራይ ውል ሥራ መጀመር ይችላሉ።

- ማንኛውም የውጭ ሀገር ፈንድ ያገኘ ስታርት አፕ ሙሉ በሙሉ የውጭ ምንዛሪውን ለሚፈልገው ሥራ ማዋል ይችላል።

- አዲስ ፈጠራ ያላቸውና ሥራቸው ወደ ገቢ መቀየር የሚችሉ ወጣቶች በውጭ ሀገራት ለተለያዩ አገልግሎቶች ክፍያ በሚጠየቁበት ወቅት በባንኮች በኩል መንግሥት በሚያመቻቸው አሠራር ክፍያ መፈጸም የሚችሉበት አማራጭ ይመቻቻል።

- በፈጠራ ላይ ለተመረኮዙ ቴክኖሎጂ መር ሥራ ፈጣሪዎች በጉምሩክ አሠራር ሂደት የሚያጋጥሙ ክፍያዎችን የሚቀንስና የጉምሩክ ድጋፍ የሚያገኙበት ማዕከል ይቋቋማል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል ፥ " ወጣቶች እንደሀገር የተመቻቸላቸውን ዕድል በመጠቀም ሃሳባቸውን አውጥተው ሥራ ላይ ማዋልና የተሻለ ገቢ ማግኘት አለባቸው " ብለዋል። #ኢፕድ

@tikvahethiopia
#ዒድአልፈጥር

የዒድ አልፈጥር በዓል #ጨረቃ ዛሬ ከታየች ነገ #ማክሰኞ ካልታየች ደግሞ #ረቡዕ ይከበራል።

በሳዑዲ አረቢያ የሸዋል ጨረቃ ለማየት በቱማይር እና ሱዳይር የመመልከቻ ቦታ አስፈላጊ ዝግጅት መደረጉ ተነግሯል።

@tikvahethiopia
የትምህርት ቤት መፀዳጃ ቤት #ተደርምሶ የ3 ታዳጊ ተማሪዎች ህይወት ተቀጠፈ።

ዛሬ በትግራይ ምስራቃዊ ዞን የጉሎመኻዳ ወረዳ በሚገኘው " መረታ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት " መፀዳጃ ቤት ተደርምሶ 3 ተማሪዎች ወዲያው ህይወታቸው አልፏል።

የመደርመስ አደጋው በእረፍት ጊዜ ከረፋዱ በ4:00 ሰአት የደረሰ ሲሆን የሴቶች የጋራ መፃዳጃ ቤት ሲጠቀሙ ከነበሩ 6 እንስት ተማሪዎች 3ቱ ወድያውኑ ሲሞቱ 3ቱ ቆስለው ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል።

ትምህርት ቤቱ ፤ ለመፀዳጃ ቤቱ መደርመስ መንስኤው በአከባቢው የዘነበ ከባድ ዝናብ እና መፀዳጃ ቤቱ ለረጅም ጊዜ ማገልገሉ እንደሆነ ገልጿል።

አደጋው በት/ቤቱ ተማሪዎች ፣ መምህራን እና ወላጆች ላይ ከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን መፍጠሩን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን ያገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia