TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
አንጋፋው የኢትዮጵያ አርቲስት ክቡር ዶ/ር አሊ ቢራ #በህይወት አለ። በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ አንጋፋው የሀገራችን አርቲስት ክቡር ዶክተር አሊ ቢራ " አረፈ / ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ " እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው። ክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ ባጋጠመው የጤና እክል የተነሳ በአዳማ ጄነራል ሆስፒታል ለላፉት ቀናት #የሕክምና_ክትትል እየተደረገለት ይገኛል። የ75 ዓመቱ አርቲስት አሊ…
" መሰል ሀሰተኛ መረጃ ሲነዛ በዚህ ወር ብቻ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ነው "

ዛሬ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች አንጋፋው የኢትዮጵያ አርቲስት ክቡር ዶ/ር አሊ ቢራ " ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ " እየተባለ ሲናፈስ የነበረው መረጃ #ሀሰተኛ ነው።

በክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ ላይ መሰል ሀሰተኛ መረጃ ሲነዛ በዚህ ወር ብቻ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ነው።

ከወራት በፊት ተመሳሳይ ሀሰተኛ ወሬ መሰራጨቱ እና ቤተሰቦቹን እጅጉን መጉዳቱና ማሳዘኑ የሚዘናጋ አይደለም።

ክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ ባጋጠመው የጤና እክል የተነሳ በአዳማ ጄነራል ሆስፒታል የሕክምና ክትትል እየተደረገለት ይገኛል።

እንዲህ ያለው ነውር በሀገራችን የማህበራዊ ሚዲያ ላይ እጅግ እየተደጋገመ ሲሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚከተሏቸው ትልልቅ የማህበራዊ ሚዲያዎችም ሰለባ እየሆኑ ነው።

አንዳንድ ጊዜ " ፈጥነን መረጃ አደረስን " ለማለት ያህል ፤ እንዲሁም የዩትዩብ ብር ለማግኘት / ላይክ ለመሰብሰብ ሲባል የሰዎችን ህይወት መረበሽ እና መበጥበጥ ከህሊና ያፈነገጠ ተግባር ነው።

@tikvahethiopia
ሀሰተኛ የትምህርት መረጃ ...

(በዳውሮ ዞን)

በዳውሮ ዞን ፤  ከጪ በተባለው ወረዳ ለመጀመሪያ ዙር በተደረገ ማጣራት ከ264 የትምህርት መረጃ 127 #ሀሰተኛ ሆኖ መገኘቱ ተሰምቷል።

ሀሰተኛ ሆኖ ከተገኘው የትምህርት መረጃ መካከል 6ቱ #የአመራርና ቀሪው #የመንግስት_ሰራተኞች ነው።

የሁለተኛ ዙሪ የማጥራት ስራ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

በዚሁ ዞን ፤ ቶጫ በተባለው ወረዳ በመጀመሪያ ዙር ከተደረገው ማጣራት ከ565 የትምህርት መረጃ የ218 ሰዎች #ሀሰተኛ ሆኖ ተገኝቷል።

መረጃቸው ወደ ግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተልኮ ከተጣራው ከ565 የመንግስት ሰራተኞች መካካል የ210 ባለሙያዎችና የ8 #አመራሮች የትምህርት መረጃ ነው ሀሰተኛ ሆኖ የተገኘው።

ይኸው የማጣራት ስራ ይቀጥላል ተብሏል።

መረጃው ከዳውሮ ኮሚኒኬሽን የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ 20 ሺህ ሰራተኞችን ሊቀጥር ነው ?

ከሀሰተኛ መረጃ ተጠንቀቁ !

በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በማህበራዊ ትስስር ገፁ 20 ሺህ #ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን መቅጠር እንደሚፈልግ አስታወቀ ፤ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን የሚቀጥረው ትግራይ ፣ አፋር፣ ሶማሌ ክልሎችን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች የቴሌኮም አገልግሎቱን ለማስፋፋት በማቀድ ነው ፤ የስራ ቅጥሩ ዲግሪ አይጠይቅም 10ኛ እና 12ኛ ክፍል ያጠናቀቁ ማመልከት ይችላሉ " እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ ፍፁም #ሀሰተኛ መሆኑን ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ገልጾልናል።

ከጥዋት አንስቶ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የተሰራጨውን የ20 ሺህ ሰራተኞች ቅጥር መረጃ በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለሚመለከተው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ክፍል " በየትኛው የማህበራዊ ትስስር ገፃችሁ ላይ ነው ይህ ያሳወቃችሁት ? መረጃው እውነት ከሆነስ በየትኛው መንገድ ነው ማመልከት የሚቻለው ? " ስንል ጥያቄ ያቀረብን ሲሆን መረጃው #ሀሰተኛ ነው የሚል ምላሽ ተሰጥቶናል።

" እኛ 20 ሺህ ሰራተኞች ለመቅጠር በየትኛውም የማህበራዊ ትስስር ገፃችን ላይ ጥሪ አላቀረብንም ፤ መሰል ሀሰተኛ መረጃዎች የሚሰራጩት ሆን ተብሎ ተመሳስለው በተከፈቱ #ሀሰተኛ_ገፆች ነው " ሲል የሚመለከተው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ክፍል ገልጾልናል።

በመሆኑም " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ 20 ሺህ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን ሊቀጥር ነው " በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው።

@tikvahethiopia
" የትኛው ፖሊስ ጋር ነው ያመለከቱት ? ፌክ ኒውስ በጣም በብዛት እያሰራጩ ነው " - የፌዴራል ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጄይላን አብዲ

በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በታጣቂዎች እገታዎች ተፈፅመው በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እንደሚጠየቅ በተደጋጋሚ መገለፁ ይታወቃል።

በቅርቡ አንድ ሰዓሊ ከጓደኛው ጋር ሶደሬ አካባቢ ከታገተ በኃላ ቤተሰቦቹ ጋር ተደውሎ ገንዘብ ከተጠየቁ በኃላ ለመነጋገር ድጋሚ ሲደውሉ " በእሱ ጉዳይ አትደውሉልን አፈር አልብሰነዋል " የሚል መርዶ ተነግሯቸው ሀዘን ላይ እንደነበሩ ፤ ጓደኛው ግን 500 ሺህ ብር ከፍሎ ከእገታ መውጣቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማሳወቁ ይታወሳል።

ከዚህ ክስተት በፊትም የሰዴን ሶዶ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ በቀለ ቃቻ ፤ ከመኖሪያ ቤታቸው በታጣቂዎች ታፍነው ከተወሰዱ ከሁለት ቀን በኃላ ተገድለው መገኘታቸውን መግለፃችን ይታወሳል።

እኚህን ባለስልጣን ያገቷቸው ታጣቂዎች 10 ሚሊዮን ብር መጠየቃቸው መነገሩም አይዘነጋም።

ወደ ጎጃም መስመር " ዓሊዶሮ " ላይም 30 ሹፌሮች እና ረዳቶች በታጣቂዎች መታገታቸውን ቤተሰቦቻቸው መግለፃቸው ፤ ከታገቱት ውስጥም 500 ሺህ እና 1 ሚሊዮን ብር ቤተሰቦቻቸው ከፍለው የተለቀቁ ስለመኖራቸው መግለፃችን የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው።

እንደውም ከቀናት በፊት ልጃቸውን ከእገታ ለማስለቀቅ 1 ሚሊዮን ብር የከፈሉ አሳዛኝ መምህር ታሪክ መሰራጨቱ ይታወሳል።

ወራትን ወደኃላ ብንጓዝ በርካቶች እየታገቱ ገንዘብ ተጠይቆባቸው ለአጋቾች ተከፍሎ ተለቀዋል ፤ በርካታ ሚዲያ ላይ ያልቀረቡ መሰል ክስተቶች አሉ።

ከታጋች ቤተሰቦች እንደሚሰማው ጉዳዩን ወደ ፖሊስ ቢወስዱት አጋቾች የያዙትን ሰው ህይወት ያጠፋሉ የሚል ስጋት አለ ፤ ከዛ ውጭ ግን ጉዳዩን ሀገር ያወቀው ፀሀይ የሞቀው ጉዳይ ነው።

ዛሬ በነበረው የፓርላማ ውሎም የምክር ቤት አባላት የእገታ ጉዳይን አንስተው አሳሳቢነቱን ገልጸዋል። ለጠ/ሚኒስትሩም ጥያቄ አቅርበዋል።

ይህንን የእገታ ጉዳይ በተመለከተ ዶቼ ቨለ ሬድዮ አንድ አጭር ዘገባ አሰራጭቶ የተመለከትን ሲሆን በዚሁ ዘገባ ላይ የነዋሪዎች / አሽከርካሪዎች እና የፌዴራል ፖሊስ ቃል ይገኝበታል።

አንድ ቃላቸውን የሰጡ አሽከርካሪ ፤ ጅቡቲ ኮሪደር ላይ እስካሁን ከነበረው አሁን ላይ መሻሻል እንዳለ፤ መንግሥት ከፍተኛ ሰራዊት መድቦ ከወለንጪቲ እስከ መተሃራ በፌዴራል እና መከላከያ የሚጠበቅ ቀጠና መሆኑን ገልጸዋል። አሁን ትልቁ ችግር ያለው ከፍቼ - ጎሃ ፂዮን ያለው ቀጠና ነው ብለዋል።

አንድ የአ/አ ነዋሪ ደግሞ ከእገታ ጋር በተያያዘ 3 ዓይነት ሰዎች አሉ ፤ እራሳቸው ሳይታገቱ " ታግተናል " በሚል ለፖለቲካም ሆነ ለሌላ አላማ የሚጠቀሙ ፣ የገንዘብ ፍላጎት ኖሯቸው የሚንቀሳቀሱ አሉ እነዚህ ገንዘብ ያላቸውን ፣ ቢዝነስ ውስጥ ያሉ ሰዎችን አጥንተው የሚንቀሳቀሱ ናቸው ፤ በረሃ ላይ አሸከርካሪዎችን የሚያግቱም አሉ እነዚህም ገንዘብ ይጠይቃሉ ሲሉ አስረድተዋል።

ልጅም " ታገትኩ " ብሎ አባቱን ገንዘብ የሚያስጠይቅም አለ እውነቱን ለማወቅ አቸጋሪ ጊዜ ነው ነገሩ ሁሉ ውስብስብ ነው ሲሉ አክለዋል።

የፌዴራል ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጄይላን አብዲ ግን የሚሰራጨው #ሀሰተኛ_መረጃ መሆኑን ገልጸው አሽከርካሪዎችም ሆኑ ሌሎች ከታገቱ የት ፖሊስ ጣቢያ ሄደው እንዳመለከቱ መረጃ ሊጣራ ይገባል ብለዋል።

አቶ ጄይላን ፤ " የትኛው ፖሊስ ጋር ነው ያመለከቱት ? ፌክ ኒውስ በጣም በብዛት እያሰራጩ ነው ፤ ፌዴራል ፖሊስ መንገድ ላይ እዛው አመልክተዋል ወይ ? ሆን ተብሎ ፌክኒውስ ሀገሪቱ ላይ ሰላም እንደሌለ ለማስመሰል ፤ፌክኒውስ እየተሰራጨ ነው ያለው ሰው ታግቷል ተብሎ " ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethiopia
የትግራይ ክልል ለጦርነት እየተዘጋጀ ነው ?

" ለጦርነት የሚዘጋጅ ኃይል ሰራዊቱን አይቀንስም ፤ ዝግጅታችን ለሰላም ብቻ ነው " - አቶ ረዳኢ ሓለፎም

" ትግራይ ለጦርነት እየተዘጋጀች ነው " በሚል እየተሰራጩ ያሉ መረጃዎች #ሀሰተኛ ናቸው ሲል ክልሉ ገለጸ።

ከሰሞኑን ክልሉ " ለጦርነት ዝግጅት እያደረገ ነው ፤ በኃይል ተይዘውብኛል የሚላቸውን የክልሉ አካባቢዎች ነፃ ለማድረግ ወደ ኃይል እርምጃ ሊገባ ነው " የሚሉ የተለያዩ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየተሰራጨ ይገኛል።

" ትግራይ ለጦርነት እየተዘጋጀች ነው " በሚል ስለሚሰራጨው መረጃ የክልሉ ጊዜያዊ መንግሥት ቃል አቀባይ ረዳኢ ሓለፎም " ይህ ውሸት ነው ፤ 24 ሰዓት ሙሉ ክልሉ እየሰራ ያለው ሰላሙን ዘላቂ ለማድረግ ነው ፤ ጉዟችን ሁሉ ለሰላም ነው " ብለዋል።

አቶ ረዳኢ ፤ " ሰላሙ እንዲጠከር ስለምንፈልግ ነው ታጣቂ ኃይሉን እየቀነስን ያለነው ፤ ከአሁን ቀደም ከትግራይ በኩል ማውረድ የነበረብንን ትጥቅ በየጊዜው እያስረከብን መጥተናል በተፈራረምነው የሰላም ስምምነት ከትግራይ የሚጠበቁትን እያደረግን ነው ቀረ የሚባል ነገር ያለ አይመስለኝም ፤ በቀጣይነትም ይህን አጠናክረን ወደ ተሟላ ሰላም ለመሄድ የትግራይ በሮች ክፍት ናቸው " ብለዋል።

" ጊዜያዊ አስተዳደሩ 24 ሰዓት እየሰራ ያለው ሰላሙን ለማፅናት ነው፤ ዘላቂ እንዲሆን ነው " ያሉት አቶ ራዳኢ ፤ " እኛ በራሳችን ማድረግ የሚገባንን እያደረግን ነው በሌላው ወገን ያልተተገበሩ ነገሮች አሉ የአማራ ታጣቂዎች በትግራይ ምድር ላይ ነው ያሉት፣ የሻዕቢያ ሰራዊት አሁንም በትግራይ ነው ያለው ፤ ያ በመሆኑ ተፈናቃዮቻችን አሁንም በስቃይ ነው እየኖሩ ያሉት ስለዚህ ይህ መፈታት አለበት ፤ እነዚህ ኃይሎች መውጣት አለባቸው ተፈናቃዮችም ወደ ቄያቸው መመለስ አለባቸው " ብለዋል።

" ይህ እየሆነ ያለው ግን እኛ ያልፈፀምነው ነገር ስላለ አይደለም የሚጠበቅብንን ሁሉ እያደረግን ነው " ሲሉ አክለዋል።

አቶ ረዳኢ ፤ " ለጦርነት የሚዘጋጅ ኃይል ሰራዊቱን አይቀንስም ፤ በቅርቡ እራሱ ከ50 ሺህ በላይ ሰው Demobilize እያደረግን ያለነው ፤ አጠቃላይ ጉዟችንም ቢሆን የሰላም ነው ፤ ሰላሙ እንዲፀና ነው የምንፈልገው፤ ድሮም ቢሆን እንዳልነው ተገደን የገባንበት እንጂ መርጠን የገባንበት አይደለም ፤ በዚህ የሚመጣው ክስ (ጦርነት ሊጀምሩ ነው) ከተግባራችን ጋር የማይሄድ ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

ይህንን እያስወሩ ያሉት " ምኞታቸውን ነው " የሚሉት አቶ ረዳኢ ሓለፎም ፤ " ትግራይ ወደ ሰላም መግባት የለባትም የሚል አቋም የያዙ አካላትና ኃይሎች ናቸው ሰላሟን እንዲታወክ ስለሚፈልጉ ሆን ብለው በየቀኑ አጀንዳ ያመጣሉ " ሲሉ ወቅሰዋል።

" ከጦርነት በፊትም ኮሽ ባለ ቁጥር የወያኔ እጅ አለበት ፤ የትግራይ እጅ አለበት ፣ ሶስተኛ ወገን አለበት እያሉ ነበር ህዝቡን ሲያጦዙት የነበረው ፤ በሌለ ነገር አዲስ ስሜት ፈጥረው ቀስቅሰው በትግራይ ተወላጆች ላይ ታሪክ ይቅር የማይለውን ስህተት እና ክህደት የፈፀሙት ፤ አሁንም ይህን የማስቀጠል ነገር ነው ዓላማቸው ፤ በትግራይ በኩል ለጦርነት የሚዘጋጅበት ምንም ነገር የለም ፤ እየተዘጋጀ አይደለም ፤ የትግራይ ህዝብም መስተዳደርም ዝግጅቱ ለሰላም ብቻ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
ጅግጅጋ የሆነው ምንድነው ?

ከሰሞኑን በጅግጅጋ ከተማ እጅግ አሰቃቂ የተባለ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ተፈፅሟል።

የአስገድዶ መድፈር ወንጀሉ የተፈፀመባት የ9 ዓመት ህፃን ልጅ ስትሆን ይህ ድርጊት ከተፈፀመባት በኃላ የድርጊቱ ፈፃሚዎች የደፈሯትን ልጅ ገድለዋታል።

ከዚህ አሰቃቂ ድርጊት በኃላ ወንጀሉን የፈፀሙ 4 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ሊውሉ እንደቻሉ ተገልጿል።

ነገር ግን ከዚህ የወንጀል ድርጊት ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎችን በመያዙ ሂደት ላይ ሰዎችን ለይቶ በአፈሳ የማሰር ድርጊት እንደነበር ቃላቸውን የሰጡ የጅግጅጋ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የጅግጅጋ ነዋሪ በሰጡት ቃል ፤ ከህፃኗ መደፈር ድርጊት ጋር በተያያዘ ሰኞ 4 ተጠርጣሪዎች ቢያዙም በከተማው ሰፊ አፈሳ ሲደረግ ነበር ብለዋል።

በተለይም ከደቡብ አካባቢ የመጡ ልጆች በድርጊቱ ላይ በመጠርጠራቸው ይህን መሰረት ያደረገ እስር ሲፈፀም እንደነበር ገልጸዋል። ድርጊቱ እስከ ትላንት ድረስ መቀጠሉን ጠቁመዋል።

አንድ ሌላ ነዋሪ ድርጊቱ እጅግ በጣም አሰቃቂና አስደንጋጭ እንደነበር ገልጸው ከተጠርጣሪዎች አያያዝ ጋር በተያያዘ በፀጥታ ኃይሎች የተፈፀመው ድርጊት ተገቢ አይደለም ብለዋል።

" ተጠርጣሪዎችን በልዩነት ማሰር እየተቻለ ሰዎች በአፈሳ ወደ ማቆያ ሲገቡ ነበር ይህ ተገቢ ያልሆነ አካሄድ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ሌላ አንድ ነዋሪ ደግሞ ፤ " እሁድ እለት አንድ ልጅ ተደፈራ ከተገደለች በኃላ ድርጊቱን የፈፀሙ ግለሰቦች ተይዘው ለህግ ቀርበዋል " ብለዋል።

" ይሄ ጥሩ ነው " ያሉት እኚሁ ነዋሪ ነገር ግን ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት የለላቸውን ሰዎች ፓሊስ በጅምላ በማፈስ ማሰረሱን ፣እና መደብደቡን ጠቁመዋል።

በነበረው ሁኔታ የሰዎች ህይወት ማለፉን እንደሰሙ ገልጸዋል።

በተለይ ከደቡብ የመጡ ወጣቶችን መታወቅያ በማየት እስር ፣ ድብደባ ሲፈፀም ነበር ይህን የሚመለከተው አካል ይወቀው ሲሉ ገልጸዋል።

የሶማሌ ክልል መንግሥት ግን ከአሰቃቂው የወንጀል ድርጊት በኃላ ተፈፅሟል የተባለው ድርጊት #አሉባልታ እና #ሀሰተኛ ነው ብሏል።

የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ አብድቃድር ረሽድ ፤ " በሱማሌ ክልል የሌላ ክልል ተወላጆች እየታፈሡ እየታሰሩ ፣እየተገደሉ ነው በሚል በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው አሉባልታ ወሬ ነው " ያሉ ሲሆን የሚንገረው ሁሉ ውሸት ነው ብለዋል።

" የሶማሌ ህዝብ ሰፊ ህዝብ ነው አቃፊ ነው ፣ ከየትኛውም ህዝብ ጋር የመኖር ባህል ያለው ማህበረሰብ ነው ፤ የሌላ ኢትዮጵያዊ ተወላጅ የማሳደድ፣ የመግደል ባህል ፈፅሞ የለውም የሚነገረው ሁሉ ውሸት ነው፤ የሶማሌ ህዝብን ስም ለማንቋሸሽ የሚሰራ ፕሮፖጋንዳ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

" የህግ አካላት ቦታው ላይ ሳይደርሱ ሁከት ለመፍጠር ሙከራ ተደርጎ ነበር " ያሉት ኃላፊው የህግ አካላት የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ የወሰዱት እርምጃዎች ነበሩ ብለዋል።

" እነዛም መቆያ አካባቢዎች ለደህንነታቸው ስጋት የቆዩ አካላት በማጣራት ወደመደበኛ ስራቸው እንዲመለሱ ትላንት በፀጥታ አካላት መመሪያ ተሰጥቷል። " ሲሉ ተናግረዋል።

" በሶማሌ ክልል ምንም ችግር የለም ሰላም ነው ፤ የሶማሌ ህዝብ አቃፊ ነው " ያሉት ኃላፊው የፖለቲካ አጀንዳ በማድረግ ተቃውሞ በመፍጠር ብጥብጥ ለመፍጠር ፣ በክስተቶች ላይ ክስተት በማጋነን ፣ እከሌ ተገደለ፣ እከሌ ዘሩ እንዲህ ነው በማለት ለፖለቲካ የሚጠቀሙ ኃይሎች አሉ " ብለዋል።

" የሶማሌ ክልል ሰላም ነው ፤ ሁሉም ወደ መደበኛው ስራ ተመልሷል " ሲሉ አክለዋል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የተሽከርካሪዎች_ጨረታ_ጉምሩክ_ኮሚሽን_አዳማ_.pdf
ውዝግብ የፈጠረው የበርካታ ተሽከርካሪዎች ጨረታ !

" ' የጉምሩክ ኮሚሽን ' የገንዘብ ሚኒስቴርን ውሳኔ በመጣስ 237 መኪኖችን ለሐራጅ አወጣብን " - ከሰደት ተመላሾችና 10 የሚደርሱ የአገር ውስጥ አስመጪዎች

" በግልፅ ጨረታ ለሽያጭ የቀረቡት ተሽከርካሪዎች ህጋዊ ስርዓቱን በአግባቡ በተከተለ መልኩ ነው። ' ህጋዊ ስርዓቱን አልተከተለም ' በሚል የሚሰራጩት መረጃዎች ሀሰተኛ ናቸው ፤ #ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ አካላትን በህግ አግባብ እንጠይቃለን " - ጉምሩክ ኮሚሽን

ከሰሞኑን የአዳማ ጉምሩክ ኮሚሽን ፅ/ቤት ያወጣው የበርካታ ተሽከርካሪዎች ጨረታ ውዝግብ የፈጠረ ሆኗል።

በዚህ ጉዳይ ላይ ቅሬታ አለን ያሉ ከሰደት ተመላሾችና የአገር ውስጥ አስመጪዎች ፤ " ጉምሩክ ኮሚሽን የገንዘብ ሚኒስቴር ውሳኔን በመጣስ 237 ተሽከርካሪዎች ለሐራጅ አወጣብን " በሚል ከሰዋል።

ጉምሩክ ኮሚሽን በበኩሉ ፤ " ምንም አይነት የህግ ጥሰት አልፈተፈፀም ህጉን እና አሰራሩን በተከተለ መልኩ ነው ተሽከርካሪዎቹ ለጨረታ የቀረቡት " ሲል አሳውቋል።

ያንብቡ 👇 https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-11-24

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ይፈለጋል #Wanted " ... ሟች ያሳድጉት የነበረው መሀመድ ሽኩር አበባው ፤ ሼህ አብዲ ያሲንን በመግደል ወንጀል ተጠርጥሮ ይፈለጋል " - ፖሊስ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፤ ሼህ አብዱ ያሲንን በመግደል የሚጠረጠረው መሀመድ ሽኩር አበባው የተባለ ግለሰብ መሆኑን ገልጿል። ግለሰቡ #እጁን_እንዲሰጥም ፖሊስ አሳስቧል። ፖሊስ ተጠርጣረው ያለበትን የሚያውቅ ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪውን አስተላልፏል።…
#ይፈለጋል #Wanted

ሼህ አብዱ ያሲንን በመግደል የሚጠረጠረው መሀመድ ሽኩር አበባው በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ ክትትሉን አጠናክሮ መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

አንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች ተጠርጠሪው እንደተያዘ በማስመሰል የሚያሰራጩት መረጃ #ሀሰተኛ መሆኑን አስታውቋል።

በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተጠርጣሪው ሳይያዝ እንደ ተያዘ አድርጎ መረጃ ማሰራጨት ተገቢ እንዳልሆነ የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ መሀመድ ሽኩር አበባው ያለበትን የሚያውቅም ሆነ ማነኛውም መረጃ ያለው በስልክ ቁጥር 011-1-11-01-11 ወይም በነፃ ስልክ ቁጥር 991 መረጃ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ ቀርቧል።

@tikvahethiopia
" ለ ' ህወሓት' የሰጠነው ምንም አዲስ እውቅና የለም " - የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ

በማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ለ "ህወሓት" እውቅና ስለ መሰጠቱ የሚሰያጨው መረጃ #ሀሰተኛ መሆኑን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ኮሚኒኬሽን ቢሮ በማህበራዊ ትስስር ገፆች በተለይም በፌስቡክ ለ " ህወሓት " እውቅና ስለመሰጠቱ #ሀሰተኛ_መረጃዎች እየተሰራጩ መሆኑን በተደረገ ቅኝት ማየት መቻሉን የገለፀ ሲሆን ለ " ህወሓት " የተሰጠ እውቅና #እንደሌለ ቢሮው ገልጿል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው እለት ፦
- ለወሎ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ
- ለኩሽ ህዝቦች ብሔራዊ ንቅናቄ
- ብሔራዊ ባይቶ ዓባይ ትግራይ ለተባሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባና የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት መስጠቱን አሳውቋል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ለ "ህወሓት" እውቅና ተሰጠ ተብሎ የሚሰራጨው #ሀሰተኛ_መረጃ ፥ መረጃውን የእውነት ለማስመሰል እየተደረገ ያለ ሙከራ መሆኑን የቦርዱ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ያስረዳ ሲሆን " ለህወሓት የሰጠነው ምንም አዲስ እውቅና የለም " ብሏል። 

ማንኛውም የብሄራዊ ምርጫ ቦርድን የተመለከተ መረጃ በቦርዱ ይፋዊ የፌስቡክ ገፅ እስካልወጣ ድረስ መረጃዎቹ ሀሰተኛ መሆናቸውንና ቦርዱን የማይወክሉ መሆኑን እንዲታወቅልኝ ሲል ቦርዱ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
#ጥንቃቄ🚨

" ማህበረሰቡ ያለበትን #የቤት_እጦት እና ፍላጎት በመገንዘብ ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ከኢትዮ - ቴሌኮም ጋር በመተባበር 100 ሚሊዮን ብር መድቦ እየሰራ ነው " እየተባለ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚሰራጨው መረጃ ፍጹም #ሀሰተኛ ነው።

በማህበራዊ ሚዲያው የሚዘዋወረው መልዕክት አጭበርባሪዎች ህብረተሰቡን #ለማጭበርበር የፈጠሩት ነው።

" ሼር ብቻ እያደረጋችሁ የቤት ባለዕድለኛ ሆኑ ፣ ተሸለሙ " የሚሉት መልዕክቶች በሁለቱም ተቋማት እውቅና የሌላቸው የአጭበርባሪዎች ስራ ናቸው።

" ቤት ታገኛላችሁ ሼር አድርጉ " እንዲህ የሚባል ነገር የለም።

ውድ የቲክቫህ ቤተሰቦቻችን ፤ መሰል #በውሸት የተሞሉ የማጭበርበሪያ ስልቶችን እንድትጠነቀቁ ከዚህ ቀደም በዛ ያሉ መልዕክቶች ተለዋውጠናል ፤ በቂ እውቀትም አላችሁ።

ምናልባት እንዲህ ያለን ሀሰተኛ መልዕክት አምኖ የሚጭበረበር ወዳጅ ዘመንድ እንዳይኖራችሁ አስገንዝቧቸው።

#TikvahFamily

@tikvahethiopia