TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከዓለም ዙሪያ ፦

#ካናዳ ፦ የካናዳው ጠ/ሚ ጀስቲን ትሩዶ አነስተኛ የእጅ ሽጉጥ መግዛትም ሆነ መታጠቅ እንዲከለከል ጠይቀዋል። የትሩዶ መንግሥት በጠቅላላው የእጅ ሽጉጥ መግዛት ሆነ ቤት ማስቀመጥ በሕግ እንዲያስቀጣ ረቂቅ እያወጣ ነው። ረቂቁ እንደሚለው ካናዳዊያን የእጅ ሽጉጦቻቸውን ባይነጠቁም ከዚህ በኋላ አዲስ መግዛት ግን አይችሉም። ትሩዶ ይህን ሐሳብ ያፈለቁት በአሜሪካዋ ቴክሳስ ግዛት አንድ አፍላ ታጣቂ 19 ሕፃናትን ተኩሶ ከገደለ በኋላ ነው።

➡️ #እስራኤል #UAE ፦ እስራኤል እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ የነፃ ንግድ ስምምነት ተፈራርመዋል ፤ ይህ እስራኤል ከአረብ ሀገር ጋር ያደረገችው የመጀመሪው ትልቅ ስምምነት ነው።

➡️ #ሴኔጋል ፦ የሴኔጋል ፖሊስ በአንድ ሆስፒታል ውስጥ በደረሰው እና የ11 ህጻናት ህይወት ከቀጠፈው የእሳት አደጋ ጋር በተያያዘ ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉ ተሰምቷል።

➡️ #ሩስያ ፦ በያዝነው ዓመት 70ኛ ዓመታቸውን የሚደፍኑት የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጤና እክል ምናልባትም በካንሰር ህመም እየተሰቃዩ ሳይሆን አይቀርም የሚሉ ያልተረጋገጡ የመገናኛ ብዙኃን ሪፖርቶች እየወጡ ናቸው። የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ግን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ታመዋል መባሉን ሀሰት ሲሉ አስተባበሉ። ላቭሮቭ ፕሬዚዳንት ፑቲን በየቀኑ በአደባባይ እንደሚታዩ እና እንደማኛውም ጤነኛ ሰው የህመም ምልክት አያታይባቸውም ብለዋል።

➡️ #ሶማሊያ ፦ የሶማሊያ ባይዶዋ ከተማ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድን ለመቀበል በዝግጅት ላይ ነች። ከተማዋ ፕሬዝዳንቱ ፈርማጆን አሸንፈው ዳግም የፕሬዜዳንትነት መንበሩን ከተረከቡ በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚጎበኟት ከተማ ትሆናለች።

#ቢቢሲ #ቲአርቲ #ሲጂቲኤን #SNTV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች እና ትምህርት ቤቶች ተሸለሙ። በዛሬው ዕለት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን እና ትምህርት ቤቶችን መሸለማቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። የፎቶ ባለቤት ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት @tikvahethiopia
#Update #UAE

በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ሙሉ ስኮላርሺፕ መስጠቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ መናገራቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ዛሬ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ወስደው ከግማሽ በላይ ውጤት ካስመዘገቡ ተማሪዎች ውስጥ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች እውቅና በሰጡበት ወቅት ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተማሪዎቹ " እንኳን ደስ ያላችሁ " ካሉ በኋላ የተሰጣቸውን ፈተና በአግባቡ መስራት በመቻላቸው " ኢትዮጵያን የሚያግዙ 273 ተማሪዎች ተገኝተዋል በዚህም ደስታ ይሰማናል" ብለዋል፡፡

ተማሪዎቹ እጅግ ዘመናዊ በሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እንደሚከታተሉና ለኢትዮጵያ እና አፍሪካ የሚደርሱ እንዲሆኑም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ተማሪዎቹ በርትተው ተምረው ሀገራቸውን ሳይረሱ የሚጠቅሙ እንዲሆኑም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።

ዶ/ር ዐቢይ ሁሉም ተማሪ ጥበብን እንዲሻ እና ሀገሩን ለመለወጥ እንዲሰራ ጠይቀዋል፤ በተለይ " ለእውነት የቆመ ተማሪ ነገ ሃገሩን ይለውጣል፤ እናንተ የላቀ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎችም እውነትን የምትሹ መሆን አለባችሁ እንደዛ ሲሆን ደግሞ ሀገርን የምትገነቡ ትሆናላችሁ " ብለዋል።

#ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
#UAE

በአቡዳቢ የኢትዮጰያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የመቃኞ ቤተ ክርስቲያን ለመንፈሳዊ አገልግሎት ክፍት ተደረገ።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ዛሬ በተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች / UAE#አቡዳቢ የኢትዮጰያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የመቃኞ ቤተ ክርስቲያንን መርቀውና ባርከው ለመንፈሳዊ አገልግሎት ክፍት አድርገዋል።

የቤተ ክርስቲያኑ መቃረቢያ ቤት ዛሬ በተመረቀበት ወቅት ቡራኬ የሰጡት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ፤ " በምትፈልጉት ጊዜ ከፍታችሁ የምትገቡበት ቤተክርስቲያን ስላገኛችሁ ደስ ብሎናል። ይህንን የሚያህል ስፋት ያለውም አይቼ አላውቅም። " ብለዋል።

Via Ethiopian Embassy - UAE

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA #UAE

የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ / UAE ፕሬዝዳንት ሼክ መሃመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ አዲስ አበባ መግባታቸው ተሰምቷል።

ሼክ መሃመድ ቢን ዛይድ አል ናህንያን አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ አቀባበል አድርገውላቸዋል ተብሏል።

በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከተለያዩ የመንግስት የስራ ኃፊዎች ጋር ተገናኝተው እንደሚወያዩ ይጠበቃል።

ሼክ መሃመድ ቢን ዛይድ ፕሬዝዳንት ከሆኑ በኋላ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሲያደርጉ ይህ የመጀመሪያቸው ነው፤ ከዚህ ቀደም የአቡዳቢ አልጋ ወራሽ በነበሩትበት ወቅት በ2018 በኢትዮጵያ ጉብኝት አድርገው ነበር።

መረጃው አልአይን ኒውስ ነው።
Photo : PM Office Ethiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ETHIOPIA 🤝 #UAE

ኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ (UAE) በፋይናንስና ኢንቨስትመንት ጨምሮ በሌሎች 17 ዘርፎች ስምምነት ተፈራርመዋል።

የስምምነቱ  ፊርማ ከመከናወኑ በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ልኡካን ቡድኖቻቸውን በመያዝ የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።

በኢትዮጵያ በኩል ከተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ የስራ ኃላፊዎች ጋር ስምምነቱን የተፈራረሙት ፦

- የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ
- የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ
- የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ
- የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር አለምፀሀይ ጳውሎስ
- የግብርና ሚኒስትር ዶ/ር ግርማ አመንቴ
- የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል
- የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ
- የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆንዲንግስ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ መለከት ሳህሉ
- የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዶ/ር ዓለሙ ስሜ
- የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ምስጋኑ አረጋ
- የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ተመስገን ጥሩነህ ናቸው።

ፎቶ፦ PMOEthiopia

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA🇪🇹 #UAE🇦🇪

ዛሬ የኢትዮጵያ አየር ኃይል እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ (UAE) አየር ኃይል አባላት በጋራ ሆነው " ጥቁር አንበሳ " የተሰኘ የአየር ላይ ወታደራዊ ትርዒት አቀረቡ።

ትርዒቱን ያቀረቡት የኢትዮጵያ አየር ኃይል 88ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ በቢሾፍቱ ከተማ በተካሄደ ስነስርዓት ላይ ነው።

በስነሥርዓቱ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ " በኢትዮጵያና በተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች አየር ኃይሎች በጋራ የቀረበው ወታደራዊ የአየር ላይ ትርዒት በትብብር ከሠራን የምንደርስበትን ደረጃ ያሳየ ነው " ብለዋል።

የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ በበኩላቸው የአየር ትርዒቱ ኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኢማራት በፖለቲካው እና በውትድርናው መስክ ያላቸውን መልካም ግንኙነት፣ ወዳጅነትና ትብብር ያሳየ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከተመሰረተ 88ኛ አመቱን የያዘ ሲሆን ካለፈው ህዳር 20 ጀምሮ የምስረታ በዓሉ እየተከበረ ነው።

Photo Credit - #PMOfficeEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ሶማሊያ በኢትዮጵያ ያሉትን አምባሳደሯን መጥራቷን ተከትሎ አምባሳደር አብዱላሂ ዋርፋ ወደ #ሞቃዲሾ ማቅናታቸው ተሰምቷል። በሌላ በኩል ደግሞ ፤ የሶማሊያ ሁለቱ የፌደራል ፓርላማ ምክር ቤቶች በአሁን ሰዓት አስቸኳይ የጋራ ስብሰባ የተቀመጡ ሲሆን በዚህ ስብሰባ ላይ የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ንግግር ያደርጋሉ ተብሏል። ከ100 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ የወደብ እና…
#Somalia #Somaliland

" የሶማሊያ ደካማ መንግስት ይሄን ታሪካዊ ስምምነት ለማስቆም ምንም አይነት ሕጋዊነት የለውም " - አብዱላሂ አርሼ (የሶማሊላንድ ባለስልጣን)

የቀድሞ የሶማሊላንድ " የሀገር ውስጥ " ሚኒስትር አማካሪ እና በአሁን ሰዓት በሶማሌላንድ " የሀገር ውስጥ " ሚኒስቴር የሚዲያ እና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር የሆኑት አብዱላሂ አርሼ የሶማሊያን መንግሥት " ደካማ መንግሥት " ሲሉ ጠርተው በኢትዮጵያ እና በሶማሊላንድ ሪፐብሊክ መካከል የተፈረመውን #ታሪካዊ_ስምምነት ለማስቆም ምንም አይነት ሕጋዊነት የለውም ብለዋል።

" የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እውቅና የሰጠው የሶማሊያ ስርዓት እንደ ወቀደ መንግስት ነው፣ ሞቃዲሾ ውስጥ የአስተዳደር ስርዓት የለም። " ሲሉ ጠንካራ ትችት ሰንዝረዋል።

ኢስማኤል ሺርዋክ የተባሉ የሶማሊላንድ ዲፕሎማት ደግሞ ፤ " ሀገራችን አንድ እርምጃ ወደፊት ስትሄድ ሶማሊያ በታሪክ ግልፅ የሆነ ጥላቻ  አሳይታለች። " ያሉ ሲሆን " ሶማሌላንድ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (#UAE) ስምምነት ላይ ሲደርሱ ተመሳሳይ እርምጃ ወስደዋል፣ ነገር ግን ምንም አይነት ውጤት አላመጣም። " ብለዋል።

" እንደ አንድ ሉዓላዊ ሀገር የዜጎቻችንን ጥቅም መሰረት አድርገን የሚያስፈልገውን እንወስናል " ሲሉ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ዛሬ ለሁለቱ የፌዴራል ም/ቤት አባላት ንግግር ማድረጋቸው የተሰማ ሲሆን የሶማሊላንድ እና የኢትዮጵያን የትብብር ስምምነት ሰነድ ተቃውመዋል።

" አንድም ኢንች የሶማሊያ ግዛት በማንም ሊፈረም አይችልም ፤ሉዓላዊነታችንንና የግዛት አንድነታችንን እንጠብቃለን ፤ በዓለም አቀፍ ህጎች መሰረት እናስከብራለን፤ እያንዳንዱን ኢንች መሬት እንጠብቃለን፤ ሶማሊያ የሶማሊያውያን ነች ፤ ይሄ የመጨረሻው ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

" አቶ መለስ ዜናዊ በሶማሊያ ውስጥ የገቡት ጣልቃ ገብነት የአልሸባብን መነሳት አስከትሏል " ሲሉ የተደመጡት ፕሬዜዳንቱ " የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እርምጃም ያሸነፍነውን አልሸባብ ዳግም እንዲነሳሳ ሌላ ዕድል የሚሰጥ ነው " ብለዋል።

" የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጥር 1 ከያዙት መንገድ እንዲመለሱ " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ ያላቸው አማራጭ አንድ ብቻ ነው እሱም በሰላም መኖር ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

የሶማሊንላንድ ባለልስጣናት ስምምነቱን የደገፉ ሲሆን በሶማሊያ ባለስልጣናት ላይም ጠንክራ ትችት እየሰነዘሩ ይገኛሉ። ስምምነቱን የማስቆም ምንም አይነት አቅም የላቸውም ሲሉ እየተደመጡ ናቸው።

@tikvahethiopia
#INDIA #UAE

ህንድ እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ (UAE) ዛሬ በህንድ ሰሜን ምዕራብ በምትገኘው ራጃስታን ግዛት የጋራ ወታደራዊ ልምምድ መጀመራቸው ተሰምቷል።

ወታደራዊ ልምምዱ " Desert Cyclone " በሚል ለቀጣይ ሁለት ሳምንት የሚዘልቅ ሲሆን በሀገራቱ መካከል ያለውን ወታደራዊ ልምድ እንዲለዋወጡ እንደሚያስችል እና ያላቸውን ትብብር ይበልጥ እንደሚያጠናክረው ተነግሯል።

የተባባሩት አረብ አሜሬትስ (UAE) ፤ ህንድ ያለችበትን የBRICS አባል ሀገራት በትላንትናው ዕለት ከነ #ኢትዮጵያ ፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ግብጽ፣ እና ኢራን ጋር በይፋ መቀላቀሏ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#IGAD ዛሬ በኡጋንዳ፣ ኢንቴቤ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግስታት (ኢጋድ) መሪዎች ስብሰባ ይደረጋል። ስብሰባው ትኩረት ከሚያደርግባቸው ጉዳዮች አንዱ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል የተፈጠረው ውጥረት ነው። ሌላው የሱዳን ጦርነት ነው። ለኢጋድ የመሪዎች ስብሰባ እስካሁን ድረስ በታወቀው ፦ የወቅቱ የኢጋድ ሊቀመንበር የጅቡቲው ፕሬዜደንት ኢሳሜል ኦማር ጌሌህ የሶማሊያው ፕሬዚዳንት…
#IGAD

" ... ማንኛውም #ስምምነት ወይም #ዝግጅት በሶማሊያ ፌዴራላዊ መንግስት #ፈቃድ መሆን አለበት " - ኢጋድ

የምሥራቅ አፍሪካ ልማት በየነ መንግሥታት (ኢጋድ) ዛሬ ኡጋንዳ ኢንቴቤ ውስጥ አስቸኳይ የመሪዎች ስብሰባውን አድርጎ ነበር።

ይህ አስቸኳይ ስብሰባ የኢጋድ መስራቿ ኢትዮጵያን ጨምሮ የኤርትራ እና የሱዳን መንግሥት ተወካዮች / መሪዎች ባልተገኙበት የተካሄደ ነው።

ስብሰባው ትኩረት ያደረገው ስለ ወቅታዊው የኢትዮጵያ እና ሱማሊያ ግንኙነት ጉዳይ እንዲሁም ስለ ሱዳን ጦርነት ነው።

ከኢጋድ አባል ሀገራት የትኞቹ መሪዎች ተገኙ ?

🇩🇯 የጅቡቲ ፕሬዜዳንት ኢማኤል ኦማር ጌሌህ (ስብሰባውን የመሩት እሳቸው ናቸው/ የወቅቱ የኢጋድ ሊቀመንበር ናቸው)
🇰🇪 የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ
🇸🇴 የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ
🇸🇸 የደቡብ ሱዳን ፕሬዜዳንት ሳልቫኪየር ማያርዲት
🇺🇬 የኡጋንዳ ፕሬዜዳንት ዩዌሪ ካጉታ ሙሴቬኒ ተገኝተው ነበር።

ሌሎችስ እነማን ተገኙ ?

- የኢጋድ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ፤
- የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሃማት
- የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ የሱዳን የግል መልዕክተኛ ራምታኔ ላምራ፣
- የሳውዲ አረቢያ መንግሥት ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሌድ አልኩራጂ
- የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች / #UAE የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ካሊፋ ሻሂን አል ማራርት
- የአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አኔታ ዌበር፤
- #የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር፤
- የአረብ ሀገራት ሊግ ረዳት ዋና ፀሀፊ ሆሳም ዛኪ
- የኢጋድ ምክትል ሥራ አስፈፃሚ መሐመድ አብዲ ዋሬ
- የደቡብ ሱዳን የኢጋድ ልዩ መልዕክተኛ እና የሱዳን የሰላም ሂደት የኢጋድ ተወካይ አምባሳደር እስማኤል ዋይስ
- የኢጋድ የቀይ ባህር፣ የኤደን ባህረ ሰላጤ እና የሶማሊያ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር መሀመድ አሊ ጉዮ
- #በቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የምስራቅ አፍሪካ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ቱትኩ ኢናም
- የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ቺክ ኮንዴ ተገኝተው ነበር።

ኢጋድ ከስብሰባው በኃላ ባወጣው መግለጫ ምን አለ ?

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ግኙነት መካከል የተፈጠረው ሁኔታ በእጅጉ እንደሚያሳስበው ገልጿል።

በዋነኛ መርህነት የሶማሊያ ሉዓላዊነት ፣ አድነት እና የግዛት አንድነት ሊከበር ይገባል ሲል አረጋግጧል። ማንኛውም ተሳትፎ ይህንን መርህ ባከበረ መልኩ ሊሆን ይገባል ብሏል። ማንኛውም #ስምምነት ወይም #ዝግጅት በሶማሊያ ፌዴራላዊ መንግስት #ፈቃድ መሆን አለበት ብሏል።

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በመካከላቸው ያለውን ውጥረት በማርገብ በምትኩ ገንቢ የሆነ ውይይት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።

ኢትዮጵያ ስብሰባው ላይ ለምን አልተገኘችም ?

ኢትዮጵያ ከዛሬው የአስቸኳይ ስብሰባ ቀደም ብላ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል " በተደራራቢ መርሃ ግብር " ምክንያት በዚህ ስብሰባ ላይ መገኘት እንዳማትችል ለጂቡቲ የውጭ ጉዳይና አለም አቀፍ ትብብር እና ኢጋድ በድብዳቤ አሳውቃለች።

ኢጋድ ከጠራው ጉባኤ ቀደም በሎ ከተያዘ መርሃ ግብር ጋር የሚጋጭ በመሆኑ እና የተቀመጠውም ጊዜ አጭር በመሆኑ በስብሰባው ላይ መገኘት እንደሚያስቸግራት በዚሁ ደብዳቤ አሳውቃ ነበር።

ነገር ግን " ኢጋድ በሚመራበት ደንብ መሰረት " በተለዋጭ ቀን ለመወያየት ዝግጁ መሆኗን አሳውቃቸዋለች።

(ሙሉ የኢጋድ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ የመግባቢያ ስምምነት ከምን ደረሰ ? " ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታገኝ መንገድ ይጠርጋል " የተባለው የመግባቢያ ስምምነት ከሶማሌለንድ ጋር ከተፈረመ ትላንት 1 ወር አልፎታል። የመግባቢያ ስምምነቱ እኤአ ጥር 1 ነበር የተፈረመው። ይህ ስምምነት በተፈረመበት ወቅት በመንግሥት ባለስልጣናት በኩል በተሰጡ ገለፃዎች ፦ * በ1 ወር ውስጥ የስምምነቱ ዝርዝር ይፋ እንደሚደረግ፤…
" ... ኢትዮጵያ ጎረቤታችን ናት፤ ከእነሱ ጋር ቢዝነስ መስራት እንፈልጋለን " - ሰኢድ ሀሰን አቡዱለሂ

የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች / #UAE / ንብረት የሆነው ' ዲፒ ወርልድ ኩባንያ ' የሚያስተዳድረው የበርበራ ወደብ የኢትዮጵያን 30 በመቶ ጭነት እንዲያስተናግድ የሶማሌላንድ ባለስልጣናት ማቀዳቸው ተሰምቷል።

ለዚህ የወደብ አጠቃቀምና የጉምሩክ ሥርዓቶችን የተመለከተ ስምምነት በኢትዮጵያና ሶማሌላንድ መካከል መፈረም አለበት።

ስምምነቱ ወደ መጨረሻውው ምዕራፍ መድረሱንና በሚቀጥሉት 60 ቀናት ተጠናቆ ሊፈረም እንደሚችል የሶማሌላንድ የወደቦች አስተዳደር አሳውቋል።

የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ሰኢድ ሀሰን አቡዱለሂ ፥ " ኢትዮጵያ ጎረቤታችን ናት፤ ከእነሱ ጋር ቢዝነስ መስራት እንፈልጋለን በአሁን ወቅት የወደብ አጠቃቀም ስምምነት ወይም Transit Agreement እያዘጋጀን ነው። አንዴ ስምምነቱን ከተፈራረምን በመጀመሪያው ዓመት ከኢትዮጵያ ጭነት 30% እናስተናግዳለን " ብለዋል።

ይህን በተመለከተ " ስምምነቱ እየተጠናቀቀ መሆኑን ገልጸው በአንድ ወይም ሁለት ቀሪ ጉዳዮች ላይ እየተወያየን ነው ምናልባት በመጪዎቹ 60 ቀናት ሊጠናቀቅ ይችላል ከ60 ቀናት በኃላ እንፈራረማለን " ሲሉ ተደምጠዋል።

ከወራት በፊት እ.አ.አ ጥር 1 ላይ ኢትዮጵያ እና ሶማሌላድ የተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነት (MoU) በተመሳሳይ ወደ ተግባር የሚገባበት የመጨረሻው ስምምነት በ2 ወራት ገደማ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የሶማሌላንድ ባለስልጣናት ገልጸዋል።

መግባቢያ ምምነቱ ከተፈረመ በኋላ ውይይቶች ሲደረጉ የቆዩ ሲሆን የቴክኒክ ኮሚቴዎችም መታጨታቸውን ተናግረዋል።

ይህ የመግባቢያ ስምምነት ወደ #መጨረሻው ደርሶ ወደ ተግባር ከገባ ኢትዮጵያ በሶማሌላንድ የባህር ዳርቻ የጦር ሰፈር በሊዝ ኪራይ የምታገኝ ሲሆን ሶማሌላንድ በበኩሏ ለረጅም አመታት ስትፈልገው የነበረውን እውቃና የማግኘት እድል እንደሚፈጥርላት ባለስልጣናቱ አመልክተዋል።

ለንግድ ስራ ሌላ ወደብ መገንባት ሳያስፈልግ የበርበራ ወደብን ኢትዮጵያ እንደምትጠቀምበት ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia
#Ethiopia #UAE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ማዕከላዊ ባንክ የተፈራረሙት ስምምነት ምንድነው ?

1ኛ. በኢትዮጵያ ብር እና የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ (UAE) ድርሀም መካከል የምንዛሬ ልውውጥ ለማድረግ ተስማምተዋል።

ይህ ስምምነት 46 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር እና 3 ቢሊዮን UAE ድርሃም በማዕከላዊ ባንክ በኩል ለመቀያየር / ለመለዋወጥ ያመቻችላቸዋል።

ዓላማው ፦
° በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የፋይናንስ እና የንግድ ትብብርን ለመደገፍ ነው።
° ድንበር ተሻጋሪ ግብይቶችን የበለጠ ውጤታማ እና ቀልጣፋ ለማድረግ ነው።

2ኛ. ኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ/UAE በራሳቸው ገንዘብ (በብር እና ድርሃም) ለመገበያየት የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ተፈራርመዋል።

ዓላማው ፦
° የንግድ ልውውጦችን በራሳቸው (በሁለቱ ሀገራት ገንዘብ) ለማድረግ ምቹ ሁኔታዎችን ይፈጥራል።
° የፋይናንስ እና የባንክ ትብብርን ያጠናክራል።
° የፋይናንስ ገበያዎችን ያዳብራል።
° የሁለትዮሽ ንግድን ያመቻቻል።
° የቀጥታ ኢንቨስትመንት ያበረታታል።
° የሙያ እና መረጃ ልውውጥ እንዲኖር ያመቻቻል።

3ኛ. የክፍያ እና የመልዕክት መለዋወጫ ስርዓቶችን ለማገናኘት የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ተፈራርመዋል።

ዓላማው ፦
° ድንበር ተሻጋሪ የገንዘብ ልውውጦችን ውጤታማነት ያሳድጋል።
° በፋይናንሺያል ቴክኖሎጂ እና በማዕከላዊ ባንኮች ዲጂታል ምንዛሬዎች ላይ ትብብር እንዲደረግ ይረዳል።
° በክፍያ መድረክ አገልግሎቶችና በኤሌክትሮኒክ ስዊች በኩል ትብብር ያደርጋሉ። በክፍያ ስርዓቶቻቸው በኩል ኢቲስዊች እና ዩኤኢስዊች እንዲሁም በመልእክት መላላኪያ ስርዓቶች በሀገራቱ የቁጥጥር መስፈርቶች በማገናኘት ትብብር ያደርጋሉ።

የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ (UAE) በአሁን ሰዓት ጠንካራ ከሚባሉ የኢትዮጵያ ወዳጅ ሀገር አንዷ ናት።

ሁለቱም የ #BRICS+ አባል ሀገራት እንደሆኑም ይታወቃል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ያሰባሰበው ከብሔራዊ ባንክ እና ከተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ማዕከላዊ ባንክ ነው።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዶላር ዛሬ ከሰዓት ጨምሯል። በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጥዋት የነበረው የዶላር ዋጋ ዛሬ ከሰዓት ጨምሯል። ባንኩ አንዱን ዶላር በ80 ብር ከ0203 ሳንቲም እየገዛ በ81 ብር ከ6207 ሳንቲም እየሸጠ ነው። በተመሳሳይ ፓውንድ ስተርሊንግም ጨምሯል። አንዱን ፓውንድ ስተርሊንግ በ97 ብር ከ8436 ሳንቲም እየገዛ በ99 ብር 8005 እየሸጠ ነው። ዩሮ 86 ብር ከ5019 ሳንቲም እየገዛ በ88 ብር ከ2320…
#ዕለታዊ : የጠዋቱ እና የከሰዓቱ የምንዛሬ ለውጥ ምን ይመስላል ? (በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)

💵 የአሜሪካ ዶላር !

➡️ ጠዋት ፦ 1 ዶላር መግዣው 77 ብር ከ1280 ሳንቲም ፤ መሸጫው 78 ብር ከ6706 ሳንቲም ነበር።

➡️ ከሰዓት ፦ 1 ዶላር መግዣው 80 ብር ከ0203 ሳንቲም ፤ መሸጫው 81 ብር ከ6207 ሳንቲም ሆኗል።

💷 ፓውንድ ስተርሊንግ !

➡️ ጠዋት ፦ 1 ፓውንድ ስተርሊንግ መግዣው 94 ብር ከ3071 ሳንቲም ፤ መሸጫው 96 ብር ከ1932 ሳንቲም ነበር።

➡️ ከሰዓት ፦ 1 ፓውንድ ስተርሊንግ መግዣው 97 ብር ከ8436 ሳንቲም መሸጫው 99 ብር ከ8005 ሳንቲም ሆኗል።

💶 ዩሮ !

➡️ ጠዋት ፦ 1 ዩሮ መግዣው 83 ብር ከ3754 ሳንቲም መሸጫው 85 ብር ከ0429 ሳንቲም ነበር።

➡️ ከሰዓት ፦ 1 ዩሮ መግዣው 86 ብር ከ5019 ሳንቲም መሸጫው 88 ብር ከ2320 ሳንቲም ሆኗል።

#UAE ድርሃም !

➡️ ጠዋት ፦ 1 ድርሃም መግዣው 18 ብር ከ7954 ሳንቲም ፤ መሸጫው 19 ብር ከ1713 ሳንቲም ነበር።

➡️ ከሰዓት ፦ 1 ድርሃም መግዣው 19 ብር ከ5002 ሳንቲም ፤ መሸጫው 19 ብር ከ8902 ሳንቲም ሆኗል።

የውጭ ምንዛሬ በገበያው መወሰን / Floating exchange rate / የሚባለው ይኸው ነው። የውጭ ምንዛሬው በፍጥነት መለዋወጥ የሚታይበት ነው።


#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia