TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አቢሲንያ_ባንክ

2ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ታህሳስ 4 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎች በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ በየሳምንቱ አምስት አምስት አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!

ሊንክ፡ https://t.me/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#አቢሲንያ_ባንክ

ለጥያቄና መልስ ውድድራችን ዝግጁ ነዎት?
3ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ታህሳስ 11 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎች በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ በየሳምንቱ አምስት አምስት አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!
https://t.me/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#አቢሲንያ_ባንክ

ለጥያቄና መልስ ውድድራችን ዝግጁ ነዎት?
4ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ታህሳስ 18 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎችን በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ ከ4ኛ ዙር ጀምሮ ባሉት ውድድሮች አስር አስር አሸናፊዎች በየሳምንቱ ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!

https://t.me/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#አቢሲንያ_ባንክ

የገና ስጦታ!
ለጥያቄና መልስ ውድድራችን ዝግጁ ነዎት?
5ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ታህሳስ 25 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎችን በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ ከ4ኛ ዙር ጀምሮ ባሉት ውድድሮች አስር አስር አሸናፊዎች በየሳምንቱ ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ፡ https://t.me/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#አቢሲንያ_ባንክ

ለጥያቄና መልስ ውድድራችን ዝግጁ ነዎት?
7ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ጥር 9 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎች በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ በየሳምንቱ አምስት አምስት አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#አቢሲንያ_ባንክ

ለጥያቄና መልስ ውድድራችን ዝግጁ ነዎት?
7ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ጥር 9 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎች በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ በየሳምንቱ አምስት አምስት አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#Telegram

ቴሌግራም በሰዓታት ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አዳዲስ ተጠቃሚዎች አገኘ።

ዓለም ላይ ለሰዓታት ፌስቡክ እና ኢንስታግራም መቋረጣቸውን ተከትሎ " ቴሌግራም "ን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች መቀላቀላቸውን የቴሌግራም መስራች እና ዋና ስራ አስፈፃሚ ፓቨል ዱሮቭ ገለጹ።

ዋና ስራ አስፈፃሚው ፤ " ኢንስታግራም እና ፌስቡክ በተቋረጡበት ባለፉት ሰአታት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ቴሌግራም ላይ ሲመዘገቡ እና ይዘቶችን ሲያጋሩ ቆይተዋል " ብለዋል።

" ቴሌግራም " ከእነዚህ አገልግሎቶች የበለጠ አስተማማኝ ነው ሲሉም አክለዋል።

" ምንም እንኳን ከሜታ አንድ ሺህ ጊዜ ያነሱ ቋሚ የሆኑ ሰራተኞች ቢኖሩንም በመተግበሪያው ላይ አዳዲስ ይዘቶችን ለማሻሻል እና አዳዲስ ፈጠራዎችን ለማከል ፈጣኖች ነን " ብለዋል።

ዋና ስራ አስፈፃሚው ፤ " በ2023 ሙሉ ከዓመቱ 525,600 ደቂቃዎች ውስጥ የቴሌግራምን አገልግሎት ማግኘት ያልተቻለው በአጠቃላይ ለ9 ደቂቃ ብቻ ነው " ያሉ ሲሆን " ይህም 99.999983% ቴሌግራም ስራ ላይ እንደነበር አመላካች ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

በቅርቡ በቴሌግራም ቻናላችን በየሳምንቱ የአንድ አመት የቴሌግራም ፕሪምየም የሚያስገኝ ውድድር የምንጀምር ሲሆን የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል እና የምንጠይቃቸውን ቀላል ጥያቄዎች በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ በየሳምንቱ አስር አሸናፊዎች ይሸለማሉ!
ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ፡ https://t.me/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#አቢሲንያ_ባንክ

የጥያቄና መልስ ውድድር ቅዳሜ ሰኔ 15 ከረፋዱ 4:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ በየሳምንቱ አስር አስር አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ቴሌግራም ፕሪምየምን ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ፡ https://t.me/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#አቢሲንያ_ባንክ

የጥያቄና መልስ ውድድር ቅዳሜ ሰኔ 22 ከረፋዱ 4:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ በየሳምንቱ አስር አስር አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ቴሌግራም ፕሪምየምን ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ፡ https://t.me/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#አቢሲንያ_ባንክ

የጥያቄና መልስ ውድድር ቅዳሜ ሰኔ 22 ከረፋዱ 4:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ በየሳምንቱ አስር አስር አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ቴሌግራም ፕሪምየምን ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ፡ https://t.me/BoAEth


#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#Telegram

የቴሌግራም መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ፓቨል ዱሮቭ ፈረንሳይ ውስጥ ታሰረ።

በፈረንሳይ የሩስያ ኤምባሲ የዱሮቭን ሁኔታ በቅርብ እየተከታተለ ነው።

ዱሮቭ ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባል።

ብሎገሮች በፈረንሳይ ኤምባሲዎች የተቃውሞ ሰልፍ እየጠሩ ናቸው።


የቴሌግራም መተግበሪያ መስራቹና ዋና ስራ አስኪያጁ ፓቨል ዱሮቭ ትላንት ቅዳሜ ምሽት ፈረንሳይ ፣ በፈረንሳይ ከፓሪስ ወጣ ብሎ በሚገኘው ቡርጌት ኤርፖርት በቁጥጥር ስር ውሏል።

ዱሮቭ በግል ጄቱ ተሳፍሮ ሊጓዝ ሲል ነው የታሰረው።

ለእረፍት ካቀናበት አዘርባጃን ተነስቶ በፈረንሳይ አድርጎ ሊጓዝ በኤርፖርቱ ባረፈበት ወቅት ነው መያዙ የታወቀው።

በፈረንሳይ የመጀመሪያ ደረጃ የፖሊስ ምርመራ አካል በሆነ የእስር ማዘዣ እንደተያዘም ነው የተነገረው።

ምርመራው ያተኮረው በቴሌግራም ሞደሬት / ቁጥጥር የማድረግ ክፍተት ላይ ነው። የፈረንሳይ ፖሊስ " ቴሌግራም የወንጀል ድርጊቶች፣ የአደገኛ እፅ ዝውውር፣ ሽብር፣ መኒ ላውንደሪንግ፣ ማጭበርበር ያለገደብ የሚተለለፉበት ሆኗል " በሚል ምርመራ ያደርጋል ነው የተባለው።

ዱሮቭ ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባል ተብሏል።

ቴሌግራም በጉዳዩ ላይ እስካሁን ያለው ነገር የለም። የፈረንሳይ የውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ፖሊስም በጉዳዩ ላይ ምንም አላሉም።

የሩስያ ምክትል የዱማ አፈ-ጉባዔ ቭላዲላቭ ዳቫንኮቭ ዱሮቭ እንዲፈታ የሚጠይቅ መልዕክት ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ፅፈዋል።

እስራቱ በፖለቲካዊ ተነሳሽነት ያለውና የቴሌግራም ተጠቃሚዎችን ግላዊ መረጃ ለማግኘት መሳሪያ ሊሆን ይችላል ነው ያሉት።

በፈረንሳይ የሩስያ ኤምባሲ ጉዳዩን በቅርብ እየተከታተለ ነው።

ብሎገሮች በፈረንሳይ ኤምባሲዎች ተቃውሞ እየጠሩ ናቸው።

በርካቶች ቴሌግራም ላይ ያነጣጠረው የሃሳብ ነጻነትን መንፈግ ነው ብለዋል።

ቴሌግራም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተጠቃሚዎች እጅ በጣም መጨመራቸው ይታወቃል።

በተለይ በሩስያ፣ ዩክሬን አካባቢ እጅግ በርካታ ተጠቃሚዎች ያሉት ሲሆን በመላው ዓለም ተጠቃሚዎቹ 1 ቢሊዮን ደርሰዋል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በበርካታ የዓለም ሀገራት መሪዎች እና ባለስልጣናት ዋነኛ ተመራጭ የመልዕክት ማስተላለፊያ መድረክ ሆኗል።

ዱሮቭ የሩስያ-ፈረንሳይ ዜግነት አለው።

#TF1TV #BFM

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Telegram የቴሌግራም መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ፓቨል ዱሮቭ ፈረንሳይ ውስጥ ታሰረ። በፈረንሳይ የሩስያ ኤምባሲ የዱሮቭን ሁኔታ በቅርብ እየተከታተለ ነው። ዱሮቭ ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባል። ብሎገሮች በፈረንሳይ ኤምባሲዎች የተቃውሞ ሰልፍ እየጠሩ ናቸው። የቴሌግራም መተግበሪያ መስራቹና ዋና ስራ አስኪያጁ ፓቨል ዱሮቭ ትላንት ቅዳሜ ምሽት ፈረንሳይ ፣ በፈረንሳይ ከፓሪስ ወጣ ብሎ…
#Telegram : የቴሌግራም መስራች እና ዋናው ስራ አስኪያጅ ፓቨል ዱሮቭ ፍርድ ቤት ቀርቧል።

ፍርድ ቤት በ5 ሚሊዮን ዩሮ ወይም 5.56 ሚሊዮን ዶላር ዋስ ተለቆ ጉዳዩን እንዲከታተል ወስኖለታል።

ከፈረንሳይ እንዳይወጣ ግን ታግዷል።

እገዳው ተጨማሪ ምርመራ ስለሚደረግ ነው የተጣለው።

በሳምንት ሁለት ጊዜ ለፖሊስ ሪፖርት ማድረግ እንዳለበት ተገልጿል።

ዱሮቭ ከቀናት በፊት ፓሪስ አቅራቢያ ኤርፖት ተይዞ ከታሰረ በኃላ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ቆይቶ ነበር። ከዚህ በላይ በህጉ ማቆየት ስለማይቻል ከማቆያ ወጥቶ በፍርድ ቤት ጉዳዩ ታይቷል።

ፍርድ ቤቱም ከፈረንሳይ እንዳይወጣ በማገድ የ5 ሚሊዮን ዩሮ ዋስትና ፈቅዶለታል።

የፈረንሳይ መንግስት ዱሮቭ ላይ ምርመራ የከፈተው በቴሌግራም ፦
- ሞደሬት የማድረግ / ቁጥጥር የማድረግ ክፍተት አለ፣
- ለባለስልጣናት አስፈላጊ መረጃ አይሰጥም
- የወንጀል ድርጊቶች ይፈጸምበታል፣
- የአደገኛ እፅ ዝውውር ይከናወንበታል
- ሽብር፣ መኒ ላውንደሪንግ ይሰራበታል በሚል ነው።

ቴሌግራም ወደ 1 ቢሊዮን ተጠቃሚዎች ያሉት ሲሆን በነጻነቱና ደህንነቱ በተጠበቀ የመልዕክት እና መረጃ ልውውጥ በብዙዎች ዘንድ እጅግ ተመራጭ ነው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Telegram : የቴሌግራም መስራች እና ዋናው ስራ አስኪያጅ ፓቨል ዱሮቭ ፍርድ ቤት ቀርቧል። ፍርድ ቤት በ5 ሚሊዮን ዩሮ ወይም 5.56 ሚሊዮን ዶላር ዋስ ተለቆ ጉዳዩን እንዲከታተል ወስኖለታል። ከፈረንሳይ እንዳይወጣ ግን ታግዷል። እገዳው ተጨማሪ ምርመራ ስለሚደረግ ነው የተጣለው። በሳምንት ሁለት ጊዜ ለፖሊስ ሪፖርት ማድረግ እንዳለበት ተገልጿል። ዱሮቭ ከቀናት በፊት ፓሪስ አቅራቢያ ኤርፖት ተይዞ…
#Telegram

የቴሌግራም መስራች እና ዋና ስራ አስፈጻሚ ፓቨል ድሮቭ ፓሪስ ውስጥ ታስሮ በዋስ ከተለቀቀ በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋዊ አስተያየት ሰጥቷል።

ዱሮቭ ምን አለ ?

አብረውት ለነበሩትና ለደገፉትና ፍቅራቸውን ላሳዩት ሁሉ ምስጋና አቅርቧል።

ባለፈው ወር ፓሪስ በደረሰ ወቅት 4 ጊዜ በፖሊስ ኢንተርቪው ተደርጎ እንደነበር ገልጿል።

በዚህ ወቅት የፈረንሳይ ባለስልጣናት ከቴሌግራም ምላሾችን ስላላገኙ ምናልባትም ለሌሎች ሰዎች ህገወጥ የቴሌግራም አጠቃቀም በግል ዱሮቭ ተጠያቂ እንደሚሆን እንደተነገረው አመልክቷል።

ይህ ግን በብዙ ምክንያቶች አስገራሚ እንደነበር አስረድቷል።

- ቴሌግራም የአውሮፓ ህብረት ጥያቄዎችን የሚቀበል እና የሚመልስ በአውሮፓ ህብረት ውስጥ ኦፊሴላዊ ተወካይ አለው። ይፋዊ ኢሜልም አለው።

- የፈረንሳይ ባለስልጣናት እርዳታ ለመጠየቅ ዱሮቭን ለማግኘት ብዙ መንገዶች ነበሯቸው። እንደ አንድ የፈረንሳይ ዜጋ በዱባይ በሚገኘው የፈረንሳይ ቆንስላ ተደጋጋሚ እንግዳም ነበር። ከጥቂት ጊዜ በፊት ደግሞ በግሉ በፈረንሳይ ያለውን የሽብርተኝነት ስጋት ለማስወገድ ከቴሌግራም ጋር የስልክ መስመር እንዲፈጥሩ ረድቷቸዋል።

- አንድ ሀገር በኢንተርኔት አገልግሎት ላይ ደስተኛ ካልሆነ በራሱ በአገልግሎቱ ላይ ህጋዊ እርምጃ መጀመር ነው። ከቅድመ ስማርት ስልክ በፊት የነበረ ህግ አምጥቶ በመተግበሪያው ላይ በሶስተኛ ወገኖች ለሚሰራ ወንጀል የድርጅት ስራ አስፈጻሚን ተጠያቂ ማደረግ ትክክለኛ አካሄድ አይደለም። ቴክኖሎጂን መገንባት በራሱ ከባድ ነገር ነው። ማንም ኢኖቬተር ሌሎች አላግባብ ለሚጠቀሙት አጠቃቀም እሱ በግሉ እንደሚጠየቅ ካወቀ አዲስ ነገር አይፈጥርም።

በግላዊ መረጃ እና በደህንነት መካከል ትክክለኛውን ሚዛን መፍጠር እንዲሁ ቀላል እንዳልሆነ ዱሮቭ ገልጿል።

አንዳንድ ጊዜ ይህን ሚዛን በመጠበቅ ጉዳይ ከሀገራት ተቆጣጣሪዎች ጋር መግባባት ሳይፈጠር ሲቀር ቴሌግራም ሀገራቱን ለቆ እንደሚወጣ አመልክቷል። ይህንን ብዙ ጊዜ እንዳደረገ ገልጿል።

ለአብነት ፦ ሩስያ ለስለላ " የኢንክሪፕሽን ቁልፎችን " መጠየቋን ተከክሎ ቴሌግራም አልሰጥም በማለቱ ሩስያ ውስጥ ቴሌግራም ታግዷል።

ኢራን የሰላማዊ ሰልፎችን ቻናሎች ብሎክ እንዲደረግላት ጠይቃ ቴሌግራም " አላደርገውም አይቻልም " በማለቱ ኢራን ውስጥ ታግዷል።

ዱሮቭ ምስራዎች የሚሰሩት ለገንዘብ ባለመሆነ ከቴሌግራም መርህ ጋር የማይሄድን ገበያ ለቆ ለመውጣት ሁሌም ዝግጁ እንደሆነ ገልጿል።

ይህ ሁሉ ማለት ግን ቴሌግራም ፍጹም ነው ማለት እንዳልሆነ ዱሮቭ አመልክቷል።

የመንግሥት አካላት / ባለስልጣናት ጥያቄያቸውን የት መላክ እንዳለባቸው ግራ ይግባሉ ይህንን ማስተካከል አለብን ብሏል።

ነገር ግን በአንዳንድ ሚዲያዎች ቴሌግራም የስርዓት አልበኞች መፈንጫ ተደርጎ የሚቀርበው ፍጹም ሀሰተኛ ነው ሲል ገልጿል።

" በየቀኑ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ጎጂ ፖስቶችን እና ቻናሎችን እናስወግዳለን " ያለው ዱሮቭ በየዕለቱ ግልጽነት መፍጠሪያ ሪፖርቶችም እንልካለን ብሏል።

መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች (NGOs) ጋር አስቸኳይ የሞደሬሽን ጥያቄዎችን በፍጥነት ለማስተናገድም የቀጥታ ስልክ መስመሮችም አሉን ሲል አክሏል።

" ሆኖም ግን ይህ በቂ አይደለም የሚሉ ድምፆችን እንሰማለን " ያለው ዱሮቭ " የተጠቃሚዎች ብዛት ወደ 950 ሚሊዮን መድረስ ወንጀለኞች የእኛን መድረክ አላግባብ ለመጠቀም ቀላል አድርጎላቸዋል። በዚህ ረገድ ያሉ ነገሮችን በከፍተኛ ሁኔታ ማሻሻል የግል ግቤ አድርጊያለሁ " ብሏል።

ይህ ሂደት በውስጥ በኩል መጀመሩን ጠቁሞ በቀጣይ ስላለው ሁኔታ ተጨማሪ ዝርዝር ጉዳዮች በቅርቡ ይፋ እንደሚደረጉ አሳውቋል።

ያለፈው ወር ክስተት ቴሌግራም እና የማህበራዊ አውታረመረብ ኢንዱስትሪን በጠቅላላ ደህንነቱ የተጠበቀና ጠንካራ እንደሚያደርገው ተስፋ እንዳለው ዱሮቭ ገልጿል።

#TikvahEthiopia
#Telegram

@tikvahethiopia
#Telegram

" አዲሱ ደንብ መተግበሪያውን ለወንጀል የሚጠቀሙት ሰዎችን ቅስም የሚሰብር ይሆናል " - ዱሮቭ

ቴሌግራም አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ የደንበኞቹን መረጃዎች ለሕግ አካላት አሳልፎ ሊሰጥ ነው።

በዚህም የቴሌግራም ተጠቃሚዎች ፦
➡️ ስልክ ቁጥሮች፣
➡️ የኢንተርኔት አድራሻ
➡️ ሌሎችንም መረጃዎች በፖሊስ፣ በፍርድ ቤት በመሳሰሉ የሕግ ተርጓሚዎች በሚፈለግበት ጊዜ ሊሰጥ እንደሚችል ቴሌግራም አሳውቋል።

የቴሌግራም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፔቨል ዱሮቭ ይህ አዲስ ደንብ እንደሆነው አመልክተዋል።

ይህ አዲስ ደንብ " መተግበሪያውን ለወንጀል የሚጠቀሙት ሰዎችን ቅስም የሚሰብር ይሆናል " ብለዋል።

" 99.999% የቴሌግራም ተጠቃሚዎች ከወንጀል ጋር የሚያያይዛቸው አንዳችም ነገር የለም። 0.001% የሚሆኑት ግን ለድብቅ ወንጀል እየተጠቀሙበት የቴሌግራምን ዝና እና ክብርን እያጎደፉት ይገኛሉ። ይህ ደግሞ ቢሊዮን የሚጠጉ ጨዋ ተጠቃሚዎቻችን የሚጎዳ ነው " ብለዋል።

ዱሮቭ ባለፈው ወር በፈረንሳይ ፣ ፓሪስ ኤርፖርት በቁጥጥር ሥር ውለው እንደነበር አይዘነጋም።

በፖሊስ ከተያዙ በኋላ የቀረበባቸው ክስ " መተግበሪያው ለወንጀለኞች መፈንጫ እንዲሆን ፈቅደዋል " የሚል ነበር።

" ሕገ ወጥ የሕጻናት ምስሎች ዝውውርና የአደገኛ እጽ አዘዋዋሪዎችን በሚያበረታታ መልኩ መተግበሪያው ለወንጀል ተግባር እንዲውል ፈቅደዋል " በሚል የተከሰሱት ዱሮቭ ከሕግ አካላት ጋር ባለመተባበርም ተወንጅለው ነበር።

ዋና ሥራ አስፈጻሚው በበኩላቸው ሌሎች ለፈጸሙት ወንጀል እሳቸው ተከሳሽ መሆናቸው " አስደናቂ እና ግራ የሚያጋባ " ነገር ነው ሲሉ የፈረንሳይ ባለሥልጣናትን ወርፈው ነበር።

በኃላ ፍ/ቤት ዱሮቭ በዋስ ወጥተው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ማዘዙ ይታወሳል።

#Telegram #BBC

@tikvahethiopia