TIKVAH-ETHIOPIA
1.42M subscribers
55.2K photos
1.38K videos
199 files
3.7K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመጪው #ሰኔ_ወር 2016 ዓ/ም ወደ ሁለት የሀገር ውስጥ የበረራ መዳረሻዎች በረራ ይጀምራል። አየር መንገዱ #ከሰኔ_10_ጀምሮ ወደ ወለጋ ፣ ነቀምቴ በረራ እንደሚጀምር አሳውቋል። በረራው በሳምንት 4 ጊዜ እንደሚካሄድ ተገልጿል። ከዚህም ባለፈ ፥ በትግራይ ጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የቆየው ወደ አክሱም የሚደረገው በረራ ከሰኔ 1 ጀምሮ ዳግም እንደሚጀምር ታውቋል።…
ፎቶ ፦ የአክሱም አፄ  ዮውሀንስ አራተኛ  ኤርፖርት #በተያዘለት_የጊዜ_ሰሌዳ አገልግሎት መስጠት እንዲጀመር የሚያስችሉት የጥገና ስራዎች አሁን ላይ ወደመጠናቀቁ መሆናቸው ተነግሯል።

በትግራይ ጦርነት ከፍተኛ የሆነ ጉዳት የደረሰበት ኤርፖርቱ የጥገና ስራው ቀን እና ሌሊት እየተሰራ ነበር።

የጥገና ተቆጣጣሪ አካል የአውሮፕላን ማረፍያው የሚገባውን ጥራት በያዘ ደረጃ ስራው እየተሰራ መሆኑን ጠቁሟል።

በረራው እንዲጀመር በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ በረራው እንዲጀመር የማጠናቀቅ ስራ እየተሰራ እንደሆነ ገልጿል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሰኔ 1 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ ወደ አክሱም መደበኛ በረራ እንደሚጀመር ማሳወቁ ይታወሳል።

#Ethiopia #Tigray #Axum

Photo Credit - Tigray TV

@tikvahethiopia            
20 % ተጨማሪ የገንዘብ ስጦታ + የዕድል ጨዋታ!

በአጋሮቻችን በኩል ባሕር ማዶ ከሚኖሩ ወዳጅ ዘመዶችዎ የተላከልዎትን ገንዘብ በቀጥታ በቴሌብር ዓለም አቀፍ ሃዋላ ሲቀበሉ 20% ተጨማሪ የገንዘብ ስጦታ እና የአየር ሰዓት የሚያሸልም የዕድል ጨዋታ ውስጥ ይካተታሉ፡፡

እስከ ሰኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም የሚቆይ!

ለበለጠ መረጃ ማስፈንጠሪያውን bit.ly/3ArwoEO ይጠቀሙ፡፡

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ፎቶ ⬆️ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ ደረጃ እያካሄደው የሚገኘውን የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት 3ኛ ቀን መርሀ ግብር ዛሬ አከናውኗል። ዛሬ በከተማ ደረጃ " #ታዋቂ ፣ #ተጽዕኖ_ፈጣሪ " ናቸው የተባሉ ግለሰቦች ተገኝተው በኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች ስለ ሂደቱ ገለጻ ተደርጎላቸዋል ተብሏል። በተመሳሳይ በተለየ ቦታ ላይ ከ112 ወረዳዎች ከ11 የህብረተሰብ የተወጣጡ ተሳታፊዎች በየማኅበረሰብ ክፍላቸውን…
#Update

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ ለ7 ቀናት ሲያደርገው የነበረውን የአጀንዳ ማሰባሰብ መርሐ ግብር ዛሬ አጠናቋል።

በማጠቃለያው መርሐ ግብር ላይ የተገኘው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዶ/ር ዮናስ አዳዬ የተለያዩ ጥያቄዎችን አቅርቧል።

Q. የ7ቱ ቀናት በአ/አ ደረጃ አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደትና ውጤቱ ምን ይመስላል ?

ዶ/ር ዮናስ አዳዬ ፦

“ ትኩረቱ የነበረው 3 ነጥቦች ላይ ነው።

የመጀመሪያው ትኩረት በቅንነት ፣ ያለአንዳች መከልከል ፣ ያለመሸማቀቅ ሕዝባችን እንዲወያይ ነበር።

ሁለተኛው ደግሞ የአካባቢን ሁኔታ መሠረት ያደረገ ከጀንዳ ማቅረብ ነበር። 

ሦስተኛው ተወካይ መምረጥ ነበር። በአጠቃላይ ሁሉም የተሳካ ነበር። ”

Q. በአ/አ ደረጃ የተሰበሰቡ አጀንዳዎች ምንድን ናቸው ? 

ዶክተር ዮናስ አዳዬ ፦

“ አጀንዳዎቹን በሙሉ ሰብስበን፣ ኮሚሽኑ ካጠናቀረ በኋላ እነዚህ የአዲስ አበባ እነዚህ የእነዛ ብሎ መናገር ይሻላል።

አሁን ባለበት ሁኔታ ግን መናገሩ አስፈላጊ አይደለም። ምክንያቱም ሌሎች የሚያስቡትን ማበላሸት ስለሚሆን። ”

Q. በአዲስ አበባ የተደረገው የተወካዮች መረጣ ከኃይማኖትና ፆታ ስብጥር አንፃር ምን ይመስላል ?

ዶክተር ዮናስ አዳዬ ፦

“ እኛ እስከገባን፣ እስካደረግነው ሥራችን ድረስ ፦
° ፆታን፣
° አካል ጉዳተኝነትን፣
° ሃይማኖትን
° የማህበረሰብ ክፍሎችንም፣ ሌላው ቀርቶ የብሔር ስብጥርን የወከለ ይመስላል።

ሴቶችን ለማካተት ተብሎ የታቀደው 30 በመቶ ነው።

በአገራችን የሴቶቻችን ብቃት ምን ያህል ነው? ምን ያህሉ ተማሩ ? በተለያዩ ዘርፎች ሴቶቻችን ብዙ አልተማሩም። ስለዚህ 50 በመቶ ብንል እንዋሻለን። ”

Q. ኢሕአፓ ከምክክሩ እንዳገለለ፣ ኦፌኮና ኦነግ በምክክሩ ዙሪያ ቅሬታ አላቸው። ከጅምሩ የሚስተዋሉ እንዲህ አይነት ተቃርኖዎች ምክክሩን አያደናቅፉትም ? ኮሚሽኑ ችግሩን ለመቅረፍ ምን እየሰራ ነው ? 

ዶክተር ዮናስ አዳዬ ፦

“ ስንጀምር ከ60 ፓርቲዎች አብረውን ለመስራት የተስማሙት 2 ወይም 3 ፓርቲዎች ነበሩ። አሁን ደግሞ የቀሩት 3 ወይም 4 ናቸው። 50 ፓርቲዎች ከእኛ ጋር እየሰሩ ነው።

ለምን ? ከተባለ አካሄዳችንን አይተዋል። አካታች፣ ለማንም ያልወገንን ግን ለኢትዮጵያ የወገን፣ ለእውነት የቆምን መሆናችንን ተገንዝበው መጥተዋል።

አሁንም #ለኦፌኮም #ለኦነግም ደብዳቤ ጽፈን ሰጥተናል እንዲመጡ። እና እነርሱ ባይመጡም ሌሎቹ አብረዋቸው የነበሩ እየመጡ እንዳሉ ማዬት ይቻላል።

እንደዚህ አይነት አለመግባባቶች ካሉ፣ ቢኖሩም ብዙም አይገርመንም። ምክክሩም ያስፈለገው እንዲህ አይነት መከፋፈል ስለነበረ ነው። ”

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
🇪🇹 #NationalDialogue 🇪🇹

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር  ፕ/ር መስፍን ዓርዓያ ፦
° እናት ፓርቲ ፣
° ኢሕአፓ ፣
° የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) እና የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ፓርቲዎች በምክክሩ ዙሪያ ቅሬታ አላቸው።

አንዳንዶቹ እኛ እየሰማን ያለነው በመገናኛ ብዙሃን ነው የሚሉ አሉ። በዚህ ጉዳይ ላይ እርሶ ምን ይላሉ ? ሲል ጠይቋል።

ፕ/ር መስፍን አርአያ ፦

“ በጣም የሚያደክሙ ጥሪዎች አድርገናል። በደብዳቤ ሳይቀር፣ ለኦነግ፣ ለኦፌኮ ለሁሉም ፓርቲዎች ጽፈናል።

የፓለቲካ ፓርቲዎች ከእኛ ጋር እንዳውም ውስጣችን ገብተው እየሰሩ ነው።

በእርግጥ በአሁኑ ሰዓት በአንዳንዶቹ የደረሱ ክስተቶች አሉ። እነዚህን ክስተቶች በጽሞና እያየናቸው ነው በአቅማችን።

እናት ፓርቲም መግለጫ አውጥተዋል ፤ አጀንዳዎቻቸውን ቀደም ብለው ሰጥተውናል።

እናም ያ ሀገራዊ ምክክሩ እስኪደርስ ድረስ መቼም ጥቂት ወራት መፍጀቱ አይቀርም። እነዛ ሁሉም ነገሮች በአምላክ ፈቃድ ይስተካከሉ ይሆናል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።

ወደ 50 የሚሆኑ ፓርቲዎች አብረውን እየሰሩ ነው። ሁሉንም እናካትታለን፤ ዝም ያሉትንም #ዱር ያሉትንም። ”

#NationalDialogue
#Ethiopia
#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የቤንዚን የችርቻሮ መሸጫ ላይ ጭማሪ ተደረገ። የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፤ ከግንቦት 1 ቀን 2016 ዓ/ም ለሊት 6፡00 ሰዓት ጀምሮ በስራ ላይ ያለው የነጭ ናፍጣ ፣ የኬሮሲን ፣ የአይሮፕላን ነዳጅ ፣ የቀላል ጥቁር ናፍጣና የከባድ ጥቁር ናፍጣ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ #ባለበት_እንደሚቀጥል አሳውቋል። በዚህ መሰረት ፦ - ነጭ ናፍጣ ብር 79.75 በሊትር - ኬሮሲን ብር 79.75 በሊትር…
#እንድታውቁት

ከነገ ግንቦት 28 /2016 ዓ/ም ጀምሮ የሁሉም የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በስራ ላይ በነበረበት ዋጋ እንዲቀጥል የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አሳውቋል።

ስራ ላይ ያለው የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ስንት ነው ?

- ቤንዚን ➡️ ብር 78.67 በሊትር
- ነጭ ናፍጣ ብር 79.75 በሊትር
- ኬሮሲን ብር 79.75 በሊትር
- የአውሮፕላን ነዳጅ ብር 70.83 በሊትር
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ ብር 62.36 በሊትር
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ ብር 61.16 በሊትር ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከተማ የአከራይ እና ተከራይ ህጋዊ ውል ምዝገባ ሰኔ 1 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚጀመር የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል።

የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ መጽደቁ ይታወቃል፡፡

በዚህም አስተዳደሩ አዋጁን በመመሪያ በማስደገፍ ወደ ስራ ለማስገባት ዝግጅቶቹን ማጠናቀቁ ተገልጿል።

ከሰኔ 1 እስከ 30 ቀን 2016 ዓ.ም በከተማዋ ውስጥ የሚገኙ የግል ቤት አከራዮች ከተከራዮቻቸው ጋር ህጋዊ ሰነዶቻቸውን ይዘው በመቅረብ ምዝገባ ማድረግ ይችላሉ ተብሏል።

ቤት አከራዮች ፦

➡️ ህጋዊ የምዝገባ ውል ለመፈጸም ወደ ወረዳ ጽ/ቤቶች በሚሄዱበት ወቅት ቤቱ የራሳቸው ስለመሆኑ ወይንም ህጋዊ ተወካይ መሆናቸውን የሚገልጽ ሰነድ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል።

ተከራዮች ፦

➡️ ማንነታቸውን የሚገልጽ #መታወቂያ ወይም ሌላ ህጋዊ ማንነታቸውን የሚያረጋግጥ ሰነድ ይዘው መቅረብ አለባቸው።

በስራ ሰዓት መመዘግብ የማይችሉ አከራይና ተከራዮች ቅዳሜና እሁድ እንዲሁም በስራ ቀን ማታ ከ12 ሰዓት በኋላ ህጋዊ የውል ምዝገባውን መፈጸም ይችላሉ።

#ENA
#Ethiopia
#AddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba በአዲስ አበባ ከተማ የአከራይ እና ተከራይ ህጋዊ ውል ምዝገባ ሰኔ 1 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚጀመር የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል። የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ መጽደቁ ይታወቃል፡፡ በዚህም አስተዳደሩ አዋጁን በመመሪያ በማስደገፍ ወደ ስራ ለማስገባት ዝግጅቶቹን ማጠናቀቁ ተገልጿል። ከሰኔ 1 እስከ 30 ቀን 2016 ዓ.ም በከተማዋ ውስጥ የሚገኙ…
#ማስታወሻ

" የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1320/2016 " ምን ይዟል ?

የመኖሪያ ቤት አከራዮች #በዘፈቀድ የኪራይ ዋጋ መጨመር #አይችሉም

አከራይ የኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው ተቆጣጣሪ አካል #በዓመት_አንድ_ጊዜ ነባራዊ የኢኮኖሚውን ሁኔታ እና ሌሎች አግባብነት ያላቸውን ጉዳዮች ከግምት በማስገባት ሊወስን የሚችለውን የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ መሠረት በማድረግ ነው።

ማንኛውም የቤት ኪራይ ጭማሪ በተቆጣጣሪው አካል በሰኔ 1 ለሕዝብ ይፋ ተደርጎ ከሰኔ 30 ጀምሮ ለአንድ አመት የፀና ይሆናል።

የቤት ኪራይ ውል ዘመን #ሳይጠናቀቅ ተከራይን ከቤት ማስወጣት ወይም በዚህ አዋጅ ከተፈቀደው ሁኔታ ውጪ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ አይቻልም። ይህም አስገዳጅ ድንጋጌ ነው።

አከራዮች #ከ2_ወር_የቤቱ_ኪራይ_በላይ ቅድመ ክፍያ መጠየቅ #አይችሉም

የቤት ኪራይ ክፍያዎች በባንክ ወይም በሌላ ሕጋዊ የኤሌክትሮኒክ ዘዴ መፈፀም አለባቸው። አከራይ እና ተከራይ የቤት ኪራይ ክፍያ ሰነዶችን አደራጅተው #የመያዝ_ግዴታ አለባቸው።

ማንኛውም የቤት ኪራይ ውል በጽሁፍ የሚደረግ ሆኖ በተቆጣጣሪው አካል መረጋገጥ እና መመዝገብ አለበት።

➡️ መኖሪያ ቤት ኪራይ ውል #ከሁለት_ዓመት ሊያንስ አይችልም።

NB. በአዋጁ መሠረት " ተቆጣጣሪው አካል ፣ ማለት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውልን እና ዋጋን እንዲቆጣጠር በክልሎች ወይም በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የሚሰየም አካል ነው፡፡

More : https://t.me/tikvahethiopia/86580?single

#Ethiopia
#የመኖሪያ_ቤት_ኪራይ_ቁጥጥርና_አስተዳደር_አዋጅ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቡሬ ➡️ “ 15 ተፈናቃዮች ናቸው በሚሊሻ የተወሰዱት ” - በአማራ ክልል የሚገኙ የወለጋ ተፈናቃዮች ➡️“ በቡሬ በኩል ስላለው መረጃ የለኝም ” - አቶ ኃይሉ አዱኛ በ2013 ዓ/ም ከኦሮማያ ክልል #ተፈናቅለው በአማራ ክልል ቡሬ ፣ ቻግኒ ፣ ፍኖተ ሰላም ፣ ባሕር ዳር የነበሩ ተፈናቃዮች ሰሞኑን ወደ ወለጋ ለመመለስ እየተጓዙ በነበረበት ወቅት ሰንቶም ቀበሌና ጣቦ የገጠር ከተማ ላይ ድንገተኛ ችግር…
#Update

“ 12 ሰዎች እስር ላይ ናቸው። 15 ቀናት አለፋቸው ፤ ምግብ አይገባላቸም ” - የታሳሪ ቤተሰቦች

ከወለጋ ተፈናቅለው በአማራ ክልል ፤ ቡሬ እና ሌሎች አካባቢዎች የነበሩ ተፈናቃዮች ወደ ወለጋ እየተመለሱ በነበረበት ወቅት “ ሰንቶም ” የሚባል ቦታ ሲደርሱ በሚሊሻ የተያዙ እንደነበሩ ከዚህ ቀደም ተዘግቦ ነበር።

አሁንስ የተያዙት ተፈናቃዮቹ ከምን ደረሱ ?

ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ በሰጡት ቃል፣ “ ያኔ ከመኪና አስወርደው ‘ቁጫ’ የሚባል ቦታ ላይ ለአንድ ሳምንት አሰሯቸው። በኋላም ከ‘ቁጫ’ ወደ ቡሬ አመጧቸው” ብለዋል።

የቡሬ አካላትን ሲጠይቁም ፥ “ ወደ አገራቸው ይሄዳሉ ብለን ላክናቸው መንገድ ላይ አስቀሯቸው። አሁን እዚህ አምጥተው አሰሯቸው። መከላከየ ነበር የያቸው ” እንዳሏቸው አስረድተዋል።

“ 12 ሰዎች በእስር ላይ ናቸው። 15 ቀናት አለፋቸው ፤ ምግብ አይገባላቸም። ገብቶ መጠየቅም አይቻልም ” ብለው፣ የሚመለከታቸው አካላት መፍትሄ እንዲያሰጧቸው ጠይቀዋል።

ተፈናቃዮቹ ለምን እንደታሰሩ እንዲሁም እንዲለቀቁስ ምን እየተሰራ እንደሆነ የጠየቅናቸው “ ተፈናቃዮቹን ፈርመው የላኩ ” የቡሬ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሃይማኖት ሥራ ላይ እንደሆኑ ገልጸው ስልክ ዘግተዋል።

ቆይት ብለው በላኩት የፅሑፍ መልዕክትም ፣ “ በጣም ይቅርታ የፀጥታ ስራ በመስራት ላይ ሆኘ ነው ” ያሉ ሲሆን፣ የማይመቼዎ ከሆነ ለቀረበው ጥያቄ የፅሑፍ ምላሽ ይስጡ ቢባሉም የሰጡት ቃል የለም።

ወደ ወረዳው የብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት እንዲሁም የኦሮሚያና አማራ ክልሎች ኮሚዩኒኬሽን ቢሮዎች ተጨማሪ ሙከራ ቢደረግም ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።

 #TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ የአክሱም አፄ  ዮውሀንስ አራተኛ  ኤርፖርት #በተያዘለት_የጊዜ_ሰሌዳ አገልግሎት መስጠት እንዲጀመር የሚያስችሉት የጥገና ስራዎች አሁን ላይ ወደመጠናቀቁ መሆናቸው ተነግሯል። በትግራይ ጦርነት ከፍተኛ የሆነ ጉዳት የደረሰበት ኤርፖርቱ የጥገና ስራው ቀን እና ሌሊት እየተሰራ ነበር። የጥገና ተቆጣጣሪ አካል የአውሮፕላን ማረፍያው የሚገባውን ጥራት በያዘ ደረጃ ስራው እየተሰራ መሆኑን ጠቁሟል። በረራው…
#Update #Axum

የአክሱም ኤርፓርት ሰኔ 2/2016 ዓ/ም ዳግም የበረራ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል። 

በትግራይ ጦርነት ከፍተኛ  የሆነ ጉዳት የደረሰበት የአክሱም አፄ ዮውሀንስ አራተኛ  ኤርፖርት ሰኔ 2 የመጀመሪያ ዳግም በረራውን ያደርጋል።

እሁድ ሰኔ 2 በኤርፓርቱ ዳግም መደበኛ የበረራ  አገልግሎት ስነ-ሰርዓት ማስጀመሪያ ጥሪ የተደረገላቸው የክልልና የፌደራል ባለስልጣናት እንደሚገኙ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአክሱም ከተማ ኮሙኒኬሽንና ህዝብ ግንኙነት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በሜክሲኮ በኩል ወደ አሜሪካ የሚገቡ ስደተኞችን ለመቆጣጠር ያለመ አዲስ እና መጠነ ሰፊ ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ ዛሬ ይፋ እንደሚያደርጉ ተነግሯል። ውሳኔው የአሜሪካ ኢሚግሬሽን ባለሥልጣናት በየዕለቱ ከሚመለከቱት በሕገ ወጥ መንገድ የገቡ ተጥገኝነት ጠያቂዎች ቁጥር በላይ አመልካቾች የሚቀርቡ ከሆነ ጥያቄያቸውን ሳይመለከቱ በቀጥታ ከአገር እንዲባረሩ ማድረግ የሚያስችል ሥልጣን…
#Update

የአሜሪካ ፕረዚደንት ጆ ባይደን በሜክሲኮ በኩል ወደ አገሪቱ የሚገቡ ስደተኞችን ለመቆጣጠር ሲባል የሀገሪቱን ፍልሰተኞች ሕግ አጥብቀዋል።

ይህ የጆ ባይደን ውሳኔ ባለሥልጣናት በሜክሲኮ በኩል ድንበር አቋርጠው የገቡ ስደተኞችን / ጥገኝነት ጠያቂዎችን በቀጥታ በኃይል ወይም በግዳጅ  እንዲመልሷቸው ሥልጣን የሚሰጥ ነው።

ጉዳያቸው የሚመዘገቡ ሰዎች ዕለታዊ ኮታ ከተሟላ የተቀሩት ከአሜሪካ በኃይል እንዲወጡ ይደረጋሉ።

ከዚህ ባለፈ ለአሜሪካ ብሔራዊ ጥቅም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ የውጪ ዜጋ ወደ አገር እንዳይገባ " #እንዲታገድ " የሚል ትዕዛዝ ፕሬዜዳንቱ አስተላልፈዋል።

#ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በርካታ አፍሪቃውያን በሜክሲኮ በኩል ወደ አሜሪካ እንደሚሻገሩ ይታወቃል።

አሜሪካ የፍልሰተኞችን ፍሰት ለመግታት በሚል ከሜክሲኮ የሚያዋስናትን ድንበር ከማጠር ጀምሮ በርካታ እርምጃዎችን ስትወስድ ቆይታለች።

ይህ የአሁኑ የፕሬዜዳንት ባይደን ውሳኔ ስደተኞች የጥገኝነት ጥያቄያቸው ለሚመለከተው የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት ቀርቦ ሳይታይ #በቀጥታ እንዲባረሩ የሚያደርግ ነው ተብሏል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፤ የስደተኞች ጉዳይ ኮሚሽን ግን ሕጉ የስደተኞችን መሰረታዊ መብት ይጥሳል ሲል ተቃውሟል።

መረጃው የጀርመን ዜና አገልግሎት፣ የዶቼ ቨለ እና ቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia
#StateofEmergency #EHRC

" በእስር የቆዩ ሰዎች ሊለቀቁ ይገባል " - ኢሰመኮ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (#ኢሰመኮ) ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አተገባበር ጋር በተያያዘ በእስር የቆዩ ሰዎች እንዲለቀቁ ጠየቀ።

በአማራ ክልል በመንግሥት እና በታጣቂ ኃይሎች (በተለምዶ “#ፋኖ”) መካከል ከሚካሄደው የትጥቅ ግጭት ጋር ተያይዞ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የነበረው እና ጥር 24 ቀን 2016 ዓ/ም ለተጨማሪ 4 ወራት የተራዘመው የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ አዋጅ ተፈጻሚነት አብቅቷል።

ይህንን ተከትሎ በእስር የቆዩ ሰዎችን የመልቀቅ ሂደት እንዲቀጥል ኢሰመኮ አሳስቧል።

ኮሚሽኑ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አፈጻጸም በሰብአዊ መብቶች አያያዝ ላይ ያለውን ተጽዕኖ በተመለከተ ክትትልና ምርመራ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል።

ከአዋጁ ትግበራ ጋር የተስተዋሉ ክፍተቶችንና የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን የሚያመላክቱ፣ እንዲሁም ምክረ ሐሳቦችን ያካተቱ ግንቦት 20 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፋ ያደረገውን ጋዜጣዊ መግለጫ ጨምሮ በተለያዩ ጊዜያት በርካታ የክትትልና የምርመራ ሪፖርቶች ይፋ ሲያደርግ የቆየ መሆኑ አስታውሷል።

በዚሁ አዋጅ አተገባበር ዐውድ ውቅጥ #በእስር የቆዩ ሰዎች እንዲለቀቁ ማድረግን ጨምሮ ወደ መደበኛው የሕግ አተገባበር ሂደት መመለስ፣ እንዲሁም በተለያዩ የክልል አካባቢዎች የተጣሉ የእንቅስቃሴ ገደቦች እንዲነሱ እና ሌሎችም ማኅበረሰባዊ #አገልግሎቶች እንዲመለሱ ኢሰመኮ ጥሪ አቅርቧል።

#EHRC #Ethiopia #StateofEmergency

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት🚨

2 የወተት ምርቶች የደህንነትና የጥራት መስፈቶች አሟልተው ባለመገኘታቸው ምክንያት ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ማሳሰቢያ ተላለፈ።

1ኛ. #Sultan Instant Full Cream Milk Powder (400g) , (PD 19/02/2024, & Exp 18/02/2026 B.NO.56

2ኛ. #Nura Super Instant Full Cream Milk Powder (400g) PD 01/11/2023 እና Exp 31/10/2025 BT 23246006 LOT No. 230915 291123003127

የወተት ምርቶች የደህንነትና የጥራት መስፈርቶች ያላሟሉ በመሆኑ ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው የንግድና ቀጠናዊ ትስስስር ሚኒስቴር አሳስቧል።

@tikvahethiopia