TIKVAH-ETHIOPIA
1.41M subscribers
55K photos
1.37K videos
199 files
3.67K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ “ ሀኪሞች ከፍተኛ የሆነ የኢኮኖሚ ችግር አለባቸው። ኩሽና ተከራይተው ነው የሚኖሩት፤ ቤት እንኳ የላቸውም። በአውቶብስ ተጋፍተው ነው እየመጡ የሚሰሩት። ይህ ችግር ግን የጤና እከል የደረሰበትን ማህበረሰብ ከማገልገል አልከለከላቸውም ፤ ያንን እያደረጉ ግን ሲታመሙ እንደ ሞያተኛ ሳይሆን ለምነው ነው የሚታከሙት። ” - ዶክተር በሀሩ በዛብህ (የኢትዮጵያ ሕክምና ማኅበር የቦርድ አባል - ለቲክቫህ…
#EMA

“ ሀኪሞች ከፍተኛ የሆነ የኢኮኖሚ ችግር አለባቸው፤ ኩሽና ተከራይተው ነው የሚኖሩት ” - የኢትዮጵያ ህምክምና ማህበር

የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር (EMA) በየዓመቱ ሰኔ 25 ቀን የሚከበረውን “ 7ኛውን የሀኪሞች ቀን ” በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ተከብሮ ነበር።

በዚህም በዘንድሮው ' የሀኪሞች ቀን ' ከጌራ የቤት ለቤት ህክምናና የሀኪሞች ቢሮ ተቋም ጋር በመሆን 2,000 ለሚጠጉ የማህበረሰብ ክፍሎች የቤት ለቤትና የጎዳና ላይ ነጻ የህክምና ለመስጠት ማቀዱን አመላክቷል።

ይኸው የነጻ ህክምና ከሐምሌ 1 /2016 ጀምሮ ነው የሚሰጠው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በተመለከተ፣ ከ34 ዓመታት ጀምሮ በአጥንት ቀዶ ህክምና እያገለገሉ የሚገኙትን የማኀበሩ የቦርድ አባልና የአባላት ጉዳይ የሚከታተሉት ዶ/ር በሀሩ በዛብህን ጠይቋል።

እሳቸው በሰጡት ቃል፣ “ ሀኪሞች ከፍተኛ የኢኮኖሚ ችግር አለባቸው፤ ኩሽና ተከራይተው ነው የሚኖሩት። ቤት እንኳ የላቸውም። በአውቶብስ ተጋፍተው ነው መጥተው የሚሰሩት ” ብለዋል።

“ ይህ ችግር የጤና እከል የደረሰበትን ማህበረሰብ ከማገልገል አልከለከላቸውም ” ያሉት ዶ/ር በሀሩ፣ “ ያን እያደረጉ ግን ሲታመሙ እንደ ሞያተኛ ሳይሆን ለምነው ነው የሚታከሙት ” ሲሉ ተናግረዋል።

“ መብራት ኃይል ለአባላቱ መብራት፣ ቴሌ ለአባላቱ የአየር ሰዓት፣ ውሃና ፍሳሽ ለአባላቱ ውሃ ይሰጣሉ። የእኛ ጤና ሲታወክ እንኳ ምንም አይሰጥም። በህግም የተቀመጠ ነገር የለም ” ሲሉ አማረዋል።

“ የሥራ ሁኔታዎች ራሱ አልተመቻቹም ፤ ከሌላ አገር ጋር ሲገጻጸር እየሰራን የሚከፈለን እራሱ ውስን ነው ” ብለዋል።

“ መሬት እንኳን ቢሰጠን ምን ችግር አለው ? መኖር ነው ያቃተን። የሚከፈለን ገንዘብ በጣም ውስን ነው ” ሲሉ አክለዋል።

በዘርፉ የበዙ ችግሮች ከመኖራቸው አንጻር በርካታ ሀኪሞች ከአገር ለመውጣት እየተገደዱ መሆኑን ገልጸው፣  መንግስት ልቦና ሰጥቶት ለሚስተዋሉ ችግሮች ሁሉ መፍትሄ እንዲሰጥ በማኀበሩ ስም ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ህክምና ማኀበር / EMA ከተመሠረተ 75 ዓመታትን እንዳስቆጠረ፣ በኢትዮጵያ ከ15,000 እስከ 20,000 ሀኪሞች እንዳሉ ተመላክቷል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION🚨 " የበይነ መረብ (ኦንላይን) ተፈታኞች በተመደባችሁበት የፈተና ጣቢያ ተገኝታችሁ ፈተናውን እንድትወስዱ እናሳስባለን " - ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ፈተና በበይነ መረብ (ኦንላይ) እንዲሁም በወረቀት እንደሚሰጥ በዛሬው ዕለት በድጋሚ አሳወቀ። በሁለቱም መንገድ ለሚሰጠው ፈተና ዝግጅት ተደርጓል ብሏል። ትላንት እና ከትላንት በስቲያ በአዲስ አበባ ያሉ አንዳንድ…
#AddisAbaba #NationalExam

“ በሙከራ ላይ እኛ ያጠፍናቸው ጣቢያዎች አሉ እንጂ ፈተና ይቀራል ብለን የሰጠነው መግለጫ የለም ” - ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተማሪ ወላጆችና ከተማሪዎች ግልጽ የሆነ ማብራሪያ ስለተጠየቀበት የበየነ መረብ (ኦንላይን) የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን በተመለከተ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱን ጠይቋል።

ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ምን አሉ ?

“ ፈተና በሁለት አይነት መልኩ (በኦንላይንና በወረቀት) ይሰጣል።

በኦን ላይን የሚሰጠው ዩኒቨርሲቲ ላይ ተመድበው የነበሩ አብርሆት ላይብረሪና ሁለት አዳሪ ትምህርት ቤቶች ብቻ ይሆናሉ።

የተቀሩት ግን በሁሉም በግልም በመንግስም መፈተኛ ጣቢያ ተመድበው የነበሩ ት/ቤቶች ሆኖ በተመደቡበት (ድልድል የወጣላቸው ት/ቤቶች ያውቃሉ) መሠረት ፈተናውን በወረቀት ይወስዳሉ።

በኦንላይን ፈተና የሚወስዱት፦
- በኮተቤ ዩኒቨርሲቲ 
- በሲቪል ሰርቪስ
- በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 
- በአዲስ አበባ ሳይንሰና ቴክኖሎጂ
- በጳውሎስ ሚሊኒየም የተመደቡ በዚያ ይወስዳሉ።


እንዲሁም፣ በአብርሆት ላይብረሪ ላይ የተመደቡ ተማሪዎች፣ የሁለቱ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በኦንላይን ይወስዳሉ።

የቀሩት ግን በሌላ መፈተኛ ጣቢያ ተመድበው የነበሩት ስለታጠፈ በወረቀት ይወስዳሉ።

በወረቀት የሚወስዱት ዩኒቨርሲቲ ነው የሚገኙት በባለፉት ሁለት አመታት እንደተሰጠው ማደሪያቸውም፣ መዋያቸውም፣ መፈተኛቸውም እዛው ይሆናል። አድረው ሲጨርሱ ነው የሚወጡት።

በኦንላይን የተመደቡት ግን ውሎ ገብ ነው። ተፈትነው ወደ ቤታቸው ሂደው አድረው ተመልሰው በጠዋት መጥተው ይፈተናሉ። ” ብለዋል።

የተፈጠረው ውዝግብ ምንድን ነው ? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ፥ “ የተፈጠረ ነገር የለም። በድብልቅ መንገድ እንደምንጥ ታሳቦ ነበረ። እሱን ነበር ስንለማመድ የነበረው ” ነው ያሉት።

“ አሁን More እርግጠኛ በተኮነበት መፈተኛ ጣቢያ (ከላይ በተገለጹት) ብቻ ይሰጣል። ” ሲሉ አክለዋል።

ትምህርት ቤቶች “ ቀርቷል ” ሲሉ ተስተውለዋል፤ ታዲያ መረጃውን ከየት አግኝተውት ነው ? ቢሮው ትዕዛዝ አውርዶ ነበር ? ስንል ኃላፊውን ጠይቀናል።

ዶ/ር ዘላለም ፥ “ በዩኒቨርሲቲዎችና በሌሎች ጣቢያቸዎች እንደሚሰጥ ነገር ግን ሌሎች ጣቢያዎች የነበሩት፣ በእነርሱ ላይ ካልሆነ በስተቀር ' ቀርቷል ' ተብሎ የተሰጠ መግለጫ አልነበረም ” ብለዋል።

አክለው፣ “ ለሙከራ ስንሞክርባቸው የነበሩ እርግጠኛ ያልሆንባቸውን ተማሪዎችና ቤተሰብ ላይ እንግልት እንዳይሆን እርግጠኛ ያልሆንባቸውን ቀንሰናል ” ያሉት ኃላፊው፣ “ በእርግጠኝነት ሊፈጸሙባቸው ተብሎ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በጋራ የተወሰኑት ላይ ግን ተወስኗል ” ብለዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር የበየነ መረብ (ኦንላይን) ፈተናው እንደቀረ ያስተላለፈው መልዕክት ነበር ? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ ደግሞ፣ “ ትምህርት ሚኒስቴር እኮ በገጹ ላይ አስታውቋል እንዳልቀረ ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

“ በሙከራ ላይ እኛ ያጠፍናቸው ጣቢያዎች አሉ እንጂ ፈተና ይቀራል ብለን የሰጠነው መግለጫ የለም። በግልና በመንግስት ትምህርት ቤቶች ተይዘው የነበሩት በተለያዩ ምክንያቶች ተቀንሰዋል ” ብለዋል።

ቢሮዎ ለትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት፣ ለትምህርት ሚኒስቴር ጻፈው ተብሎ ሲሰራጭ የነበረው ደብዳቤ (ከላይ ተያይዟል) የቢሮ ነው ? ለሚለው ጥያቄ ፥ “አዎ። ትክክል ነው !! ” ብለዋል።

“ አሁን ባልናቸው ጣቢያዎች ማለት ነው። በፊት በ153 ጣቢያዎች ብለን ነበር ይዘን የነበረው አሁን ግን በእርግጠኝነት ይሳካል የተባለበት ቦታ ከላይ የተጠቀሱት ጣቢያዎች ብቻ ናቸው ” ሲሉ ተናግረዋል።

በመሆኑም በተቀመጠው መርሀ ግብር መሠረት ተማሪዎች ከምንም አይነት ውዢምብር ራሳቸውን ጠብቀው ከቢሮውና ከትምህርት ሚኒስቴር በሚወርዱ መመሪያዎች ብቻ ተረጋግተው እንዲፈተኑ አሳስበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#EthioTelecom

ኢትዮ ቴሌኮም የ2016 ዓ/ም በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርትን በዛሬው እለት አቅርቧል።

የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ሪፖርቱን በማቅረብ ገለፃ አድርገዋል።

በዚህም ተቋሙ አጠቃላይ ዓመታዊ ገቢውን ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት በ21.7% ወይም በ16.7 ቢሊዮን ብር በማሳደግ 93.7 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል።

21.79 ቢሊዮን የተጣራ ትርፍ ነው።

የእቅዱን 103.6% ማሳካቱንም አሳውቋል።

ተቋሙ የቴሌኮም ደንበኞቹንቁጥር ከአምና ተመሳሳይ ወቅት በ8.9% በማሳደግ 78.3 ሚሊዮን አድርሶ የእቅዱን 100.4% ማሳካቱን ገልጿል።

ቴሌኮሙ በበጀት አመቱ የቴሌኮም እና የዲጂታል መሰረተልማት አቅምን ለማሳደግ ምን ሰራ ?

- የ4G ኔትወርክ አገልግሎትን ወደ 124 ተጨማሪ ከተሞች እና ወረዳዎች በማስፋፋት በአጠቃላይ 4G ተደራሽ የሆነባቸውን ከተሞች ቁጥር ከ300 ወደ 424 ማሳደጉን ገልጿል።

- በተጨማሪም በ79 የሞባይል ጣቢያዎች ላይ የ5G የኔትወርክ ማስፋፊያ ስራ በማከናወን የ5ጂ ጣቢያዎችን ቁጥር ወደ 189 ማድረስ እንደቻለ ጠቁሟል።

- አዲስ አበባን ጨምሮ 5 የከልል ዋና ከተሞችን የ5G ተጠቃሚ ማድረግ የተቻለ ሲሆን ተጨማሪ 4 ከተሞችን የ5G ተጠቃሚ ለማድረግ የትግበራ ስራ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል ተብሏል።

የዲጂታል ገንዘብ ዝውውር እና የተቋሙ የሞባይል ገንዘብ ቴሌብር አፈፃፀም ምን ይመስላል ?

- ቴሌኮሙ የቴሌብር ደንበኞቹን ብዛት 47.55 ሚሊዮን በማድረስ የእቅዱን 107.8% ማሳካቱን አሳውቋል።

- የገንዘብ ዝውውርን በቴሌብር ዲጂታላይዝ በማድረግ በበጀት አመቱ 1.81 ትሪሊዮን የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ ዝውውር በቴሌብር
ተከናውኗል።

- አገልግሎቱ ከተጀመረ (May 11, 2021) ጀምሮ አጠቃላይ በኢኮኖሚው ላይ 2.55 ትሪሊየን የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ ማንቀሳቀስ ተችሏል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update (ቅዳሜ ሰኔ 29/2016 ዓ/ም) ስለ ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ታጋች ተማሪዎች ጉዳይ ከምን ደረሰ ? በታጣቂዎች ስለታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲውን ፣ የግቢው የወንጌላውያን ተማሪዎች ህብረት እና የታጋች ቤተሰብን ምን አዲስ አለ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬም ጥያቄ አቅርቧል። የታጋች ቤተሰቦች አጋቾቹ ወደ 20 የሚሆኑ ታጋቾችን ከትላንት ጀምሮ ወደ ማያውቁትና ጫካ በበዛበት…
#Update (No. 5)

የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ቤተሰብ እየተመለሱ በነበሩበት በታጣቂዎች ስለታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በተደጋጋሚ መረጃ አድርሰናችሁ ነበር።

ዛሬስ ምን አዲስ ነገር አለ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለታጋቾቹ ምን አዲስ አለ ? ሲል የተማሪ ወላጆችን የወንጌላውያን ተማሪዎች ህብረት፣ ደርባርቅ ዩኒቨርሲቲ እና ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል።

ይህ ዘገባ እስከተዘጋጀበት ወቅት ድረስ ከእገታው ያልተለቀቁ ተማሪዎች እንዳሉ ወላጆች ቃላቸውን ሰጥተዋል።

አጋቾቹ አሁንም ለአንድ ተማሪ ግማሽ ሚሊዮን ብር እንደጠየቋቸው፣ ያሰባሰቡትን የተወሰነ ገንዘብ ልከው ታጋቾቹን እንዲለቁላቸው ቢማጸኑም ገንዘቡ ካልተሟላ እንደማይለቋቸው ገልጸዋል።

በርካታ ተማሪዎች አሁንም እንደታገቱ መሆናቸውን እንዳረጋገጡ የገለጹት ሁለት የታጋች ቤተሰቦች፣ ጉዳዩ በሚዲያ እየተንሸራሸረ ስለሆነ መንግስት ሰምቷል ፤ ታዲያ ለምን መፍትሄ አይሰጠንም ? ሲሉ ጠይቀዋል።

የታገቱ ተማሪዎች ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቃቸው አንድ ስማቸው እንዲነገር ያልፈለጉ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ አካል፣ ትንሽ ታጋቾች ቢለቀቁም አብዛኛዎቹ ገና እንደሆኑ መስማታቸውን ተናግረዋል።

ከዚህ የተለዬ መረጃ ግን እንዳልተገኘ አስረድተዋል።

ከትምህርት ሚኒስቴር ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተመሳሳይ ጥያቄ ያቀረበላቸው ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የተባሉ አቶ አብዱ ናሲር፣ ስለጉዳዩ ከፍተኛ አመራሮች እንዲጠየቁ ከመናገር ውጪ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

በዩኒቨርሲቲው የወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት በሰጠው ቃል፣ ታጋቾቹ ወደ ወለጋ መስመር እንደተወሰዱ መስማቱን ገልጿል።

በሌላ በኩል ፥ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) 138 ታጋቾች እንደተለቀቁ መግለጹን ሪፓርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ደግሞ በሸኔ ታግተው የነበሩት 167 ተማሪዎች ናቸው ከነዚህ ውስጥ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ባካሄዱት ኦፕሬሽን 160ዎቹ ከእገታ ተለቀዋል ብሏል።

ይህንን የመረጃና በየሚዲያው " አብዛኛው ተለቀዋል " እየተባለ የሚሰራጨውን መረጃ ተመልክተው ከደቂቃዎች በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መልዕክት የላኩ የተማሪ ወላጆች በጣም እንደተበሳጩ ገልጸው " ውሸት ባይዘገብስ " ሲሉ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba " የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ውጤታቸውን በ https://aa.ministry.et/account#/student-result ላይ በመግባት መመልከት ይችላሉ " - የአ/አ ትምህርት ቢሮ የ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በማለፊያ ውጤቱ ዙሪያ ውይይት በማድረግ የማለፊያ ነጥቡን ይፋ…
#AddisAbaba

የ6ኛ ክፍል ውጤት በቀጣይ ሳምንት ይለቀቃል !

የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት የቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሠጡት ቃል ፦

“ የ8ኛ ክፍል ውጤት ዛሬ ተለቋል። የማለፊያ ውጤት ወስነን ቆርጠን ይፋ አድርገናል።

ወንድም ሴትም 50ና ከዚያ በላይ ያመጡ ናቸው ወደ ሚቀጥለው ክፍል የሚያልፉት። የአካል ጉዳተኞች ማለፊያ ነጥብ 45 እና ከዚያ በላይ ነው።

78 በመቶ የሚሆኑት ተፈታኞቻችን አልፈዋል።

የ6ኛ ክፍል ውጤት በቀጣይ ሳምንት ይለቀቃል። ”


የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት መመልከቻ : https://aa.ministry.et/account#/student-result
(መለያ ቁጥርና ስም ያስገቡ)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update እህታቸው የታገተችባቸው የአዲስ አበባ ነዋሪ ለዶቼ ቬለ ከሰጡት ቃል ፦ " በጣም ይገርማል በእውነት፤ እኔ እኮ በእራሳቸው ስልክ (በአጋቾቹ ማለታቸው ነው) ትናንት ጠዋትም ከሰአት በኋላም እራሴ አግኝቻታለሁ በድምፅ፣ ሰዎቹንም አግኝቻቸዋለሁ። ልጆቹ አሁንም እዚያው ነው ያሉት፤ ተፈተዋል ምናም የሚባለው ነገር ውሸት ነው። ማታ ዜና ስንሰማ ነበር። እንዴት እንዲዚህ ያለ ነገር ይሰራል እስኪ…
#Update (No.7)

• “ እኔ 50 ሺህ፣ ጓደኛዬ 30ዐ ሺህ ብር ከፍለን ተለቀናል። በርካታ ተማሪዎች እየተሰቃዩ ነው ” - ከእገታ የተለቀቀ ተማሪ

• “ እኛም 700 ሺህ ላኩ ተብለናል ” - የታጋች ተማሪ ወንድም


ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ቤተሰብ እየተመለሱ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በታጣቂዎች ከታገቱ 10 ቀናት አስቆጥረዋል።

ስለታጋቾቹ ዛሬስ ምን አዲስ ነገር አለ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ገንዘብ ከፍሎ ከእገታው የተለቀቀ ተማሪ እና የታጋች ቤተሰቦችን ስለጉዳዩ ጠይቋል።

አንድ ስሙ እንዲገለጽ ያልፈቀደ ከእገታው የተለቀቀ ተማሪ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል፣ “ እኔ 50 ሺህ ፣ ጓደኛዬ 300 ሺ ብር ከፍለን ተለቀናል። በርካታ ተማሪዎች እየተሰቃሉ ነው ” ብሏል።

ከታጋቾች መካከል 36 የሚሆኑት ከኦሮሚያ  ሲሆኑ 28ቱ በነጻ ሲለቀቁ ሌሎች 9ኙ ግን እዛው እደታገቱ ናቸው ፤ ከአማራ እና ደቡብ የሆኑም እንዳልተለቀቁ ገልጿል።

‘ ታጋቾች ተለቀዋል፣ 7 ታጋቾች ናቸው ያልተለቀቁት ’ የሚባለው ዜና ውሸት መሆኑን ገልጾ፣ ከገርበ ጉራቻ በእግር የ1 ሰዓት የእግር መንገድ ከሚወስድ ጫካ አሁንም ከ60 በላይ ታጋቾች እንዳሉ መመልከቱን ተናግሯል።

የአይን እማኙ፥ “ ያሳለፍኩትን ከባድ መከራ በቃላት አልገልጸውም ” ያለ ሲሆን ታጋቾቹ በምግብ እጦትና በብርድ እየተሰቃዩ በመሆናቸው መንግስትም እንዲደርስላቸው አሳስቧል።

“ ቤተሰቦቼ ድሃ ናቸው ብዬ አልቅሼ ነው የለቀቁኝ ። ጓደኛዬ 300 ሺህ ብር ባይከፍል ግን አይለቁኝም ነበር ” ብሏል።

አንድ የታጋች ወንድም በሰጡት ቃል ደግሞ ፥ “ ' ልጆች ተለቀዋል ' ይባላል ፤ በርካታ ወላጆች ግን ልጆቻቸው በእገታ ላይ ናቸው። ደውለን እየጠየቅን ነው። እኛም 700 ሺህ ላኩ ተብለናል። ግን ገንዘብ የለንም !! ” ብለዋል።

ሌላኛዋ የታጋች እህት በበኩሏ ፣ ታጋች እህቷ እስከ 3 ቀናት 40ዐ ሺህ ብር ላኪ እንደተባለች፣ ከ10 ሺህ ብር በላይ ግን ማግኘት እንዳልቻለ ገልጻላች።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚሁ ጉዳዩ ላይ ምላሽ ለማግኘት ወደ ኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን፣ ሰላምና ጸጥታ ቢሮዎች ያደረገው ሙከራ ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ምላሻቸውን ማካተት አልተቻለም። 

በተጨማሪም፣ የኢፌዴሪ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ታጋቾቹን ለማስለቀቅ ምን እየተሰራ እንደሆነ ጥያቄ አቅርበናል።

የአገልግሎት ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ከበደ ደሲሳ ፥ " በጉዳዩ ላይ የኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ከሰጠው ወጪ የተለየ ነገር የለኝም " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የኮሙኒኬሽን ቢሮ ፣ ከቀናት በፊት በሰጠው መግለጫ በ ' ሸኔ ቡድን ታግተው ተወሰዱ ' ካላቸው 167 ታጋቾች መካከል የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ባካሄዱት ኦፕሬሽን 160ዎቹ ከእገታ መለቀቃቸውን 7 ታጋቾች ብቻ እንደቀሩ አሳውቆ ነበር።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ሁለት ወራት ከ18 ቀናት ነው መተከል የቆየሁት አንድም ቀን መብራት አልበራም " - ዶክተር መብራቱ አለሙ የኢትዮጵያ ፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የሥራ አስፈፃሚ ፣ የቦሮ ዲሞክራሲ ፓርቲ (ቦሮ) የውጪ እና ዓለም አቀፍ ዘርፍ ኃላፊ ፣ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ረዳት ፕሮፌሰር ዶ/ር መብራቱ አለሙ የቦሮ ዲሞክራሲ ፓርቲን ወክለው ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በዚህ ቆይታቸው…
🔈#የነዋሪዎችድምጽ

• “ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የሚተገበረው ግን መቼ ነው ? ” - የቡለን ወረዳ ነዋሪዎች

• “ ‘ለምን አልመርጣችሁኝም ’ በማለት በበቀል ህዝብን መጉዳት ተገቢ አይደለም ” - ዶ/ር መብራቱ አለሙ


በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ቡለን ወረዳ ‘ ለምን ፓርቲውን መረጣችሁ ’ በሚል ሰበብ በደል እየደረሰባቸው መሆኑን የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አባላት እና ፓርቲው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

በአካባቢው ከዚህ ቀደም በነበረው የጸጥታ ችግር ሳይካሄድ ቀርቶ የነበረው ምርጫ በቅርቡ መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን፣ ምርጫውን ያሸነፈው የፓርቲው አባላት ላይ የ ' ቡለን ወረዳ አስተዳደር ' እስራትን ጨምሮ ድብደባ እያደረሰባቸው መሆኑን ተናግረዋል።

“ እኛ የፈለግነውን የመምረጥ መብት አለን። ቦሮን መረጣችሁ በማለት እንዴት እንግልት ይደርስብናል ? ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የሚተገበረው ግን መቼ ነው ? ” ሲሉ ጠይቀዋል።

የፓርቲው የውጪና አለም ዓቀፍ ዘርፍ ኃላፊ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ከፍተኛ አመራር ዶ/ር መብራቱ አለሙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ አመራሮች ከምርጫ በኋላ ‘ለምን ቦዴፓን መርጣችሁ’ በሚል ሰበብ ” የሚከተሉትን ድርጊቶች በአባላቱ ላይ እየፈጸሙ መሆኑን ገልጸዋል።

➡️ ከቀበሌ ሚሊሻ አርሶ አደሮች ትጥቅ ማስፈታት
➡️ ነጋዴዎች ላይ ከፍተኛ ግብር መጫን
➡️ የመንግስት ሠራተኞችን ማዋከብና ፣ ማስፈራራት፣ ማሰርና ማዘዋወር
➡️ ነዋሪዎችን ‘በልማት ስራ አልተገኛችሁም’ በማለት በገንዘብ መቅጣት
➡️ መንግስታዊ አገልግሎት መንፈግ ለአብነት የመታወቂያ እድሳት፣ አዲስ የመታወቂያ ጥያቄ አለማስተናገድ፣
➡️ የድጋፍ ደብዳቤ መከልከል ተጀምሯል ሲሉ ድርጊቶቹን አስረድተዋል።

“ ከነበሩት ቦታ ያለአግባብ የተዘዋወሩ ሁለት የግብርና ባለሙያዎች ቅሬታ በጽሑፍ ሲያቀርቡ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ ወርቀቱን ተቀብሎ ቀዶ ከጣለ በኋላ ባለጉዳዮች እንዲታሰሩ አድርጓል ” ሲሉም ወቅሰዋል።

“ የባለጉዳዮችን አቤቱታ ቀዶ የጣለውን ትተው ባለጉዳዮችን አስረዋል ” ነው ያሉት።

“ ህዝቡ የፈለገውን ፓርቲ የመምረጥ መብት አለው። የፈለገውንም መርጧል ” ያሉት ዶ/ር መብራቱ ፥ “ መንግስት ደግሞ የመርጠውንም ያልመርጠውን እኩል የማገልገል ግዴታ አለበት ” ብለዋል።

“ ‘ ለምን እኔን አልመርጣችሁኝም ’ በማለት በበቀል ህዝብን መጉዳት ተገቢ አይደለም። ይህ አካሄድ መልሶ መንግስትን ይጎዳል። ይህ ድርጊት የወንጀል ተጠያቂነትን ያስከትላል ” ሲሉ አክለዋል።

“ በአጠቃላይ በወረዳው ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ህገወጥ ወከባ የማይቆም ከሆነ በወረዳው ግጭት ሊፈጠር ይችላል ” ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

ቅሬታ ለፈጠረው የመብት ጥሰት ቅሬታ የወረዳውን ምላሽ በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈#የኢትዮጵያ_ቃለ_ሕይወት_ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታ ላይ በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት እየተወሰደ ነው ያለችው ሕገወጥ እርምጃ እንዲቆም የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ጥሪ አቅርባለች። ቤተክርስቲያኗ በዛሬው ዕለት ስለጉዳዩ ሰፋ ያለ ዝርዝር መግለጫ ልካልናለች። ከመግለጫው መካከል ፦ " በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እየተካሄደ…
#Update

“ ሃያ (20) ሄክታሩን አጥረውታል። መጋዘኖችንም እያፈረሷቸው ነው። ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ” - ቤተክርስቲያኗ

የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን፣ 40 በመቶ የሚሆን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታዋን የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ‘ በጉልበት ሊወስደው ነው ’ ስትል ከሰሞኑን በተደጋጋሚ መግለጫ መስጠቷ ይታወቃል።

ጉዳዩ ከምን ደረሰ ?

ቤተ ክርስቲያኗ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠችው ቃል ፣ “ 20 ሄክታሩን አጥረውታል። መጋዘኖችን እያፈረሷቸው ነው። ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ” ብላለች።

“ ዛሬ (ሰኞ ሐምሌ 8 ቀን 2016 ዓ/ም) ግቢ ውስጥ ገብተው በጉልበት አጥረውታል። መሳሪያ በያዙ ሰዎች እያስጠበቁት ነው ያሉት ” ስትል ገልጻለች።

ይህንን ያሉት አንድ የቤተ ክርስቲያኗ አካል ፣ “ እኛም ዛሬ ለጠቅላይ ሚኒስቴሩም፣ ለኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ አመራሮችም ደብዳቤ እየላክን ነው ” ብለዋል።

“ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጠዋት ነው የላከነው፣ ለአቶ ሽመልስ አብዲሳም ልከናል። ገና ምንም የሰጡት ምላሽ የለም ” ሲሉ አክለዋል።

“ 40 በመቶ ገደማ ይዞታችን ነው ይወሰዳል የተባለው ” ያሉት እኝሁ አካል፣ “ አሁን ግማሹን አጥረዋል። ለሁለት ግለሰቦች ነው ይሰጣል የተባለው ” ነው ያሉት።

በተጨማሪ ፣ በፍርድ ቤትም እግድ እንዲያወርድላቸው እንደጠየቁ፣ የሚጠብቁት ያስገቡትን ደብዳቤ ምላሽ እየጠበቁ እንደሆነ ገልጸዋል።

“ አስቸኳይ ምላሽ የማይሰጠን ከሆነ ሰላማዊ ሰልፍ ወደ መጥራት የምናመራ ይሆናል። በሰላማዊ መንገድ ድምፃችንን እናሰማለን። ሁል ጊዜ ቤተ ክርስቲያን የምትቆመው ከሰላም ጎን ነው። የመረበሽ የማስረበሽ ዓላማ የላትም ” ብለዋል።

ቅሬታ የቀረበበት የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም። ሆኖም በቀጣይ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆነ ምላሹን የምናቀርብ ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
🔈#የነዋሪዎችድምጽ

“ ከሆስፒታሉ ውጪ በ3 እጥፍ ዋጋ መድኃኒት እየገዛን ነው ” - ታካሚዎች

“ የአቅርቦት እጥረት አለ ” - የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል 

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል በመድኃኒት እጥረት ሳቢያ ታካሚዎች ከ3 እጥፍ በላይ በሆነ ዋጋ ከግል መድኃኒት ቤቶች መድኃኒት ለመግዛት እየተገደዱ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አማረሩ።

በርካታ ታካሚዎች ዋጋው ከአቅማቸው በላይ በመሆኑ ህክምናቸውን እያቋረጡ መሆኑን፣ ችግሩ መቀረፍ ሲገባው ተባብሶ እንደቀጠለ አስረድተዋል።

በተለይ እንደ ሴፍትሪያክዞን፣ ዲ40% የመሳሰሉ መድኃኒቶች ከሆስፒታሉ ከጠፉ ወራት እንደተቆጠሩ ተናግረዋል።

“ ከሆስፒታል ውጪ በ3 እጥፍ ዋጋ መድኃኒት እየገዛን ነው” ያሉት ታካሚዎቹ፣ የላብራቶሪ ምርመራዎች ‘በተደጋጋሚ ተበላሽተዋል’ እየተባለ የምርመራ ከሆስፒታል ውጪ ለማሰራት እየተገደዱ መሆኑን ተናግረዋል።

ችግሩ ለምን ተፈጠረ ? ሲል ቲክቫህ የጠየቃቸው የጎንደር ዩኒቨርሲቲው ሆስፒታል ቺፍ ክሊኒካል ዳይሬክተር ዶ/ር መኳንንት መለሰ፣ “ አሁን ባለው የበጀት Ristriction፣ የፋይናንስ እጥረት ምክንያት አንዳንድ መድኃኒቶች አይኖሩም ” የሚል ምላሽ ተሰጥተዋል።

“ በወቅታዊ ችግር አሁን በወቅታዊ ችግር መንገድ ዝግ ነው። መድኃኒት ቀጥታ ከአዲስ አበባ በደጀን በኩል ነበር የሚመጣው አሁን በአፋር ክልል ነው የሚመጣው። የአቅርቦት እጥረት አለ ” ብለዋል።

➡️ ዲ 40% የተሰኘው መድኃኒት ያልነበረው “ትራውማ ካዡዋሊቲ” በዝቶ ስለነበር እንደሆነ፣
➡️ ይሁን እንጂ አሁን የመድኃኒት አቅርቦቱ እንዳለ፣ 
➡️ የላብራቶሪ ማሽኑ በመብራት መቆራረጥ ሳቢያ በመቆሙ ለሳምንት የተመላላሽ ታካሚዎች ህክምና ተቋርጦ እንደነበርና ማሽኑም እየተጠገነ መሆኑን አስረድተዋል። 

ሆስፒታሉ በቀን ከ3,000 በላይ፣ በአጠቃላይ ደግሞ 13 ሚሊዮን ለሚሆኑ ሰዎች የተለያዩ የህክምና አገልሎቶች እንደሚሰጥ ተገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
⚠️ እባካችሁ ተጠንቅቃችሁ አሽከርክሩ ⚠️

ዛሬም በትራፊክ አደጋ የበርከታ ሰዎች ህይወት አልፏል።

የዛሬው አደጋ በጌዴኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ ዲባንድቤ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው የደረሰው።

በዚህም የ9 ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ አልፏል።

ከሟቾች ባሻገር በ4 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሰ ሲሆን ተጎጂዎቹም ወደ ዲላ ሪፈሪያል ሆስፒታል ሪፈር ተብለው ገብተዋል።

የጮርሶ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፤  የአደጋው መንስኤ ታርጋ ቁጥሩ ኢት ኮድ (03)19178 የሆነ ሲኖትራክ፣ ከዲላ ወደ ሞያሌ ሲጓዝ ከነበረው ዶልፈን ሚኒንባስ ኮድ 0322503፣ በተመሳሳይ ከዲላ ወደ ከቡለሆራ ሲጓዝ ከነበረ FSR መኪና ታርጋ ቁጥር AA ከድ 03 74596 ጋር በመጋጨቱ መሆኑን አሳውቋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM