TIKVAH-ETHIOPIA
1.49M subscribers
56.6K photos
1.41K videos
203 files
3.85K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Amhara

በነገው ዕለት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ይጀመራል።

በአማራ ክልል ውስጥ የተፈታኞች ቁጥር ከታቀደው በግማሽ እንደሚያንስ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ዛሬ አስታውቋል።

ቢሮው በዚህ ዓመት ከ200 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እንደሚቀመጡ አቅዶ ነበር።

ነገር ግን አሁን ፈተና ላይ ይቀመጣሉ የተባሉት  96 ሺህ 408 ተማሪዎች ብቻ ናቸው።

ቀሪ 106 ሺህ ያክል ተማሪዎች ፈተና አይወስዱም።

አሁን ላይ ፈተናውን የማይወስዱ ተማሪዎች  ተምረው በመስከረም 2017 ዓ/ም በሁለተኛ ዙር ለመፈተን እቅድ እንደተያዘ ተነግሯል።

በነገ ዕለት ፈተና የሚጀምሩት ተማሪዎች ለፈተናው መቀመጥ የሚያስችላቸውን ትምህርት የተከታተሉ እንደሆኑ ቢሮው አሳውቋል።

ባለፉት በርካታ ዓመታት የሀገሪቱ ከፍተኛው ውጤት የሚመዘገብበት እና እጅግ በጣም ጎበዝ ተማሪዎች የሚገኙበት አማራ ክልል ዘንድሮ የሚጠበቅበትን ያክል ተማሪ ባለማስተማሩ ሳቢያ በርካታ ተማሪዎች በመጀመሪያ ዙር ፈተና ላይ መቀምጥ አልቻሉም።

በሌላ በኩል በአማራ ክልል ዘንድሮ ትምህርታቸውን መማር ከነበረባቸው 6.2 ሚሊዮን ተማሪዎች መካከል መማር የቻሉት 3.7 ሚሊዮን ተማሪዎች ናቸው።

ከ2.5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች ትምህርት አልተማሩም።

ይኸው እስከ ዛሬ ትምህርት ያልጀመሩ ዞኖች እና ወረዳዎች አሉ።

በቅርቡ ቢሮው ዓመቱን ሙሉ በሙሉ ጭራሽ ምንም ያልተማሩ ተማሪዎች እንዳሉ ገልጾ ነበር።

ተማሪዎች ካልተማሩባቸው መካከል ሰሜን ጎጃም እና ምዕራብ ጎጃም ዞኖች ዋነኞቹ ሲሆኑ ምንም አይነት ተማሪ / አንድም እንኳን ተማሪ የ6ኛ ፣ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ፈተና እንደማያስፈትኑ መግለጹ ይታወሳል።

#AmharaEducationBureau
#NationalExam
#DeutscheWelle

@tikvahethiopia