TIKVAH-ETHIOPIA
1.49M subscribers
56.6K photos
1.41K videos
203 files
3.85K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የሀድያ ዞን ምክር ቤት የሀድያ ብሔረሰብ የራሱን #ክልል እንዲመሰርት የቀረበለትን የውሳኔ ሀሳብ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።

©ኤርመኮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተደረገ በሚገኘው ሰላማዊ ሰልፍ የተሰሙ መፈክሮች፦

√ከአጎራባች ህዝቦች ጋር ያለን #አብሮነታችን ተጠናክሮ ይቀጥላል!

√የክልልነት ጥያቄያችን በአስቸኳይ ይመለስ!

√የወላይታ ህዝብ በብዝሃነት ላይ የተመሰረተ አንድነትን #ይደግፋል!

√ሀገራዊ ለውጡ #ተጠናክሮ እንዲቀጥል የህግ የበላይነት ሊከበር ይገባል!!

√መንግስት በወላይታ ብሄር ተወላጆች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት #ሊያስቆም ይገባል።

√የደቡብ ክልል ምክር ቤት የህዝባችንን የክልል ጥያቄ አዳፍኖ መያዙን አጥብቀን #እንቃወማለን!

√በ1950ቹ የነበረው የወላይታ አውሮፕላን ማረፊያ #ይመልስልን!

√አሁን ያለው ሀገራዊ ለውጥ በምንም አይነት ሁኔታ #ሊደናቀፍ አይገባም!!

√እኛ የለውጥ #ደጋፊዎች ብቻ ሳንሆን የለውጥ #ባለቤቶች ነን!!

√ሀገር ለነበረው ወላይታ #ክልል መሆን አይከለከልም!!

√ስራ ወዳድነት #ክብር እንጂ ውርደት አይደለም!

√ወላይታ በሞግዚቶች መመራት በቃው! ጋሞ፣ ጎፋ፣ ሲዳማ፣ ዳውሮ የወላይታ ወንድም ሕዝቦች ናቸው!

√ኢትዮጵያዊነት ፀጋ እንጂ ኩነኔ ሊሆን አይገባም!

√የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለወላይታ!


በአሁን ሰዓት በወላይታ ሶዶ ስታዲየም ብዙ ሺ ሰዎች በተገኙበት የማጠቃለያ ፕሮግራም እየተካሄደ እንደሆነ ለመስማት ችለናል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UpdateSport የአውሮፓ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ በአዘርባጃኗ ዋና ከተማ ባኩ መካሄዱ ብዙ ቅሬታዎችን አስነስቷል።

የፊታችን ቅዳሜ የሚደረገው የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ ለመታደም ብዙ እንግሊዛውያን ወደ ስፔኗ መዲና ማድሪድ እንደሚጎርፉ ይጠበቃል።

ነገር ግን ዛሬ የሚካሄደውን የአውሮፓ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ለማየት ወደ አዘርባጃን መዲና ባኩ መምጣት የሚችሉት የአርሰናልና የቼልሲ ደጋፊዎች ቁጥር ከ6000 እንደማይበልጥ ተገልጿል።

ከዚህ በተጨማሪ የአርሰናሉ ሄነሪክ ሚኪታሪያን #በአርሜኒያዊ ዜግነቱ ምክንያት ደህንት አይሰማኝም በማለት ወደ አዘርባጃን እንደማይሄድ አስታውቋል። አርሜኒያ እና አዘርባጃን 'ናጎርኖ ካራባክ' የተባለው #ክልል የይገባኛል ፍጥጫ ውስጥ ያሉ ሲሆኑ የሚኪታሪያንም #የስጋት ምንጭ ይሄው ነው።

ብዙዎችም የፍጻሜ ጨዋታውን ለምን በአዘርባጃን ማካሄድ አስፈለገ? በማለት ቅሬታቸውን እየገለጹ ነው። የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ግን ሃገሪቱ ለምስራቅ አውሮፓ ሩቅ በመሆኗ ምክንያት ውድድሩን ከማዘጋጀት ልትታገድ አይገባም ብሏል።

ባላት የነዳጅ ሃብት ምክንያት እጅግ የበለጸገችው አዘርባጃን ብዙ ሚሊዮን ዶላሮችን ፈሰስ በማድረግ በዓለማቀፍ ስፖርት ቤተሰቦች ዘንድ ያላትን ተቀባይነት ከፍ ለማድረግ እየሰራች ነው።

Via #ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
" ... ህወሓቶች የሀገሪቱን ሕገ መንግስት እንዲያከብሩ ፤ እና እንደ ኢትዮጵያ አንድ #ክልል እንዲንቀሳቀሱ ለማሳመን እየሞከርን ነው " - ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለመፍታት በሚካሄደው ሂደት ከባድ የውጭ ጣልቃ ገብነት እንዳለ ጠቅላይ ሚኒስተር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ከCGTN  ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ነው።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ሰላምን ለማምጣት ባለው ሂደት " የውጪ ጣልቃ ገብነት " ቢኖርም የሰላም ስምምነት እንደሚደረስ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።

" በእርግጥ ከግራም ሆነ ከቀኝም በርካታ ጣልቃ ገብነቶች የሚኖሩ ከሆነ በጣም አስቸጋሪ ይሆናል " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ ፤ " ኢትዮጵያውያን መረዳት ያለባቸው የራሳችንን ጉዳይ በራሳችን መፍታት አንደምንችል " ነው ሲሉ አክለዋል።

" ህወሓት የሀገሪቱን #ህገመንግስት እንዲያከብር ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ አንድ ክልል  እንዲንቀሳቀስ ለማሳመን ጥረት እያደረገን ነው " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ " ፍላጎታችንን መገንዘብ የሚችሉ ከሆነ እና የራሱን ህገመንግስት የሚያክብር እና በህጉ መሰረት የሚንቀሳቀስ ከሆነ ሰላም ይሰፍናል ብየ አስባሁ " ብለዋል።

(ሙሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
🇪🇹 #NationalDialogue 🇪🇹

የመጅሊሱ ቅሬታ ምንድነው ?

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ህዝበ ሙስሊሙ ሀገራዊ ምክክሩን እጅግ እንደሚደግፈው ነገር ግን ከምክክሩ ተሳታፊዎች ጋር በተያያዘ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እንዳልተሰጠው በዚህም ምክንያት ቅሬታ እንዳደረበት ገልጿል።

ም/ቤቱ ያደረበት ቅሬታ " በምክክሩ ላይ የሙስሊሞች ውክልና አነስተኛ ነው ፤ ይህ ደግሞ በምክክር ውጤቱ ላይ ተጽእኖ እንዳያሳድር ስጋት አለኝ " የሚል ነው።

" #ከወረዳ እስከ #ክልል ድረስ የሚሳተፉት ተወካይ ሙስሊሞች ቁጥር እጅግ አነስተኛ ነው " የሚለው ም/ቤቱ ፥ " እንደ ሙስሊም በጋራ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ መግባባት ላይ ለመድረስ በቂ ተወካዮች አልተወከሉም " ብሏል።

የምክር ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ከማል ሀሩን ምን አሉ ? (ለሃሩን ሚዲያ)

- ሙስሊሙ ከምንም በላይ ምክክሩን ይፈልገዋል።

- ሙስሊሙ የቆዩ ችግሮች ስላሉበት ይሄን ምክክር እንዲሳካ በጣም ከሚደግፉት ማህበረሰብ ክፍሎች ዋነኛው ነው።

- ከሌሎች እምነቶች ሲነጻጸር ሙስሊሙ ማህበረሰብ ለዚህ ምክክር ያለው ድጋፍ ፈጽሞ ሊወዳደር የሚችል አይደለም። ሙስሊሙ ይህንን ምክክር የሚፈልገው ያልተመለሱለት ጥያቄዎቹ እንዲመለሱለት ነው።

- ተወካዮች ከታች ሲመረጡ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ተሳታፊ እንዲሆን ያስፈልጋል። ኮሚሽኑም check and balance ማድረግ አለበት ፤ በትክክልም የዚህን ማህበረሰብ ጥያቄዎች የሚያነሱ ተወካዮች ተወክለዋል የሚለውን።

- የተሳታፊዎች ልየታ ከታች ጀምሮ ሲመጣ በትክክል ሁሉም ማህበረሰብ መወከሉን ማረጋገጥ ይገባል። ኮሚሽኑም ከሌሎች እምነቶች ጋር balance የማድረግ ስራ ይጠበቅበታል።

- ተሳትፎ ላይ ቁጥሩ የተዛባ ከሆነ፣ በጣም አነስተኛ ከሆነ ቅሬታ ስለሚያስከትል ጥንቃቄ ያስፈልጋል።

- ኮሚሽኑ አካሄድ የነበረው ሲቪል ማህበራት፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ መምህራን ፣ አርብቶ አደሮች፣ እድሮች፣ የፍትህ አካላት፣ የመንግሥት ሰራተኞች፣ ፖለቲከኞች የያዘ ነው በሃይማኖት መልክ ግን የቀረበ ነገር የለም። እነዚህ አደረጃጀቶች ምን ያህል ሙስሊሙ ተሳትፎ አለው ? የሚለው ያሳስበናል፤ ስጋትም አድሮብናል።

- የተነሱ ጥያቄዎችን እና ያሉትን ስጋቶች በተደጋጋሚ ለኮሚሽኑ ቀርበው የጋራ ኮሚቴ ጭምር እንዲቋቋም መረጃዎችም እንዲሰጡ ተጠይቆ በተለያየ ምክንያት ሊሳካ አልቻለም።

- ውይይቶች አድርገናል በተደጋጋሚ ፤ በውጤቱ ላይ የሙስሊሙን ተሳትፎ የሚያሳዩ መረጃዎች (ዳታ) ማግኘት አልተቻለንም።

- እንደ አጀንዳ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ጥያቄዎች በ9 አጀንዳዎች ተካተው ፣ በ47 ጥያቄ ቀርቦ የካቲት 2 ላይ ለኮሚሽኑ ቀርቧል። መጨረሻ ላይ ኮሚሽኑ ያንን የማስፈጸም ኃላፊት አለበት።

- ታች ያለው የማህበረሰቡ ውክልና በተሻለ ሁኔታ ሁሉ የሃይማኖት ተቋማት ባገናዘበ፣ ሃይማኖት ተቋማትን balanced ባደረገ ሁኔታ መታየት አለበት ቁጥሩ። ለምሳሌ ፦ ከ12 ሺህ ምን ያህል ሙስሊም ተካቷል ፤ ከአዲስ አበባም ከ2500 ተሳታፊ ካለ ምን ያህል ሙስሊም ተሳታፊ ነው ? የሚለው ነው የማህበረሰቡ ጥያቄ።

- እኛ በቂ መረጃዎች የሉንም ለማህበረሰቡ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት አስቸጋሪ ነው። በአንዳንድ ሁኔታ ስናጣራ በጣም አነስተኛ ቁጥር ያለበት ስለሆነ የተሻለ ውጤት እንዲገኝ ጥያቄ በማያስነሳ መንገድ እንዲሄድ ማድረግ ይገባል።

- የሙስሊሙ ማህበረሰብ ተሳታፊ ቁጥር አነስተኛ ከሆነ የሚቀርበው አጀንዳ ይቀራል ፤ ያ ደግሞ እጅጉን ያሳስበናል።

- በእኛ በኩል አሁንም ምላሽ እየጠበቅን ነው።

#EthiopianMuslims
#HarunMedia
#NationalDialogue

@tikvahethiopia