TIKVAH-ETHIOPIA
1.44M subscribers
55.9K photos
1.4K videos
202 files
3.77K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አላማጣ‼️

በአላማጣ የማንነት ጥያቄ ባነሱ ወጣቶችና በጸጥታ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ ግጭት የሰዎች #ህይወት ጠፍቷል።

ትናንት በአላማጣ ከተማ በታጠቀ የልዩ ኃይልና በወጣቶች መካከል በተፈጠረው ግጭት አምስት ግለሰቦች #በጥይት ተመትተው መሞታቸው የዓይን እማኞች ተናግረዋል።

ከጥቂት ወራት በፊት ጀምሮ የአላማጣ ከተማ ወጣቶች የማንነት ጥያቄዎችን እንደሚያነሱ የከተማው ነዋሪዎች ይናገራሉ።

አቶ ዝናቡ ማርፌ የአላማጣ ከተማ ነዋሪ ሲሆኑ ትናንት በከተማዋ በተካሄደው ሰልፍ ላይ ተሳታፊ ነበሩ። በስልፉ ወቅት ድብደባ ተፈጽሞብኛል የሚሉት አቶ ዝናቡ ''ካለፉት ሦስት ወራት ወዲህ የከተማዋ ወጣቶች ወረቀት በመበተን ሰላማዊ ሰልፎችን ለማካሄድ ጥረቶችን ያደርጉ ነበር። ለውጡን እንደግፋለን የሚሉ ከነቴራዎችን ያደርጋሉ በእነዚህ ተግባሮቻቸውም ይታሰራሉ ከዚያም ይፈታሉ። የትናንቱ ግን አስከፊ ነበር'' በማለት የትናንቱን ክስተት ያብራራሉ።

ትናንት የእጅ ኳስ ሜዳ ላይ በተጀመረ የተቃውሞ ሰልፍ ለበርካቶች የህይወት መጥፋት እና የአካል ጉዳት ምክንያት ሆኗል። የከተማዋ ነዋሪዎች እንደሚሉት ከሆነ መሰብሰብ አትችሉም የተባሉት የከተማዋ ወጣቶች ከፀጥታ ኃይሎች ጋር #ተጋጭተዋል

ሌላው ለደህንነቱ ሲል ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈለገ የከተማዋ ነዋሪ በትናንቱ ግጭት በጥይት ታፋው ላይ ተመትቷል። ''በጥይት የተመታን ልጅ ለማንሳት ስሄድ እኔም ተመታሁኝ'' ይላል። ''በጥይት መመታቴን እንኳ አልታወቀኝም ነበር። አጠገቤ ያሉ ሰዎች ናቸው ስሜን እየጠሩ በጥይት መመታቴን የነገሩኝ። አንገቴ ላይ ደም ስመለከት አንገቴን የተመታሁ መስሎኝ ነበር። አንገቴ ላይ የነበረው ደም ግን የሟቹ ልጅ ነበር'' በማለት ሁኔታውን ያስረዳል።

ይህ ወጣት ትናንት ወደ የእጅ ኳስ ሜዳው ተሰባሰበው በሄዱበት ወቅት እንዲበተኑ በመደረጉ በተፈጠረ ግጭት ጉዳቱ መድረሱን ያስረዳል።

''የሆነ ነገር ያደርጉኛል ብዬ ስለሰጋሁ ወደ የግል ሕክምና እንጂ ሆስፒታል አልሄድኩም። አሁንም የምገኘው በመኖሪያ ቤቴ ነው'' ይላል። የአላማጣ ከተማ ነዋሪው አቶ ዝናቡ እንደሚሉት የሃገር መከላከያ ሠራዊት አባላት በቦታው ቢደርሱም የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ ግን ተስኗቸዋል ይላሉ። ''የልዩ ኃይሉ የሚፈጽመውን ጥቃት እንዲያስቆሙ ስንጠይቃቸው 'የተዘጋውን መንገድ ብቻ ነው የምናስከፍተው' አሉን'' ይላሉ።

የተጎጂዎች ቁጥር ከአቶ ዝናቡ ማርፌ እና ከሌሎች የከተማዋ ነዋሪዎች እንደተሰማው ከሆነ 5 ሰዎች #ተገድለዋል 15 የሚሆኑ ደግሞ ከባድ እና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል። እንዲሁም ከ50 ባለይ ሰዎች ለእስር ተዳርገዋል።

የማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አግዜ ህዳሩ በበኩላቸው የሟቾችን ቁጥር 9 የተጎጂዎችን ደግሞ 16 ያደርሱታል።

የትግራይ ክልል ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ደግሞ በፌስቡክ ገጹ ላይ በአላማጣ ከተማ በማንነት ስም በሚንቀሳቀሱ አካላት እና በፀጥታ ኃይሎች መካከል በተከሰተ ግጭት የሦስት ሰዎች ህይወት አልፏል ብሏል።

ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የአላማጣ ሆስፒታል ባልደረባ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ከሆነ በትናንቱ ግጭት ጉዳት የደረሰባቸው 25 ሰዎች በሆስፒታሉ የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሆነ እና አንድ ሰው ደግሞ ባጋጠመው ከፍተኛ ጉዳት ለተጨማሪ ህክምና ወደ መቀሌ መላኩን ነግረውናል።

አላማጣ ዛሬ ረፋድ አቶ ዝናቡ እና ሌላ የከተማዋ ነዋሪ እንደሚሉት ከሆነ ዛሬ እስከ ረፋድ ድረስ አላማጣ ውስጥ መንገድ ዝግ ነበር። የሃገር መከላከያ ሠራዊት አባላት መንገድ ለማስከፍት ጥረት ሲያደርጉ ውለዋል።

ትናንት ከተገደሉት 5 ሰዎች የሁለቱ ሰኞ ጠዋት አላማጣ እየሱስ ቤተ ክርስቲያን የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸው ተፈጽሟል። ''የሟቾች ሰውነት በከፍተኛ ሁኔታ የተበጣጠሰ ስለሆነ በጠዋት ነው የተቀበሩት'' ሲሉ አቶ ዝናቡ ተናግረዋል።

ከሟቾቹ መካከል የሦስቱ ግለሰቦች አስክሬን ከአላማጣ ውጪ ወደ ሆኑ ቦታዎች የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸው ሊፈጸም አስክሬናቸው ወደ ትውልድ ስፍራቸው መላኩን ከከተማዋ ነዋሪዎች ሰምተናል።

የማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አግዜ ህዳሩ በበኩላቸው የአካባቢው ህዝብ ላለፉት ሦስት እና አራት ወራት የማንነት ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ ለማቅረብ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል ያሉ ሲሆን፤ ''የትግራይ ክልል መንግሥት ግን ከፍተኛ ቁጥር ያለውን ልዩ ኃይል ወደ አካባቢው በማስገባት የማንነት ጥያቄውን ለማዳፈን ወጣቶችን በማሸማቀቅ ከፍተኛ የሆነ የሥነ-ልቦና ጫና እያደረገ ነው'' ይላሉ።

አቶ አግዜ ጨምረውም ራያ አዘቦ፣ ራያ አላማጣ እና ኦፍላ የማንነት ጥያቄ የሚነሳባቸው ወረዳዎች ናቸው ብለዋል።
የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ኮሚኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በበኩሉ በፌስቡክ ገጹ ላይ ''የህዝብን የማንነት ጥያቄ በማስመሰል ሌላ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት እየተደረገ ያለው ሩጫ በማንኛውም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው።'' በማለት ተግባሩ ኮንኗል። ''ይህ ሳያንስ የዜጎች ሰላም፣ ፀጥታና ደህንነት ለመጠበቅ ከተሰማራው የፀጥታ መዋቅር ጋር መጋጨትና አነሳስቶ እርምጃ እንዲውስድ መግፋት ደግሞ በፍፁም መደገም የሌለበት ተግባር ነው'' በማለት የክልሉ የኮሚኒኬሽን ቢሮ በመግለጫው አትቷል። መግለጫው በዚህ ተግባር ላይ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የተሳተፉትን አካላት በቸልታ አላልፋቸውም ብሏል።

አላማጣ ወረዳን ወክለው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ረዳኢ ዝናቡ በበኩላቸው የወረዳው ነዋሪ በርካታ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ አለበት ካሉ በኋላ "በመልካም አስተዳደር እጦት ምክንያት እኛ ማንነታችን ራያ ነው፤ ስለዚህም በራሳችን ሰዎች መተዳደርና መዳኘት አለብን ማለት የጀመረ የህብረተሰብ ክፍል አለ" ብለዋል።

በትግራይ ምክር ቤት ውስጥ የወረዳው ህዝብ ተወካይ የሆኑት ወይዘሮ ጃኖ ንጉሰ ደግሞ "እኛ ትግራዋይም አማራም አይደለንም፤ እኛ ራያ ነን የሚሉም አሉ። ይህ ተግባር የፍትህ እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ያለበትን የህብረተሰብ ክፍል ለማጋጨት እየተደረገ ያለ ነገር ነው። እንደዚህ አይነት ጥያቄ በህጋዊ መንገድ መጠየቅ አለበት።" ብለዋል።

ምንጭ፦ BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update በሶማሌ ክልል #ጅጅጋ በሰልፈኞችና በፖሊስ መካከል በተፈጠረ ግጭት ቢያንስ ሁለት ሰዎች #ተገድለዋል። ስልፈኞቹ በአንድ ጎሳ ስር የተደራጁ ወጣቶች ናቸው። የክልሉ ፕሬዝዳንት #ሙስጠፋ_ዑመር በፌስ ቡክ ገፃቸው ሶማሊኛ ተናጋሪ ባልሆኑ ነዋሪዎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃትን መንግስት እንደማይታገስና ህጋዊ #እርምጃ እንደሚወስድ ገልፀዋል።

ምንጭ፦ ዋዜማ ራድዮ
ፎቶ፦ Rajo
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በደቡብ ክልል ካፋ ዞን፣ ደቻ ወረዳ ባለፈው ቅዳሜ 9 ሰዎች በድንገተኛ ጥቃት #ተገድለዋል፡፡ ጥቃቱ የተፈጸመው ባንድ ሠፈራ ጣቢያ ውስጥ መሆኑን ሪፖርተር የአካባቢውን ምንጮች ጠቅሶ አስነብቧል፡፡ በጥቃቱ ሌሎች 4 ሰዎች ክፉኛ ተጎድተዋል፤ ብዙ ንብረትም ወድሟል፡፡ ጥቃት አድራሾቹ ከዞኑ ጠረፋማ አካባቢዎች ወይም ከአጎራባቾቹ ቤንች ማጂና ደቡብ ኦሞ ዞኖች የመጡ መዔኒት የተባሉ አርብቶ አደር ጎሳ አባላት እንደሆኑ ተገምቷል፡፡

ምንጭ፦ ሪፖርተር(wazemaradio)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፈጣሪ ያውቃል⁉️

በረሐ እና ባሕር አቋርጠው ወደ ሳዑዲ አረቢያ የሚተሙት ኢትዮጵያውያን በየመን ጦርነት እንዳለ እንኳ አያውቁም። አንድ ወደ #ጅቡቲ የተሰደደ #የመናዊ በመንገድ ያገኟቸውን ኢትዮጵያውያን «ወዴት ነው የምትሔዱት? በመንገዳችሁ ጦርነት አለ ስንላቸው ፈጣሪ ያውቃል» የሚል መልስ ሰጡን ሲል ለኢኤንኤን ተናግሯል።

የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ድረ-ገፅ እደሚጠቁመው በየመን የርስ በርስ #ጦርነት

•5,900+ ሰላማዊ ሰዎች #ተገድለዋል

•9,400+ ሰላማዊ ሰዎች #ቆስለዋል

•3 ሚሊዮን ከመኖሪያ ቀያቸው #ተፈናቅለዋል

•22.2 ሚሊዮን ሕይወታቸውን ለማቆየት የለት ደራሽ ዕርዳታ #ጥገኛ ናቸው

•2.5 ሚሊዮን ሕፃናት ከትምህርት ገበታ እርቀዋል፤ ቢሆንም #ኢትዮጵያውያኑ ፈጣሪ ያውቃል እያሉ መንገድ ላይ ናቸው።

Via Eshet Bekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ባህር_ዳር

በባህር ዳር በተለምዶ #አባይ_ማዶ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ዛሬ ረፋዱን በነበረ የተኩስ ልውውጥ ሰዎች መሞታቸውን የዓይን እማኞች ለጀርመን ራድዮ ተናግረዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች እንደገለጹት ዛሬ ከምሳ ሰዓት በፊት የጸጥታ ኃይሎች “ተጠርጣሪ ለመያዝ” ተኩስ ከፍተው ነበር። ከዚያ በኋላ በነበረ የተኩስ ልውውጥ ተጠርጣሪውን ጨምሮ ቁጥራቸው በወል ያልታወቀ የጸጥታ ኃይሎች #ተገድለዋል ብለዋል። ስለጉዳዩ የተጠየቁት የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኃላፊ አቶ አበረ አዳሙ “ስብሰባ ላይ እንደነበሩ እና ሪፖርት እንዳልደረሳቸው” ለጀርመን ራድዮ ተናግረዋል።

Via #የጀርመን_ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አማራ : ለወራት የቀጠለው የትጥቅ ግጭት ዐውድ እና አሉታዊ የሰብአዊ መብቶች እንድምታው " ተፋላሚ ኃይሎች ሲቪል ሰዎችንና ንብረቶችን፣ የሕዝብ አገልግሎቶችን እና መሠረተ ልማቶችን ዒላማ ከማድረግ ሊቆጠቡ፣ መንግሥት የማኅበራዊ አገልግሎቶች እዲቀጥሉ አስቻይ ሁኔታ ሊፈጥር ይገባል። " በአማራ ክልል ጉዳይ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዛሬ የተላከልን መግለጫ ከላይ ተያይዟል። መግለጫው በክልሉ በተለያዩ…
#አማራ

በአማራ ክልል ለወራት ከቀጠለው የትጥቅ ግጭት ጋር በተያያዘ በርካቶች በድሮን ጥቃት መገደላቸው እና በክልሉ ከፍርድ ውጭ ግድያዎች መቀጠላቸውን ዛሬ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከተላከልን መግለጫ መረዳት ችለናል።

ከኢሰመኮ በደረሰን መግለጫ ፤ ከሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ባለው ጊዜ ውስጥ የአማራ ክልል ሁሉም ዞኖች በተለያየ ደረጃና ጊዜ የትጥቅ ግጭት ተካሂዶባቸዋል።

በተጨማሪም እነዚህ አካባቢዎችና ወረዳዎች በአንድ ወቅት ላይ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች በሌላ ወቅት ደግሞ በታጣቂው ቡድን (በተለምዶ ፋኖ በመባል የሚታወቀው) በቁጥጥር ስር ውለዋል።

የትጥቅ ግጭቱ በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ በከባድ መሣሪያ እና አልፎ አልፎ በአየር / ድሮን ድብደባ ጭምር የታገዘ ነው።

በግጭቱ ዐውድ ውስጥ #የአየር /#ድሮን መሣሪያን ጨምሮ በከባድ መሣሪያዎች ጥቃት የተነሳ በሲቪል ሰዎች ላይ ሞት እና የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን ፣ ሰዎች መኖሪያ አካባቢያቸውን ጥለው ለመሸሽ ተገደዋል።

ለምሳሌ ፦

- በሰሜን ሸዋ ዞን፣ በረኸት ወረዳ፣ ' መጥተህ ብላ ' ከተማ ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. በተፈጸመ የድሮን ጥቃት የአንድ ዓመት ከሰባት ወር ሕፃንን ጨምሮ በርካታ ሲቪል ሰዎች #ተገድለዋል፤ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

- በደብረ ማርቆስ ከተማ ጥቅምት 8 ቀን 2016 ዓ.ም. በተፈጸመ የድሮን ጥቃት  ቢያንስ 8 ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል

- በደንበጫ ከተማ ጥቅምት 3 ቀን 2016 ዓ.ም. በከባድ መሣሪያ ድብደባ ምክንያት ሲቪል ሰዎች ላይ የሞትና የአካል ጉዳት ደርሷል።

ኮሚሽኑ እነዚህን መረጃዎች ያገኘው የአካባቢውን ነዋሪዎች እና የዓይን ምስክሮችን በማነጋገር ነው።

በአንዳንድ አካባቢዎች ጥቃትን አልያም ግጭትን በመሸሽ ነዋሪዎች ሙሉ በሙሉ ከቀያቸው ተፈናቅለው በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለማረጋገጥ ተችሏል።

በምንጃር ወረዳ ውስጥ የአውራ ጎዳና ጎጥ ነዋሪዎች ከመስከረም 6 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ከቀያቸው ተፈናቀለው ቢያንስ 3ዐዐዐ የሚሆኑት አሞራ ቤቴ ቀበሌ በሚገኝ አንድ ትምህርት ቤትና ክፍት ሜዳ ላይ (በዛፍ ሥር) ተጠልለው የሚገኙ ሲሆን፣ ሌሎች ቁጥራቸው ያልታወቀ መተሃራና አዋሽን ጨምሮ ወደ የተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለዋል።

ለተፈናቃዮች የተወሰነ ድጋፍ በማኅበረሰቡና እና በአንድ ተራድዖ ድርጅት የተደረገ ቢሆንም፣ በቂ ባለመሆኑ በአሳሳቢ ሁኔታ እንደሚገኙ ለመረዳት ተችሏል።

የነዋሪዎችን መፈናቀል ተከትሎ ሰብላቸው እንደወደመ፣ ንብረታቸው እንደተዘረፈ፣ የቤቶቻቸው ጣራያ እና በር እየተነቀለ እንደተወሰደ፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ቤቶቻቸውን ከአጎራባች ክልል በመጡ ኃይሎች በኮንስትራክሽን መሣሪያዎች ጭምር ማፍረስ እንደተጀመረ ኢሰመኮ ያነጋገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎችና የመንግሥት ኃላፊዎች አስረድተዋል።

በመንግሥት የጸጥታ ኃይል አባላት የሚፈጸሙ ከሕግ ውጪ የሆኑ ግድያዎች አሁንም መቀጠላቸውን ኢሰመኮ ተዓማኒ መረጃዎችን እየተቀበለ እንደሚገኝ ገልጿል።

ግጭቱ በተካሄደባቸው አካባቢዎች የመንግሥት የጸጥታ አካላት በመንገድ ላይ ወይም ቤት ለቤት ፍተሻ በማድረግ ከያዟቸው በርካታ ሲቪል ሰዎች ውስጥ ፦

- " ፋኖን ትደግፋላችሁ "

- " ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ "

- " መሣሪያ አምጡ "


- " የተኩስ ድምጽ ስለተሰማበት አቅጣጫ መረጃ ስጡ " በሚልና ይህንን በመሰሉ ምክንያቶች ከሕግ ውጭ የሆኑ ግድያዎች መፈጸማቸውን የሚያሳዩ ተዓማኒ መረጃዎች ተገኝተዋል።

እንደማሳያ ፦

▪️በባሕር ዳር ሰባታሚት አካባቢ መስከረም 29 እና 30 ቀን 2016 ዓ.ም. #ሦስት_ወንድማማቾችን ጨምሮ በርካታ ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል

▪️በሰሜን ጎጃም ዞን፣ አዴት ከተማ መስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ፍልሰታ ደብረ ማሪያም የሚኖሩ 12 የአብነት ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል

▪️ በምሥራቅ ጎጃም ዞን፣ አማኑኤል ከተማ ጥቅምት 3 ቀን 2016 ዓ.ም. ቢያንስ 8 ሲቪል ሰዎች በቤት ለቤት ፍተሻ እንደተገደሉ ለማወቅ ተችሏል።

▪️በምሥራቅ ጎጃም ዞን፣ ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ፣ ግንደወይን ከተማ ሞጣ በር ተብሎ በሚጠራ አካባቢ መስከረም 18 ቀን 2016 ዓ.ም. አንድ በጥይት የቆሰለን ግለሰብ እናቱና እህቱ በባጃጅ አሳፍረው ወደ ሕክምና ተቋም በመውሰድ ላይ እያሉ፣ የመንግሥት የጸጥታ አካላት ባጃጁን አስቁመው ሁሉንም ተሳፋሪዎች ካስወረዱ በኋላ " የቆሰለው እኛን ሲዋጋ ነው " በሚል ምክንያት የባጃጅ አሽከርካሪውን ጨምሮ አራቱን ሰዎች በጥይት እንደገደሏቸው ኮሚሽኑ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች አስረድተዋል።

በባሕር ዳር፣ በፍኖተሰላም፣ በጎንደር እና በወልድያ ከተሞች በትጥቅ ግጭቱ ቆስለው ሕክምና ሲከታተሉ የነበሩ የተወሰኑ ሲቪል ሰዎች እና የታጣቂ ቡድኑ አባላት በመሆን በመንግሥት የጸጥታ አካላት የተጠረጠሩ ሰዎች ሕክምናቸው እዲቋረጥ ተደርጎ #ወዳልታወቀ_ስፍራ ከተወሰዱ በኋላ ፣ ከፊሎቹ ከተወሰኑ ቀናት በኋላ ወደ ሕክምና ተቋማቱ ሲመለሱ ቀሪዎቹ ያሉበት ሁኔታ ይህ መግለጫ እስከወጣበት ጊዜ ድረስ ማረጋገጥ አልተቻለም።
 
በሌላ በኩል በየደረጃው የሚገኙ ሲቪል የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች፣ ግድያዎችና እገታዎች በታጠቁ ኃይሎች ተፈጽመዋል።

ለምሳሌ ፦

መስከረም 28 ቀን 2016 ዓ/ም የአማራ ክልል ምክር ቤት የሕግ፣ ፍትሕና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢን ጨምሮ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ከባሕር ዳር ወደ ደብረ ታቦር ሲሄዱ ' አለምበር ከተማ ' አካባቢ በታጣቂዎች ተገድለዋል

በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ማረሚያ ቤቶችና ፖሊስ ጣቢያዎች ላይ ጥቃት በመሰንዘር ታራሚዎችና ተጠርጣሪዎች እንዲያመልጡ ተደርጓል። 
 
ኮሚሽኑ ባደረገው ክትትል ፤ በተለይም ከመንግሥት ተቋማት ጭምር በሚደርሱት መረጃዎች መሠረት በግጭቱ ዐውድ የሚፈጸሙ የአስገድዶ መድፈር ድርጊቶች በጣም አሳሳቢ እና በአፋጣኝ ተገቢው ምርመራ ተደረጎ አርምጃ ሊወሰድበት የሚገባው ነው፡፡

የሕክምና አገልግሎት ለማግኘት በተለያዩ የጤና ተቋማት መድረስ የቻሉትን ተጎጂዎች ቁጥር ብቻ መሠረት በማድረግ ከሐምሌ ወር 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ይህ መግለጫ እስከ ወጣበት ጊዜ ድረስ ቢያንስ #2ዐዐ_የአስገድዶ_መድፈር ተጎጂዎች በጤና ተቋማት ተመዝግበዋል፤ ከተጎጂዎች መካከልም የሀገር ውስጥ ተፈናቃይ ሴቶች እና የጤና ባለሞያ ሴቶች ጭምር ይገኙበታል።

ከትጥቅ ግጭቱ መስፋፋት ጋር ተያይዞ ፦
🔹ሲቪል ሰዎች እና የሲቪል የንግድ እና የመሠረተ ልማት ተቋማት ላይ ዝርፊያ ተፈፅሟል።
🔹የማሳ ላይ ሰብል ውድመት ጨምሮ በሲቪል ሰዎች፣ በሕዝብ እና በመሠረተ ልማት ላይ ጉዳት ደርሷል።
🔹ሕፃናት ከትምህርት ውጪ ሆነዋል በአንዳንድ አካባቢዎች የትምህርት ተቋማት ለወታደራዊ አገልግሎት ውለዋል። ይህ ደግሞ አፋጣኝ ትኩረት የሚሻ ነው።

በክልሉ ውስጥ በተለየ ሁኔታ ከተፈቀደላቸው ተቋማት በስተቀር ይህ መግለጫ እስከ ወጣበት ጊዜ ድረስ የኢንተርኔት አገልግሎት የተቋረጠ ሲሆን፣ በተለይም በግጭት ላይ ባሉ አካባቢዎች የስልክ አገልግሎትም ጨምሮ ተቋርጧል።

(ዛሬ ከ #ኢሰመኮ የተላከል ሙሉ መግለጫ በዚህ ታገኛላችሁ ፦ https://t.me/tikvahethiopia/82609?single)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Amhara ኢሰመኮ፦ - ከየካቲት 15 እስከ 28 ቀን 2016 ዓ/ም በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ደጋ ዳሞት ወረዳ (ዝቋላ ወገም፣ ፈረስ ቤት01፣ ገሳግስና ጉድባ ሰቀላ ቀበሌዎች) እና ሰከላ (አጉት፣ ጉንድልና አምቢሲ ቀበሌዎች እና ግሼ ዓባይ ከተማ) በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎችና በታጣቂዎች መካከል የተካሄዱ የትጥቅ ግጭቶችን ተከትሎ በሲቪል ሰዎች ላይ ሞት፣ አካል ጉዳትና የንብረት ውድመት ደርሷል። - የካቲት 20/2016…
#Oromia

ኢሰመኮ ፦

- ታኀሣሥ 15 ቀን 2016 ዓ.ም. በግምት ከጠዋቱ 1፡30 ሰዓት አካባቢ በኦሮሚያ ክልል በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ጉዱሩ ወረዳ ውስጥ በተፈጸመ #የድሮን_ጥቃት
° በየነ ጢቂ፣
° ጉደታ ፊጤ፣
° ሀብታሙ ንጋቱ፣
° ታዴ መንገሻ፣
° ዳመና ሊካሳ፣
° ዱጋሳ ዋኬኔ፣
° ሕፃን አብዲ ጥላሁን
° ሕፃን ኦብሳ ተሬሳ የተባሉ 8 ሰዎች ተገድለዋል

በተጨማሪም፦
• ስንታየሁ ታከለ፣
• ሽቶ እምሩ፣
• ተሜ ኑጉሴ
• አለሚ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል። በአካባቢው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶ “ #ኦነግ_ሸኔ ”) በሰፊው ይንቀሳቀስ የነበረ መሆኑን እና የሀገር መከላከያ ሰራዊት በአካባቢው በሚደረጉ ውጊያዎች አልፎ አልፎ #በድሮን_ይጠቀም የነበረ መሆኑን ኢሰመኮ ያነጋገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።

- ጥር 9/2016 ዓ/ም በሰሜን ሸዋ ዞን ፤ ደራ ወረዳ የሀገር መከላከያ ሰራዊት #ለሌላ_ግዳጅ አካባቢውን ለቅቆ ይወጣል። ይህን ተከትሎም የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (ኦነግ ሸኔ) ታጣቂዎች በማግስቱ አካባቢውን ከተቆጣጠሩ በኋላ “ ለመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ምግብ ስታቀርቡ ነበር ” በማለት 01 ቀበሌ የሚገኘው ሳላይሽ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ጥበቃ የነበሩት አቶ ስዩም ካሴን #በጥይት_በመምታት ገድሏል። አቶ ከበደ ዓለማየሁ የተባሉ ነዋሪን ከመኖሪያ ቤታቸው አስወጥተው ከወሰዷቸው በኋላ በአካባቢው ጫካ አስክሬናቸው ወድቆ ተገኝቷል።

- ጥር 13 ቀን 2016 ዓ/ም ከጠዋት 2 ሰዓት ጀምሮ ማንነታቸው ያልታወቀ ታጣቂዎች በምዕራብ ጉጂ ዞን፣ ገላና አባያ ወረዳ ኤርገንሳ ቀበሌ ለሚኖሩ ነዋሪዎች የኩፍኝ በሽታ ክትባት ለመስጠት በመጓዝ ላይ በነበሩ ሠራተኞች ላይ በፈጸሙት ጥቃት የገላና አባያ ወረዳ አስተዳደር ጤና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊን ጨምሮ ሁለት ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል። እንዲሁም 3 ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

- ከየካቲት 28 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ በአማራ ክልል ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ #የአማራ_ታጣቂ_ቡድኖች የኦሮሚያ ክልል ፤ በሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ በሚገኙ አዋሳኝ ቀበሌዎች በሲቪል ሰዎች ላይ #በተከታታይ በፈጸሟቸው ጥቃቶች ፦
➡️ 25 ሲቪል ሰዎችን ገድለዋል ፤ 
➡️ 4 ሲቪል ሰዎች ላይ የአካል ጉዳትን አድርሰዋል
➡️ ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ ሲቪል (ሰላማዊ) ሰዎችን #አግተው ወስደዋል። በታጣቂዎቹ በተፈጸመ ጥቃት በርካታ የመኖሪያ ቤቶች ተቃጥለዋል።

- በሰሜን ሸዋ ዞን ፤ ደራ ወረዳ የሚንቀሳቀሱ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶው “ ኦነግ ሸኔ ”) ታጣቂዎች ከኅዳር ወር 2016 ዓ/ም ጀምሮ በወረዳው በሚገኙ የተለያዩ ቀበሌዎች በሲቪል ሰዎች ላይ በፈጸሟቸው ጥቃቶች ፦
➡️ 15 ሲቪል (ሰላማዊ) ሰዎች #ተገድለዋል
➡️ ቁጥራቸው ለጊዜው በትክክል ያልታወቀ በርካታ ነዋሪዎችን #አግተው_ወስደዋል
➡️ በርካታ የቀንድ ከብቶችን ዘርፈዋል
➡️ መኖሪያ ቤቶችን አቃጥለዋል።

- መጋቢት 1/2016 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ ስልካምባ ከተማ ላይ የኦሮሞ ነጸነት ሰራዊት (በተለምዶ “ #ኦነግ_ሸኔ ”) ታጣቂዎች በከፈቱት ጥቃት የወረዳው አበዪ ሄቤን ቀበሌ ነዋሪ የነበሩ አቶ ሹመቴ ፋርስ እና ወ/ሮ ተቀባ አበጋዝ የተባሉ አረጋዊያን በመኖሪያ ቤቶቻቸው ፊት ለፊት ተገድለዋል

- መጋቢት 16/2016 ዓ/ም ከምሽቱ 3፡00 እስከ 5፡00 ባሉት ሰዓታት ማንነታቸው ያልታወቀ የታጠቁ ቡድኖች በምዕራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ከተማ 02 ቀበሌ ውስጥ 7 ሰዎችን ተኩሰው መግደላቸውን ለማወቅ ተችሏል። በዕለቱ በተፈጸመ ጥቃት የቀበሌው ነዋሪ የሆነ እና የምዕራብ አርሲ ሃገረ ስብከት የዶዶላ ደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የሆነ ግለሰብ ፣ ከባለቤቱ እና #ከ2_ልጆቹ ጋር በመኖሪያ ቤታቸው እያሉ እንዲሁም ሌላ አንድ ዲያቆን ከባለቤቱ እና ከእህቱ ጋር በመኖሪያ ቤታቸው መገደላቸውን ለማወቅ ተችሏል። 

- መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ/ም በዶዶላ ወረዳ በደነባ ቀበሌ በግምት ከምሽቱ 5፡00 ሰዓት አካባቢ ላይ 4 የቀበሌው ነዋሪዎች ማንነታቸው ባልታወቀ የታጠቁ ሰዎች/ቡድኖች በጥይት ተመተው ሲገደሉ 5 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ለማወቅ ተችሏል።

- የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ( በተለምዶ “ #ኦነግ_ሸኔ ” ) በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን፣ አመያ ወረዳ ውስጥ “ የመንግሥት ሠራተኞች እና የመንግሥት ጸጥታ ኃይል አባላት ቤተሰቦች ናችሁ ” በሚል ወይም “ለመንግሥት አካላት ትብብር አድርጋችኋል” በሚል ምክንያት በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች በየካቲት እና ሚያዝያ ወራት በፈጸማቸው ተከታታይ ጥቃቶች በሲቪል ሰዎች ላይ ግድያ፣ አካል ጉዳት፣ እገታ፣ ንብረት ውድመት እና ዘረፋ ፈጽሟል።

ለምሳሌ ፦

👉 በወረዳው አቡዬ ጀብላል ቀበሌ የካቲት 7/ 2016 ዓ.ም. በፈጸመው ጥቃት 11 ሲቪል ሰዎችን ገድሏል፤ መኖሪያ ቤቶችንና ሞተር ብስክሌቶችን አቃጥሏል፤ የቀንድ ከብቶችን ዘርፏል።

👉 መጋቢት 27/2016 ዓ.ም. በወረዳው ቆታ ከተማ ላይ በፈጸመው ጥቃት 31 ሲቪል ሰዎችን ገድሏል፣ 3 ሲቪል ሰዎችን አቁስሏል፣ የቀንድ ከብቶችንና ሌሎች ንብረቶችን ዘርፏል እንዲሁም ንብረቶችን አቃጥሏል።

👉 ሚያዝያ 8/2016 ዓ/ም በደራ ቲርቲሪ ቀበሌ ላይ ታጣቂ ቡድኑ በፈጸመው ጥቃት 2 ሲቪል ሰዎችን ገድሏል ፣ ከ100 በላይ የተለያዩ የቀንድ ከብቶች ዘርፏል።

👉 በሚያዝያ 13/2016 ዓ/ም በጎምንቦሬ አሊይ ቀበሌ 36 የቀንድ ከብቶችንና 3 የሞቶር ብስክሌት ዘርፏል።

#Oromia #Ethiopia #EHRC

@tikvahethiopia