TIKVAH-ETHIOPIA
1.41M subscribers
55K photos
1.37K videos
199 files
3.67K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#updateየቡራዩ ከተማ ፖሊስ⬆️

የቡራዩ ከተማ ፖሊስ በተለያዩ ቀበሌዎች የጸጥታ አካላት ደንብ ልብስ፣ የጦር መሳሪያ፣ ገንዘብ እና ሌሎች ቁሳቁሶችን #በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል።

በግለሰቦች መኖሪያ ቤትና በተሸከርካሪዎች ላይ በተደረገ ፍተሻ የአዲስ አበባ ፖሊስና የአገር መከላከያ ሰራዊት ደንብ ልብስ፣ 3 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 5 ሽጉጥ፣ የተለያዩ ህገወጥ ማህተሞች፣ 45 ሺህ ብርና ሌሎች ድምጽ አልባ መሳሪያዎች ተይዘዋል።

እንዲሁም #ግጭቱን ለማስተባበር ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሁለት ቪትስ መኪናዎች ከነአሽከርካሪያቸው ጋር መያዙን የከተማዋ ፖሊስ ጠቁሟል።

የከተማዋ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኮማንደር ደረጀ ባይሳ እንደተናገሩት፤ በቡራዩና አካባቢዋ በደረሰውን ጥቃት የተጠረጠሩ ሰዎች ህብረተሰቡ በሰጠው ጥቆማ መሰረት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል።

“ከዚህ #ወንጀል በስተጀርባ ያሉ የተለያዩ ዕቃዎችም ተይዘዋል።ሽጉጦች፣ ክላሾች፣ በዚህ በወንጀል ድርጊቱ በሰው ግድያ ላይ በተለይ የተጠረጠሩ ሰዎች ተይዘዋል። እነዚህ ሰዎች #እንዲጨፋጨፉ፣ ለወንጀል ድርጊት እና #ለሞት መንስዔ የሆኑ ናቸው ተብሎ ህብረተሰቡ በሰጠን ጥቆማ፣ በሁለት ቪትስ መኪና እየተንቀሳቀሱ የተያዙ ሰዎች ምርመራ እየተደረገባቸው ነው። ውጤቱ ለህዝብ ይፋ ይሆናል።

በዚህ ሂደት የተለያዩ ዩኒፎርሞች፣ የተለያዩ ዕቃዎች፣ የቢሮ ማህተሞች ተይዘዋል። ከዚህ ከግድያ ጋር ላይያያዝ ይችላል። የተለያዩ የሚሊተሪ፣ የፖሊስ ልብስ ተይዘዋል። ፖሊስ አስመስሎ፣ ፖሊስ እንደዚህ አደረገ በማለት ይህን በመልበስ የክልሉን ፖሊስ ስም በማጥፋት የሚንቀሳቀሱ ሰዎች ይሆናሉ ብለን የያዝነው አለ በምርመራ፣ በቁጥጥር ስር ውሎ-#እያጣራን ነው። የአገር መከላከያ ደንብ ልብስ እራሱ ሬንጀር ለብሶ ከቤቱ የተገኘ ስላለ እሱንም የአገር መከላከያ ሰራዊት ስም ለማበላሸት እነሱ ናቸው እንደዚህ የሚያደርጉ የሚል ግምት ስላለ እሱንም አሁን በቁጥጥር ስር አውለን ከዚህ ጋር በተያያዘ ወደ 8 ሽጉጥ፣ 3 ክላሽ ተይዞ በዚህ ይዞ ሲንቀሳቀሱ ያየነው አሁን በቁጥጥር ስር አውለን እያጣራን ነው።

ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ ግለሰቦች ላይ ኮሚቴ ተቋቁሞ ምርመራ እያካሄደ እንደሆነ የተናገሩት አዛዡ በጥቃቱ የደረሰውን ጉዳት የማጣራት ስራ እየተሰራ እንደሆነ ጠቁመዋል።

ፖሊስ የከፋ ጉዳት እንዳይከሰት ከወጣቶች፣ ከአድማ በታኝ ፖሊስና ከማህበረሰቡ ጋር በመሆን ችግሩን ለመቆጣጠር የተለያዩ ስራዎች ሰርቷል።

እስከ ትናንት ድረስ በወንጀሉ ተጠርጥረው የተያዙት ሰዎች ቁጥር ከ200 በላይ መድረሱን ተናግረዋል።

በደረሰው ጥቃት የተፈናቀሉ ወገኖች ቢኖሩም ድርጊቱ #የኦሮሞ ተግባር #ሳይሆን የተጀመረው አገራዊ ለውጥ እንዳይቀጥል የሚፈልጉ ሃይሎች ተግባር እንደሆነ በመግለጽ ሳይፈናቀሉ የቀሩ ሰዎች እንዳሉ ገልጸዋል።

የተፈናቀሉ ወገኖችን ለመመለስ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ አባላት ያለው ኮሚቴ ተቋቋሞ እየተሰራ እንደሆነ የጠቆሙት ምክትል ኮማንደር ደረጀ ህብረተሰቡ የተፈናቀሉትን ዜጎች ለመቀበል ዝግጁ እንደሆነ ተናግረዋል።

የፖሊስ አዛዡ ከዚህ በኋላ በዜጎች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ህግ የማስከበር ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል እንደሚሆን ጠቁመዋል።

©OBN
@tsegabwolde @tikvahethiopia