TIKVAH-ETHIOPIA
1.49M subscribers
56.5K photos
1.41K videos
203 files
3.84K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
" የተስፋፋዉ የሙስና ሰንሰለት ሙሉ በሙሉ የሀብታም ልጅ በገንዘቡ ፤ የባለስልጣንም ልጅ በስልጣኑ ስራ እንዲቀጠር ሲያደርገው ሌላው የድሀ ልጅ ከስራ ውጭ አድርጎታል ! " - ነዋሪዎች (ከሰሞኑን በሚዛን አማን በነበረ ህዝባዊ ውይይት ላይ የተነሳ) #ቲክቫህኢትዮጵያ @tikvahethiopia
" የሀብታም ልጅ #በገንዘቡ የባለስልጣን ልጅ #በስልጣኑ ስራ እንዲቀጠር ሲያደርገዉ ሌላዉን የድሀ ልጅ ከስራ ውጭ አድርጎታል " - ነዋሪዎች

ሰሞኑን በሚዛን አማን ከተማ ህዝባዊ የውይይት መድረክ ተካሂዶ ነበር።

ይኸው ውይይት በደቡብ ኢትዮጵያዊ ህዝቦች ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደና በቤኒሻንጉል ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ የተመራ ነበር።

በህዝብ ወይይቱ በርካታ ጥያቄዎች ቀርበዋል።

ከነዚህ መካከል ፦

እንደካሮት ቁልቁል የሚሄደዉ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ለምን ባለቤት አጣ ? ተመዘበረበት የተባለዉን ገንዘብ ጉዳይ የያዘዉ የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ወዴት አደረሰው ?

ያለብን የመንገድ ችግር አሁንም እናቶች በህክምና እጦት #ለሞት እየዳረገ ነው። መፍትሄ ለምን አይሰጥም ? የሚሉት ይገኙበታል።

ሌላው የተስፋፋዉ የሙስና ሰንሰለት ሙሉ በሙሉ የሀብታም ልጅ በገንዘቡ ፤ የባለስልጣን ልጅ በስልጣኑ ስራ እንዲቀጠር ሲያደርገዉ ሌላዉን የድሀ ልጅ ከስራ ዉጭ አድርጎታል ሲሉ የውይይቱ ተሳታፊዎች ያላቸውን ከፍተኛ ቅሬታ አሰምተዋል።

ተሳታፊዎቹ መንግስት ቁርጠኛ አመራር በመስጠት ስርአቱን ሊያስተካክለዉ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በእለቱ መድረኩን የመሩት የደቡብ ኢትዮጵያዊ ህዝቦች ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ፤ ፣ ሌብነትና ብልሹ አሰራር በመንግሥት በኩል ቀይ መስመር በማለት ያስቀመጠዉ ጉዳይ ነው " ሲሉ  ገልጸው ችግሩን በመቅረፉ ሂደት ህዝቡ ከመንግስት ጎን ሊቆምና ሊታገል ይገባል ብለዋል።

መረጃው በሀዋሳው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል የተዘጋጀ ነው።

@tikvahethiopia