TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.6K photos
1.39K videos
200 files
3.74K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ?

የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ፤ በውስጡ ባለው #ሙስና እና ብለሹ አሰራሮች ምክንያት እጅግ በርካቶች ይማረሩበታል፤ በተደጋጋሚ ጊዜ የዚህ መስሪያ ቤት ጉዳይ ቢነገርም ችግሩ ግን ዛሬም ድረስ ሊቆም አልቻለም።

ዜጎች #በህጋዊ መንገድ ማግኘት ያለባቸውን አገልግሎት በሙስና ሰንሰለት በተጣመሩ አካላት ምክንያት ከፍተኛ ክፍያ እንዲከፍሉና ከሌሎች በፊታ ያለ አንዳች ወረፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ይደረጋል።

በዚህ መስሪያ  ቤት የአገልግሎት አሰጣጥ የሚማረሩ፣ የሚበሳጩ እና እንግልት የደረሰባቸው በርካቶች ናቸው።

ከሰሞኑን ደግሞ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣብያ (ኢቲቪ) አንድ የምርመራ ጋዜጠኝነት ስራ ሰርቶ አየር ላይ አውሎ ነበር።

በዚህ የምርመራ ስራም በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ውስጥ ፦

-   በፓስፖርት እድሳት እና ከአስቸኳይ ፓስፖርት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ ዜጎች ለሕገ-ወጥ አሠራር ተጋላጭ ሆነዋል።

- በሕጋዊ መንገድ ከ6 ሺህ 500 ብር በታች በሆነ ወጪ መጨረስ የሚቻለውን ፓስፖርት እስከ 40 ሺህ ብር በመክፈል አገልግሎት እንዲያገኙ እንደሚደረግ ተረጋግጧል።

- ዜጎች መብታቸው ለሆነው አገልግሎት ሕገ-ወጥ ክፍያ እንዲከፍሉ ይጠየቃሉ ፤ ተቋሙ ባለበት አካባቢ እስከ ውስጥ ድረስ የተያያዘ የሙስና ሰንሰለት አለ።

ለመሆኑ ይህ ተቋም ይህን ሁሉ ችግሮች ለመቅረፍ ምን እያደረገ ነው ?

ቃላቸው ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ የሰጡት የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳሬክተር አቶ ብሩህተስፋ ሙሉጌታ  ፦

" ከ33 በላይ የተቋሙ ሠራተኞች ላይ የሥነ -ምግባር እርምጃ ቢወስድም ዛሬም ግን በሙስና እና በብልሹ አሠራር እየተፈተንን ነው።

ዜጎች በተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ቅሬታ ካላቸው ከቅሬታ ሰሚ ዴስክ አንሥቶ እስከ ተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ድረስ በመገናኘት ቅሬታቸውን ቢያሰሙ እርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ ነን። 

ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታትም 95 በመቶ የሚሆነው ከፓስፖርት ሕትመት ጋር ተያይዞ ያሉ ግብዓቶች ጭምር በሀገር ውስጥ እንዲሆኑ የሚያስችሉ ሥራዎች ተጠናቀዋል።

አገልግሎቱ እንዲጓደል የሚያደርጉ የተቋሙ ሠራተኞች በቅርብ በሚካሄድ የአደረጃጀት ሪፎርም ላይ ይጋለጣሉ እርምጃም ይወሰድባቸዋል። " ሲሉ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
🇪🇹 የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹

" መንግሥት የሰውን ሞት ትኩረት እየሰጠው አይደለም " ሲል እናት ፓርቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ለሰጠው ቃል ወቅሷል።

ድርጊቱን ማስቆም እንዳለበትም አጥብቆ ጠይቋል።

እናት ፓርቲ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበረው ቆይታ ምን አለ ?

Q. ፓርቲው አሁናዊ የኢትዮጵያ የጸጥታ እና ደህንነት ሁኔታ እንዴት ይገመግመዋል ? በምን ደረጃ ላይ ይገኛል ? 

እናት ፓርቲ ፦

" አገራዊ ሁነቱ የውድቀት አፋፍ ላይ ነው ያለው። ኢትዮጵያ ከእግዚአብሔር ጥበቃ በታች የመጨረሻ የሚባለውን ሰቆቃ እያየች ነው።

ሰው በሰላም ወጥቶ የማይገባባት፣ የሰው ሞት የእንስሳትን ሞት ያህል የማያስጨንቅበት ጊዜ ላይ ደርሰናል።

በሌላ ጎን ሞቱ አለ፤ በሌላ መንገድ ደግሞ ሞቱን የሚንቅ አለ። ‘ይሄ በለውጥ ሂደት ውስጥ የሚያጋጥም ነውና እኔ ትክክለኛ ስራዬን እየሰራሁ ነው ፤ ከእኔ ስንፍናና ጉብዝና የሚገናኝ አይደለም ' ብሎ የሚያምን፣ ለሕዝብ ሞት እውቅና የማይሰጥ ስርዓት ነው ያለው። "

Q. መፍትሄው ምንድን ነው ?

እናት ፓርቲ ፦

" የአማራ ሕዝብ የህልውና አደጋ፣ ከፍተኛ መከፋት ውስጥ ወድቋል። እናም መንግሥት እሰጥ አገባውን አቁሞ ወደ ድርድር መምጣት አለበት። 

ድርድሩ ደግሞ ቄስ፣ ሼይኽ በመላክ አይሆንም። ምክንያቱም ይሄ ስርዓት እንዲህ አይነት እሴቶችን የሚያከብር ይመስላል እንጂ አይቀበልም።

የሚቀበለው ባለዶላር ፤ ባለዩሮዎችን ነው። ስለዚህ እነሱ በተገኙበት ለ “ ሸኔ ” እንደተደረገው ቁጭ ብሎ መነጋገሩ የተሻለ ነው። "

Q. “ መርጦ አልቃሽ ናችሁ ” የሚል አስተያዬት ለፓርቲያችሁ ይሰጣል ፤ ለዚህ ምላሻችሁ ምንድን ነው ?

" በኢትዮጵያ ፓለቲካ ውስጥ ትግራይ፣ በተለይ አማራ፣ በሃይማኖት ደግሞ ኦርቶዶክስ በፍጹም ታርጌት ተደርጎ ይገደላል። ይሄ ማለት ኦሮሞ ውስጥ ያለው ኦሮሞ አይገደልም ማለት አይደለም። 

በእስልምናውም በክርትናውም ነባር በሆኑት ተደጋጋሚ ግድያ ይደረጋል። በዛ ምክንያት ሞቅ ብሎ ተሰምቶ ሊሆን ይችላል።

ሞቅ ብሎ የተሰማው ግን በተግባር የተደረገ ነው። አልተደረገም ብሎ የሞገተን አካል የለም፤ ሊኖርም አይችልም፤ እውነት ነውና። "

Q. እንደ ፓርቲ ደረሰብን የምትሉት ጫና ምንድን ነው ?

እናት ፓርቲ ፦

" በአመራሮች ላይ እስራት እየተፈጸመ ነው። ለአብነትም የወልዲያና አካባቢው ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዶክተር ደርበው ከዋሽ አርባ በእስር እየማቀቀ ይገኛል። 

ምርጫ ቦርድ የተሻለ ነበር በዘመነ ብርቱካን፤ አሁን ‘ለምን’ ብሎ የሚጠይቅ የለም። ስብሰባ መሰብሰብ፣ በአካል ማግኘት አይቻልም።

ፓለቲካ ላይ መስራትን በእሳት እንደ መጫወት ነው ያደረገው ስርዓቱ። "

Q. በቀጣይ ይደረጋል ተብሎ ለሚጠበቀው ሀገራዊ ምርጫ ምን አይነት ዝግጅት እያደረጋችሁ ነው ? ለህዝብ አማራጭ ሆኖ ለመቅረብ እየተዘጋጃችሁ ነው ?

እናት ፓርቲ ፦

" ዝግጅት እያደረግን ነው። እውነትም ምርጫ አለ ወይ ? የሚለው ጥያቄ በሁላችንም አዕምሮ የሚመላለስ ቢሆንም እያደር የምንገልጻቸው ጉዳዮች ይኖራሉ። በምርጫ ተሳትፈን ማሸነፍ ነው በቸኛው አማራጫችን። "

📱 ቲክቫህ ኢትዮጵያ በተከታታይ የሌሎች #በህጋዊ_መንገድ ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎችን ሁሉ ሀሳብ ያቀርባል።

በተለይም ፦
- ስለሀገራዊ ጸጥታ እና ደህንነት ጉዳይ ያላቸውን ግምገማ
- ስለዜጎች የሰብዓዊ መብት ፣
- ስለብልሹ አሰራር
- ስለኑሮ ሁኔታ
- ስለቀጣዩ ምርጫ አማራጭ ሆኖ ለመቅረብ ስላላቸው ዝግጅት በዋነኝነት ያነሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM