TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.6K photos
1.39K videos
200 files
3.74K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ፎቶ ፦ በአማራ ክልል ፣ ባህር ዳር ከ60 ዓመታት በላይ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረውን ድልድይ የተካው በታላቁ የዓባይ ወንዝ ላይ የተገነባው " የዓባይ ድልድል " ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል።

የግንባታው ውል በ2011 ነበር የተፈረመው።

ስራውን #የቻይናው ኮምኑኪዬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ በኃላፊነት የወሰደ ሲሆን ቦቴክ ቦስፈረስ የተባለ የቱርክ ድርጅት እና ከስታዲያ ኢንጅነሪንግ ስራዎች የተባለ ሀገር በቀል ተቋም በጋራ ሆነው የማማከር ስራ ሰርተዋል።

ድልድዩ የ380 ሜትር ርዝማኔ አለው፡፡

የጎን ስፋቱ 43 ሜትር ሲሆን በግራ እና በቀኝ በአንድ ጊዜ 6 ተሽርካሪዎች ማስተናገድ ይችላል።

5 ሜትር የእግረኛ መሄጃ የተሰራለት ሲሆን በሁለቱም አቅጣጫ ለብስክሌት ተጠቃሚዎች የሚሆን መስመርን አካቷል።

ግንባታው በአጠቃላይ 1,437,000,000 ብር ወጪ እንደወጣበትና ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት እንደተሸፈነ ተገልጿል።

#AmharaCommunication
@tikvahethiopia