TIKVAH-ETHIOPIA
1.47M subscribers
56.1K photos
1.4K videos
202 files
3.8K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
“ 1.2 ቢሊዮን የምስኪን ሕዝብን ገንዘብ 4 ዓመታት ሙሉ ኦክሎክ ጀነራል ትሬዲንግ እየተጠቀመበት ነው። በውላችን መሠረት መኪና አላስረከበንም ” - የቱሪስት ታክሲ ማኀበራት በስራቸው ከ2,800 በላይ አባላት ያሏቸው ከ40 በላይ የሚሆኑ ሕጋዊ የቱሪስት ታክሲ ማኀበራት ከ3 ዓመታት በፊት " ከኦክሎክ ትሬዲንግ/ኃላ/የተ/የግ/ ማኀበር " መኪና እንዲቀርብላቸው ቢዋዋሉም መኪናው ሳይቀርብ የውል ገደቡ እንዳለፈ፣…
#Update

ኦክሎክ ሞተርስ “ስሜን አጥፍቷል” ላለው ቱሪስት ታክሲ ማኀበራት ምን ምላሽ ሰጠ ?

ኦክሎክ ጀነራል ትሬዲንግ ኃላ/የተ/የግ/ማኀበር ፤ በቱሪስት ታክሲ ማኀበራት " የስም ማጥፋት ዘመቻ ተፈጽሞብኛል " በማለት ኮንኗል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ የኦክሎክ ጀነራል ትሬዲንግ ኃላ/የተ/የግ/ማኀበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ታመነ ካሳሁንን የድርጅቱ ስም ጠፋ ያሉበትን ምክንያት ጠይቋል።

አቶ ታመነ ካሳሁን ፦

“ ‘ሕዝቡ ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ድሃዎችን እያስለቀሰ ነው። 1.2 ቢሊዮን ብር ወስዶ እየሰራበት ነው’ የሚለው በሕዝብም በመንግሥትም ዘንድ ተቀባይነት እንድናጣ ለማድረግ የተደረገ ሩጫ ነው። ” ብለዋል።

በተጨማሪ ፦

“ ... እነዚህ ሰዎች (1.2 ቢሊዮን ብር ከፈሉ የተባሉት) የከፈሉት 110 ሚሊዮን ብር ነው። ያመጣነው መኪና ግቢ ውስጥ እንኳ የቆመው ብቻ 200 መኪና ነው። 200 መኪና በትንሹ እንኳ በ1 ሚሊዮን 950 ሺሕ ብር ስናባዛው ከ400 ሚሊዮን በላይ ነው። ስለዚህ የዛን ያህል ዋጋ ከፍለን ስናመጣ እኛ ከእነርሱ (ከማኀበራቱ) የተቀበልነው ገንዘብ ግን ያን ያህል (110 ሚሊዮን ብር) ነው ” ሲሉ ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦

- ኦክሎክ #ከሄሎ_ታክሲ ጋር የነበረው ውል ምንድን ነው ? ለምን ተቋረጠ ?
- የቱሪስት ታክሲ ማኀበራት አባላት ፥ “ ኦክሎክ በስማችን የመጣውን መኪና #እየሸጠ_ነው ” ስለሚለው ምን ምላሽ አላችሁ ? የሚሉና ሌሎችም ጥያቄዎች አቅርቧል። የኦክሎክ ሥራ አስኪያጅ በዚህ ላይ ምላሽ ሰጥተዋል።

በዝርዝር ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-04-07-2

@tikvahethiopia