TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.4K photos
1.39K videos
199 files
3.72K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ኢትዮጵያ

በነዳጅ የሚሠሩ እንዲሁም ሙሉ በሙሉ ውጪ ተገጣጥመው ወደ ሃገር ውስጥ በሚገቡ አውቶሞቢሎች ላይ የውጪ ምንዛሬ እቀባ ተደረገ።

የጉምሩክ ኮሚሽን በነዳጅ የሚሠሩ እና ሙሉ በሙሉ ውጭ ተገጣጥመው ወደ ሃገር  የሚገቡ አውቶሞቢሎች ላይ የውጪ ምንዛሬ እቀባ መጣሉን አሳውቋል።

ዕቀባው ያስፈላገበት ዋና ምክንያት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ እና በሃይብሪድ /በኤሌክትሪክ እና በነዳጅ/ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሃገር ውስጥ እንዲገቡ ለማበረታት ነው ተብሏል።

አሰራሩ ፥ የአረንጓዴ ልማትን ተግባራዊ ለማድረግ እና ለነዳጅ እና በነዳጅ ለሚሰሩ አውቶሞቢሎች ግዢ ይወጣ የነበረውን የውጪ ምንዛሬ ለመቀነስ ይረዳል ሲል ኮሚሽኑ አመልክቷል።

ይህ እቀባ #ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚችል ተገልጿል።

በነዳጅ የሚሠሩ አውቶሞቢል ተሽከርካሪዎችን ወደ ሃገር ውስጥ የሚያስገቡ አስመጪዎችም ጥንቃቄ እንዲያደርጉ #ማሳሰቢያ ተላልፏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው ከገቢዎች ሚኒስቴር ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba “ በለበሰው ሹራብ የኮፍያ ገመድ አንቀው ነው የገደሉት። ተሽከርካሪውን ይዘው ተሰውረዋል ” - የሟች ቤተሰብ “ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የተለያዩ ሥራዎች እየተሰሩ ነው ” - የአዲስ አበባ ፓሊስ ወጣት ሶፎኒያስ አስራት የሚባል ሹሬር ማክሰኞ መጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ/ም ከሌሊቱ 8 ሰዓት ገደማ ሰዎችን አሳፍሮ እንደወጣ አለሙለሱን፣ በመጨረሻም ሹፌሩን ገድለው ፣ ተሽከርካሪውን…
#Update

ወጣት ሶፎኒያስ አስራትን ገድለው ተሽከርካሪውን ዘርፈው የተሰወሩ ' ማንነታቸው ያልታወቁ ' ወንጀል ፈፃሚዎችን በ48 ሰዓት ውስጥ ከዘረፉት ተሽከርካሪ ጋር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

ሟች ወጣት ሶፎኒያስ መጋቢት 24/2016 ዓ/ም ከንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ናሆም ሆቴል አካባቢ ከሌሊቱ 8፡00 ሰዓት ላይ ማንነታቸው የማይታወቁ 3 ግለሰቦችን አሳፍሮ ወደ ቦሌ ሚካኤል ለማድርስ መሄዱን ጉዳዩን ለመከታተል የተቋቋመው የፖሊስ የምርመራና የክትትል ቡድን አባላት ባደረጉት ክትትል አረጋግጠዋል።

ወንጀል ፈፃሚዎቹ ወንጀል ለመፈፀም አቅደው እና ተደራጅተው የትራንስፖርት አገልግሎት ፈላጊ መስለው ሹፌሩን በመቅረብ ከተሳፈሩ በኋላ አንገቱን በገመድ አንቀው በመግደል አስክሬኑን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 አሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ አካባቢ ወደ አቦ ቤተክርስቲያን በሚወስደው መንገድ ላይ በመጣል አይነቷ ቪትዝ የሴሌዳ ቁጥር ኮድ ' 2A 93488 ' ተሽከርካሪ ጨምሮ 2 ሞባይል ስልኮችን ዘርፈው ይሰወራሉ፡፡

ፖሊስ ሌት ተቀን ባደረገው ብርቱ ክትትል ወንጀል ፈፃሚዎቹ የሰረቁትን ተሽከርካሪ ለመሸጥ እየተስማሙ መሆኑን በበቂ ማስረጃ ካረጋገጠ በሗላ ክትትሉን በመቀጠል ሦስቱን ዋና ወንጀል ፈፃሚዎች የሰረቁትን መኪና በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ቦሌ ቡልቡላ አካባቢ ለመሸጥ እየተደራደሩ እንዳለ በቁጥጥር ስር በማዋል የተሰረቀችውን መኪና ፣ 2 ሞባይል ስልኮችን ልዩ ልዩ ኤግዚቢቶችን ይዞ ምርመራውን መቀጠሉን ገልጿል።

ፖሊስ ባደረገው ክትትልና ምርመራ ማንነታቸው የማይታወቁ ወንጀል ፈፃሚዎችን በ48 ሰዓት ጊዜ ውስጥ በመለየት 3 ዋና ወንጀል ፈፃሚዎችንና 3 ግብራበሮቻቸውን በቁጥጥር ስር ማዋሉ ታውቋል፡፡

የምርመራ ሥራው እንዳበቃ የፍርድ ሂደት ውጤቱን በቀጣይ ለህዝብ እንደሚገለፅ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኘው ከእስር ተለቀቁ። የቀድሞው የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኘው፤ ከ5 ዓመት ከ4 ወራት እስር በኋላ ዛሬ ከሰዓት ከእስር መፈታታቸውን ጠበቃቸው ለ" ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ድረገፅ በሰጡት ቃል ተናግረዋል። ጠበቃቸው አቶ ሓፍቶም ከሰተ የቀድሞው የሜቴክ ዋና ዳይሬክተር ዛሬ ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ የተለቀቁት ፤ አብዛኛውን…
ፎቶ ፦ ላለፉት ዓመታት በእስር ላይ የነበሩት እና በቅርቡ ከእስር የተፈቱት የቀድሞው የ #ሜቴክ ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኘው ዛሬ መቐለ ገብተዋል።

መቐለ ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

የፍትህ ሚኒስቴር የሜጄር ጄነራል ክንፈ ዳኘውና የቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዜዳንት አብዲ ኢሌ ክስ ተቋርጦ ከእስር የተፈቱት " ለዘላቂ የህዝብ ጥቅም ሲባል ነው " ማለቱ ይታወሳል።

Photo Credit - Demtsi Woyane

@tikvahethiopia
#ኩሽ #ሴራሊዮን

የሴራሊዮን መንግሥት በአገሪቷ በተንሰራፋው ‘ #ኩሽ / Kush ’ እየተባለ በሚጠራው የአደንዛዥ እፅ ምክንያት ብሔራዊ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀ።

' ኩሽ ' የተለያዩ ሱስ የሚያስይዙ ግብዓቶችን በመደባለቅ የሚሰራ አደገኛ እፅ ሲሆን ለዓመታት በአገሪቷ ተንሰራፍቶ ይገኛል።

በአደንዛዥ እጹ ውስጥ ከሚጨመሩ ግብዓቶች መካከል አንዱ የተፈጨ #የሰው_አጥንት ነው።

በዚህም ምክንያት #ከመቃብር ውስጥ አፅም ለማውጣት የሚቆፍሩ #ሱሰኞችን ለማስቆም የጸጥታ አካላት በመካነ መቃብር ሥፍራዎች የሚያደርጉትን ጥበቃዎች አጠክረው ቆይተዋል።

የሴራሊዮን ፕሬዚደንት የሆኑት ጁሊየን ማዳ ባዮ አስተዳደራቸው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲያውጅ ያስገደደውን ይህንን እፅ / ኩሽ “ የሞት ወጥመድ ” ሲሉ የገለጹት ሲሆን በአገሪቷ ላይም የህልውና ቀውስና ስጋት ፈጥሯል ብለዋል።

ፕሬዚደንት ባዮ ፤ በእፁ ምክንያት የሚሞቱ ሰዎች ቁጥርም እንዳሻቀበ ተናግረዋል።

በመሆኑም በ ' ኩሽ ' እፅ ምክንያት የሚደርሰውን ቀውስ ለመከላከል በሀገሪቱ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጇል ፤ ብሔራዊ ግብረ ኃይል እንዲቋቋምም መደረጉን ቢቢሲ አስነብቧል።

ፎቶ/ቪድዮ ፦ ቻናል 4 እና አፍሪካ ኒውስ (ፋይል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
“ 1.2 ቢሊዮን የምስኪን ሕዝብን ገንዘብ 4 ዓመታት ሙሉ ኦክሎክ ጀነራል ትሬዲንግ እየተጠቀመበት ነው። በውላችን መሠረት መኪና አላስረከበንም ” - የቱሪስት ታክሲ ማኀበራት በስራቸው ከ2,800 በላይ አባላት ያሏቸው ከ40 በላይ የሚሆኑ ሕጋዊ የቱሪስት ታክሲ ማኀበራት ከ3 ዓመታት በፊት " ከኦክሎክ ትሬዲንግ/ኃላ/የተ/የግ/ ማኀበር " መኪና እንዲቀርብላቸው ቢዋዋሉም መኪናው ሳይቀርብ የውል ገደቡ እንዳለፈ፣…
#ቅሬታ

“ እኔ 1.5 ሚሊዮን ብር ነው #የተጨመረብኝ። እውነት ድርጅቱ ጨምሮበት ነው ወይስ የድሃ እንባ ፈልጎ ነው ? ”- እያለቀሱ ቅሬታ ያቀረቡ ቆጣቢ እናት

2012 ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ በኦክሎክ ጀነራል ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኀበር አማካኝነት መኪና ለማስመጣት ገንዘብ ሲቆጥቡ የነበሩ ከ40 በላይ በሆኑ ማኀበራት ሥር የሚገኙ ከ2 ሺህ 800 በላይ ቆጣቢዎች፣ ውል የገባላቸውን መኪና አስመጪ ማኀበሩ በውሉ መሠረት መኪናውን እንዳላቀረበላቸው ገልጸዋል።

ከቅሬታ አቅራቢዎቹ መካከል አንዱ ቆጣቢ፣ “ እኔ በሥነ ስርዓት መረጃ አለኝ። በእኛ ስም እየመጣ እየተሸጠ ነው። ለዚህ እኔ ምስክር ነኝ ” ሲሉ ኦክሎክ ጀነራል ቲሬዲንግን ኮንነዋል።

ሌሎች ቅሬታ አቅራቢዎች በሰጡት ቃል ምን አሉ ?

➡️ አንድ ቅሬታ አቅራቢ፣ “ ገንዘባችንን ሰጥተን ለማኝ እየሆንን ነው። ገንዘባቸውን ከፍለው እንደገና የጥበቃ ሰራተኛ ሆነው ተጠግተው መኪና ያገኙ ራሱ አሉ ” ብለዋል።

➡️ ሌላኛው አባት በበኩላቸው፣ “ መኪናውን የሚጠብቁ ሁለት ልጆች አሉኝ። ገናኮ ለየትኛው እንደምሰጥ እያሰብኩ ነው ያለሁት” ሲሉ የነበራቸውን ተስፋ አስረድተው፣ “ ጎዳና ላይ ከምታድር ድሃ መቀነቷን ፈትቶ እንደመውሰድ ነው። ችግር ካለ ስብስቦ ሊጠይቀን ይችል ነበር። ግን በስማችን መነገድ ነው የፈለገው ” ብለዋል።

➡️ ሌላኛዋ ቆጣቢ በበኩላቸው ፦

“ ውላችን ከ3 እስከ 6 ወራት፣ ካልሆነ ደግሞ እስከ 1 ዓመት ነበር፣ 60 ሺሕ ከፍለን የሚለው። 25 በመቶ መኪናው አገር ውስጥ ከገባ በኋላ ገንዘብ እንከፍላለን የሚል ነው ውላችን ላይ የነበረው። 60 ሺሕ ከፍለን እያለ 2013 ዓ/ም ላይ 25 ፐርሰንት ክፈሉ ተብሎ የመኪናውን ዋጋ 25 በመቶ ስንከፍል፣ እኔ ተመዝግቤ የነበረው መኪና 520 ሞዴል ነበር። የመኪናው ዋጋ 520 ሺሕ ብር ነበር። 

በመካከል 25 በመቶ ክፈሉ ‘የቻንሲና የሞተር ቁጥር መጥቷል’ ተብሎ ተከፈለ። ነገር ግን ‘ይህን መኪና ፋብሪካው ማምረት ስላቆመ 690 ሺሕ የሚመረተውን መኪና ቀይሪ’ ተብዬ 690 ሺሕ ብር የመኪናውን 25 ፐርሰንት 2013 ዓ/ም ኀዳር ወር ከፍዬ እየጠበኩ ሁለት ዓመታት ተቆጠሩ።

በ2014 ዓ.ም ከ2,800 በላይ አባላት በተገኙበት ኦሮሚያ የባህል አዳራሽ ተሰብስቦ ‘ከጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ የመጣሁ ነኝ መኪናችሁን 1 ሳምንት ባልሞላው ጊዜ ውስጥ ተውስዳላችሁ። እንባችሁ ታብሷል ” ያላቸው አካል እንደነበር ገልጸው፣ ምንም መፍትሄ ስላልተገኘ፣ መንግሥት ይዳኘን " ሲሉ ጠይቀዋል።

➡️ አንዲት እያለቀሱ ቅሬታቸውን ያቀረቡ እናት በመጀመሪያ የነበረውን ውል መሠረት በማድረግ ተስማምተው እንደገቡ ገልጸው፦ “ ሁለት ወራት ጠበቁና 35፣ ‘45 ፐርሰንት ጨምሩ’ አሉን። ያን አድርገን ሳንጨርስ (ተበድረን ያስገባነውን ጉድ) መልሰው ሦስት ወራት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ‘400 ሺሕ ብር ጨምሩ፣ አበዳሪ ተገኝቷል በሁለት ወራት ውስጥ ገጣጥመን እናስገባለን’ አሉ። እኔ 1.5 ሚሊዮን ብር ነው የተጨመረብኝ። እውነት ድርጅቱ ጨምሮበት ነው ወይስ የድሃ እንባፈልጎ ነው?። አልገባኝም። #መንግሥት_ይዬን ። ” ሲሉ እያለቀሱ ቅሬታ አቅርበዋል።

➡️ ሌላኛው ቆጣቢ በበኩላቸው፣ “ ትዳራችንን ልናፈርስ ጫፍ ላይ ደርሰናል። አብዛኞቻችን ደግሞ የተሸወድነው የመንግሥት ባለስልጣንና ባንክ ቁጭ አድርጎ ቃል ሲገባልን ነው ” ነው ያሉት።

#TikvahaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia