TIKVAH-ETHIOPIA
1.47M subscribers
56.1K photos
1.4K videos
202 files
3.8K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#BREAKING

የኢትዮጵያ መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ለማቆም ውሳኔ አሳለፈ።

መንግስት ባወጣው መግለጫ ፤ በአሁኑ ወቅት በሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ክልል ነዋሪዎች የሰብዓዊ እርዳታን ፍለጋ ወደአጎራባች ክልሎች እየተጓዙ መሆኑን አመልክቷል።

እነዚህ ዜጎች የሰብዓዊ እርዳታው ከቀያቸው ሳፈናቀሉ ባሉበት እንዲርሳቸው ቢደረግ እንግልታቸውን እንደሚቀንስ በጽኑ እንደሚያምን አሳውቋል።

በመሆኑም በከፍተኛ ችግር ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ችግር በአፋጣኝ የመፍታት ኃላፊነቱ ከምንም ነገር በላይ ቅድሚያ የሚሰጠው መሆኑን በመረዳት የአስቸኳይ የሰብዓዊ አቅርቦቶች ወደ ትግራይ ክልል በበቂ ሁኔታ መድረስ የሚችሉበትን ሁኔታ ለማሳካት የተቻለውን ሁሉ ጥረት ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል።

በዚህም በከፍተኛ ችግር ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ህይወት ለመታደግ እና የዜጎችን እንግልት ለመቀነስ ከተለመደው የተለዩ እርምጃዎችን መውሰድ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ይህ ውሳኔ ከወጣበት ሰዓት ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት የማቆም ውሳኔ መተላለፉን አብስሯል።

መንግስት ዓለም ዓቀፉ የለጋሾች ማህበረሰብ እያቀረበ ያለውን ድጋፍ እና እርዳታ በከፍተኛ መጠን እንዲጨምር ጥሪ አቅርቧል።

የሰብዓዊ እርዳታ በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተባብሮ ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑን የገለፀው መንግስት ጥረቱ እና ቁርጠኝነቱ የሰብዓዊ ሁኔታውን በማሻሻል ረገድ የሚኖረው ስኬት የሚረጋገጠው በሌላኛው ወገን የሚገኘው አካል በተመሳሳይ ለዚህ አላማ በሚኖረው ቁርጠኝነት ልክ ነው ብሏል።

ውሳኔው ውጤት ማምጣት እንዲችል በትግራይ ክልል የሚገኙ አማጺያን ከማንኛውም የጥቃት እንቅስቃሴ እንዲታቀቡ እና በጉልበት ከያዟቸው የአጎራባች ክልል አካባቢዎች እንዲወጡ መንግስት ጠይቋል።

(ሙሉውን ከላይ ያንብቡ)

@tikvahetiopia
#BREAKING

ሩስያ በአምነስቲ ኢንተርናሽናል እና ሂውማን ራይትስ ዎች ላይ እርምጃ ወሰደች።

ከተመድ የሰብዓዊ መብቶች ም/ቤት የታገደችው እና በዩክሬን የጦር ወንጀል ፈፅማለች እየተባለች በሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ስሟ እየተነሳ ያለው ሩስያ ላለፉት 30 ዓመታት በሀገሪቱ ሲንቀሳቀሱ የነበሩትን ሁለቱን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች (ሂውማን ራይትስ ዎች እና አምነስቲ ኢንተርናሽናል) ፤ የምዝገባ ፍቃድ ሰርዛለች በሀገሯ (ሞስኮ) የነበሩ ቢሮዎችን ዘግታቸዋለች።

ሩስያ ከአምነስቲ ኢንተርናሽናል እና ሂውማን ራይትስ ዎች ባለፈ በአጠቃላይ 15 ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት (NGO)ን " ዝርዝር ማብራሪያ ሳትሰጥ " የሩስያ ፌዴሬሽን ህግን በመጣስ " በሚል እርምጃ እንደተወሰደባቸው በፍትህ ሚኒስቴሯ በኩል አሳውቃለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሰበር_ዜና የቀድሞው የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ በድጋሚ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሆነው ተመረጡ። ሀሰን ሼክ ሞሐመድ የአሁኑን የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሞሀመድ አብድላሂ ፈርማጆን እጅግ ፉክክር በተሞላበት ሶስት ዙር የምርጫ ሂደት አሸንፈዋቸዋል። የመጨረሻ ውጤት ፦ 👉 ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ 214 ድምፅ 👉 ሞሐመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ➡️ 110 ድምፅ 3 ድምፅ ዋጋ ቢስ ሆኗል። @tikvahethiopia
#BREAKING

የሶማሊያ ፌደራል ፓርላማ ሀሰን ሼክ ሞሀመድን የሀገሪቱ 10ኛ ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል።

አዲሱ ፕሬዜዳንት እ.ኤ.አ. ከመስከረም 2012 እስከ የካቲት 16 / 2017 ድረስ በፕሬዝዳንትነት አገልግለዋል።

ሀሰን ሼክ ሞሀመድ ተሰናባቹን ፕሬዝዳንት ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆን በማሸነፍ በሶማሊያ ታሪክ ለሁለት ጊዜ ፕሬዝዳንት ሆነው የተመረጡ የመጀመሪያው ሰው መሆን ችለዋል።

ምንጭ፦ የሶማሊያ ብሄራዊ ቴሌቪዥን

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#BREAKING

የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛው ተርባይን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀመረ።

ጠ/ሚር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በቤንሻንጉል ጉሙዝ ጉባ ወረዳ በታደሙበት ዝግጅት ነው በዛሬው ዕለት 2ኛው ተርባይን ኃይል ማመንጨት የጀመረው።

የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ካሉት 13 ተርባይኖች መካከል ዩኒት 9 የሚባለው ሁለተኛው ተርባይን የተሳካ ተከላ እና ሙከራ ከተደረገ በኋላ ኃይል የማመንጨት ስራው እውን መሆኑን ብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።

ዛሬ በይፋ ሥራ የጀመረው ሁለተኛው ዩኒት 375 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳለው ተገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#የምስራች🎉 የአባይ ውሃ ለሦስተኛ ጊዜ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አናት ላይ መፍሰስ ጀምሯል፡፡ በግድቡ ግንባታ ላይ የተሳተፉ ባለሙያዎችም የደስታ ስሜታቸውን ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከለውጡ በኋላ በፕሮጀክቱ ላይ በተወሰደው የማስተካከያ እርምጃ በግድቡ ውስጥ መተከል የነበረባቸው የውሃ ማስተላለፊያ የብረታ ብረት ስራዎች ተጠናቀው የግድቡን የመካከለኛው ክፍል ከፍታ ከባህር ጠለል በላይ…
#BREAKING

ሶስተኛው ዙር ሙሌት በስኬት ተጠናቀቀ።

የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሶስተኛው ዙር ሙሌት በስኬት ተጠናቆ ውሃ በግድቡ አናት ላይ መፍሰስ ጀምሯል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች የግድቡን ሙሌት በስኬት መጠናቀቅ ለማብሰር በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መገኘታቸውን ብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኬንያ በኬንያ የተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ውጤት ዛሬ ሰኞ ከሰዓት በኋላ ይፋ ይደረጋል ተብሎ እየተጠበቀ ባለበት ጊዜ አለመግባባት እና ውዝግብ ተፈጥሯል። የፕሬዝዳንታዊ ምርጫውን ውጤት ያሳውቃሉ ተብለው በሚጠበቁት የኮሚሽኑ ባለሥልጣንት መካከል ክፍፍል መፈጠሩ ነው የተነገረው። በዚህም 4 የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች በይፋ የፕሬዝዳንታዊ ምርጫው ውጤት ከሚነገርበት ማዕከል ውጪ መሃል ናይሮቢ በሚገኘው ሴሬና…
#BREAKING

ዊሊያም ሩቶ የኬንያን ምርጫ ማሸነፋቸው ይፋ ሆነ።

የኬንያ ምርጫ ኮሚሽን በቦማስ ማዕከል ዊልያም ሩቶ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫውን ማሸነፋቸውን ይፋ አድርጓል።

ዊልያም ሩቶ እና ራይላ ኦዲንጋ በተቀራራቢ ውጤት አንገት ለአንገት ተናንቀው እስከ አሁኗ የውጤት መግለጫ ሰዓት የደረሱ ሲሆን በመጨረሻም የፕሬዜደንታዊ ምርጫው አሸናፊ ዊሊያም ሩቶ መሆናቸውን በቦማስ ማዕከል ባለው ኮሚሽን ተገልጿል።

ሩቶ ያሸነፉት ከተሰጠው ጠቅላላ ድምፅ 50.49% በማግኘት ሲሆን ራይላ ኦዲንጋ 48.8% ድምፅ አግኝተዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#HappeningNow ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነ ስርዓቱን በአዲስ አበባ " ወዳጅነት አደባባይ " በአሁን ሰዓት እያካሄደ ይገኛል። በዚሁ ስነስርዓት ላይ ቀደም ብሎ እንደተገለፀው የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና የኬንያው ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ተገኝተዋል። Photo Credit : Safaricom Ethiopia @tikvahethiopia
#BREAKING

ለሳፋሪኮም ሞባይል መኒ ተፈቀደ።

የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ " ሞባይል መኒ " መፈቀዱን አስታውቀዋል።

ይህን ያሳወቁት በአሁን ሰዓት እየተካሄደ በሚገኘው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ ነው።

ውድ ቤተሰቦቻችን ተጨማሪ መረጃዎችን እንልክላችኃለን።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#LIVE በአፍሪካ ህብረት መሪነት በደቡብ አፍሪካ ሲደረግ ከነበረው የሰላም ንግግር ጋር በተያያዘ እስካሁን ስላለው ሂደት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ መግለጫ እየሰጡ ነው። በደቡብ አፍሪካ ፤ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የተረጋገጠ የፌስቡክ ገፅ ላይ በቀጥታ መከታተል ይቻላል👇 https://www.facebook.com/DIRCOza @tikvahethiopia
#BREAKING

የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት ዘላቂ ግጭት የማቆም ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

ይህ የተገለጸው በደቡብ አፍሪካ ሲያደረግ የነበረው የሰላም ንግግር ውጤት በተገለጸበት ወቅት ነው።

የፌደራል መንግሥት እና የህወሓት የሰላም ንግግር ይዘት የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ እየገለጹ ነው።

@tikahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በአሁን ሰዓት በናይሮቢ እየተሰጠ ባለው ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓት ወታደራዊ አመራሮች ባለፈው በደቡብ አፍሪካ፣ ለተፈረመው የሰላም ስምምነት ቁርጠኝነታቸውን ገልፀዋል። ተጨማሪ መረጃዎችን ይጠብቁ። @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#BREAKING

በናይሮቢ ሳምንት ያህል የፈጀውን ውይይት ተከትሎ የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓት ከፍተኛ የጦር አዛዦች #ጦርነቱን_ለማቆም የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ፤ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በዘላቂነት ግጭት እንዲቆም ስምምነት መፈረማቸው ይታወሳል ዛሬ ወታደራዊ አመራሮቹ በናይሮቢ ስምምነቱን ለማስፈጸም የሚያችል ስነድ ተፈራርመዋል፡፡

ተጨማሪ መረጃ ይጠብቁ።

Video Credit : Ruud Elmendrop

@tikvahethiopia