TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Share #ሼር

ለጠቅላላ ሀኪሞች የወጣ የኮንትራት ቅጥር ፦

የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ በዞን ጤና መምሪያ እና በልዩ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት ክፍት የስራ መደብ ላይ ተፈላጊውን ችሎታ የሚያሟሉ ሀኪሞችን በኮንትራት ቅጥር አወዳድሮ መመደብ እንደሚፈልግ አሳውቋል።

👉 የስራው መደቡ መጠሪያ - ጠቅላላ ሀኪም
👉 የሙያ መስመር /ተፈላጊ ችሎታ - በጠቅላላ ህክምና በዲግሪ የተመረቀ/ች
👉 የስራ ልምድ- #ዜሮ_ዓመት
👉 ብዛት - 379 (#ሶስት_መቶ_ሰባ_ዘጠኝ )
👉 ደመወዝ - 9,056
👉 የስራ ቦታ - በእጣ ነው የሚለየው

ማሳሰቢያ ፦

1ኛ. በደቡብ ክልል ጤና ቢሮ በሚመደብበት በማንኛውም ዞን / ልዩ ወረዳ ሄደው ለመስራት ፍቃደኛ የሆነ /የሆነች።

2ኛ. በዕጣ ከጤና ቢሮ ለዞን/ልዩ ወረዳ ሲመደቡ ዞን/ልዩ ወረዳ በሚሰጠው በማንኛውም ጤና ተቋማ /ምደባ / ቦታ ሄደው ለመስራት ፍቃደኛ የሆነ/የሆነች።

3ኛ. በማንኛውም የመንግስት ተቋም ውስጥ ያልተቀጠረ /ያልተቀጠረች

የመመዝግቢያ ጊዜ ፦ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት። (ከተሰጠው ቀን ውጭ የሚመጣ አይስተናገድም)

የመመዝገቢያ ቦታ ፡ በደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ሰው ሀብት አስተዳደርና ልማት ዳይሬክቶሬት በአካል በመቅረብ ሲሆን ኦርጂናል የትምህርት እና የሙያ ፍቃድ ማስረጃ ከማይመለስ ፎቶ ኮፒ ጋር መያዝ እንዳትዘነጉ።

የፈተናው ቀን : በቀጣይ ይገለፃል።

@tikvahethiopia
#AmharaRegion

የጠቅላላ ሀኪም የቋሚ ቅጥር ፦

የአማራ ክልል ጤና ቢሮ በክልሉ ስር ባሉ ጤና ተቋማት ጠቅላላ ሀኪሞችን መድቦ ማሰራት ይፈልጋል።

👉 የስራ መደቡ መጠሪያ - ጠቅላላ ሀኪም
👉 ደመወዝ - 9,056 ብር (ዘጠኝ ሺ ሃምሳ ስድስት ብር)
👉 ብዛት - 631 (#ስድስት_መቶ_ሰላሳ_አንድ)
👉 የስራ ቦታ - በክልሉ ባሉ የጤና ተቋማት ክፍት ቦታዎች
👉 ተፈላጊ የትምህርት ዝግጅት - በጠቅላላ ሀኪም የመጀመሪያ ዲግሪ እና 0 (#ዜሮ) ዓመት የስራ ልምድ
👉 የሞያ ፍቃድ ያለው / ያላት

የመመዝገቢያ ቦታ በአብክመ ጤና ቢሮ እና በሁሉም ዞን ጤና መምሪያዎች ማስረጃዎቻችሁን ዋናውንና የማይመለስ ኮፒ በመያዝ መመዝገብ ትችላላችሁ ተብሏል።

የዞን ጤና መምሪያዎች ምዝገባው ከተጠናቀቀበት ቀን ጀምሮ ባሉት 3 ተከታታይ ቀናት ውስጥ በሶፍት ኮፒ እና በሃርድ ኮፒ እንዲልኩ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

ማሳሰቢያ ፦

1ኛ. በማንኛውም ጤና ተቋም ዕጣ በደረሰው ቦታ ላይ ለመስራት ፍቃደኛ የሆነ/የሆነች
2ኛ. ከዚህ በፊት በመንግስት ጤና ተቋም በቋሚ ቅጥር ያልተቀጠረ/ያልተቀጠረች

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
#SidamaRegion

የሲዳማ ክልል " ጠቅላላ ሀኪሞች " ን በክልሉ ስር ባሉ የጤና ተቋማት አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

👉 የሙያ አይነት - ጠቅላላ ሀኪም
👉 የት/ት ደረጃ - የመጀመሪያ ዲግሪ
👉 የወር ደመወዝ - 9,056 ብር
👉 ብዛት - 126 (አንድ መቶ ሀያ ስድስት)
👉 የስራ ልምድ - 0 ዓመት ( #ዜሮ_ዓመት)
👉 የመመዝገቢያ ቀን - ከ1/06/2014 ዓ/ም እስከ 10/06/2014 ዓ/ም (10 ተከታታይ የስራ ቀን)
👉 መመዝገቢያ ቦታ -የሲ/ክ/ጤ/ቢሮ ሰው ሀብት ልማት ቢሮ ቁጥር 3
👉 ሁሉም ተወዳዳሪዎች ከታወቀ ከመንግስት ዩኒቨርሲቲ የተመረቀ/የተመረቀች የሙያ ፍቃድ/ላይሰንስ ያለው/ያላት

ማሳሰቢያ ፦

1ኛ. ሁሉም ተወዳዳሪዎች በክልሉ ባለው የጤና ተቋም በዕጣ ተመድቦ ለመስራት ፍቃደኛ መሆን አለባቸው።

2ኛ. ሁሉም ተወዳዳሪ የት/ት ማስረጃ ኦርጂናል እና የማይመለስ ኮፒ ማቅረብ አለበት።

(መዕክቱን ለሌሎች share ያድርጉ / Copy አድርገው ያሰራጩ)

@tikvahethiopia
#ቅጥር

የአዲስ አበባ አስተዳደር የጤና ቢሮ በስሩ ላሉት ተቋማት ሰራተኞችን አወዳድሮ በቋሚ ቅጥር ለማሰራት ይፈልጋል።

መስፈርቶቹን የምታሟሉ ከ8/06/2014 ዓ/ም ጀምሮ ባሉት 10 የስራ ቀናት መመዝገብ ትችላላችሁ ተብሏል።

ሁሉም የስራ መደብ የስራ ልምድ #ዜሮ ዓመት ነው።

ከፍተኛ ባለሞያ የተፈለገበት የስራ መደብ - ጠቅላላ ሀኪም ሲሆን በመጀመሪያ ዲግሪ በ9,056 ብር ደመወዝ አጠቃላይ 150 ሰው ይፈለጋል።

በተጨማሪ በ ዘO (ጤና መኮንን) በተመሳሳይ የመጀመሪያ ዲግሪ በ7,071 ብር ደመወዝ 50 ሰው ይፈለጋል።

እንዲሁም በደረጃ 4 ጤና ኤክስቴንሽን (ዲፕሎማ / ሌቭል 4) በ5,358 ብር ደመወዝ ፣ በደረጃ 4 ነርስ (ዲፕሎማ / ሌቭል 4) በ4,609 ደመወዝ ፣ በሚድዋይፈሪ ፕሮፌሽናል (የመጀመሪያ ዲግሪ) በ6,193 ብር ደመወዝ ፣ በፋርማሲ ፕሮፌሽናል (የመጀመሪያ ዲግሪ) በ7,071 ብር ደመወዝ በተጠቀሱት እያንዳንዱ የስራ መደቦች 30 ሰዎች ይፈለጋሉ።

በሌሎችም የስራ መደቦች ላይ ያሉ ቦታዎችን ፣ የደመወዝ መጠን ፣ የትምህርት ደረጃ ከላይ በተያያዘው ምስል ይመልከቱ።

@tikvahethiopia