TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" የቡድን እና የነፍስወከፍ መሳሪዎችን የማስፈታቱ ሂደት ዘግይቷል " - የብሔራዊ መልሶ ማቋቋም ኮሚሽን

የፕቶሪያውን የህወሓትና የፌደራል መንግስትን ስምምነት ተከትሎ ህወሓት ታጥቋቸው የነበሩ ከባድ መሳሪያዎችን የማስፈታት ሥራው በተሳካ ሁኔታ ቢፈፀምም፣ የቡድንና የነፍስወከፍ መሳሪዎችን የማስፈታቱ ሁኔታ በተለያዩ ምክንያቶች መዘግየቱን የብሔራዊ መልሶ ማቋቋም ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

ኮሚሽኑ ይህን ያስታወቀው ዛሬ በባህር ዳር ከተማ በተዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ ነው።

የተሀድሶ ኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ፤ አገራችን ባለፉት ሁለት ዓመታት በጦርነት ውስጥ ማለፏን ጠቅሰው ጦርነቱ ያስከተለውን ጥፋት በማየትና ካለፍንባቸው ችግሮች መማርና ወደ ሰላም መምጣት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

ምክትል ኮሚሽነር ብርጋዴር ጀነራል ደርቤ መኩሪያ በበኩላቸው፤ የፕሪቶያውን ስምምነት ተከትሎ የትግራይ ኃይሎች የከባድ መሳሪያ ትጥቅ መፍታታቸውን ጠቁመዋል።

የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን ግን በተለያዩ ምክንያቶች እስካሁን ማስፈታት ሳይቻል መቆየቱን ተናግረዋል፡፡

ለመዘግየቱ ዋነኞቹ ምክንቶች ፦ ኮሚሽኑ የቅድመ ዝግጅት ስራ ስለነበረበት፣  በትግራይ ክልል የሽግግር መንግስት ሳይቋቋም በመቆየቱና ሌሎች አንዳንድ መሰናክሎች እንደነበሩ ነው ያስረዱት፡፡

አሁን ግን ሁኔታዎች እየተስተካከሉ በመሆኑ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ተግባራት ይፈፀማሉ ብለዋል።

በውይይት መድረኩ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርን ዶ/ር ጌታቸው ጀንበርን ጨምሮ ሌሎች የሲቪልና ወታደራዊ ባለስልጣናት ተገኝተው እንደነበር ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።

#ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
#ቦረና

በ ' ሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን ' የተሰራ የውሃ ፕሮጀክት ተመረቀ።

ፋውንዴሽኑ በቦረና ዞን ሚዮ ወረዳ፣ በቦኩ ሉቦማ መንደር እና ዱቡሉቅ ወረዳ የንፁህ ውሃ ፕሮጀክቶችን አጠናቅቆ አስመርቋል።

ፕሮጀክቱ ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ እንደወጣበት ተመላክቷል።

በዝግጅቱ ላይ የአርቲስቱ ቤተሰቦች፣ የአካባቢው ማህበረሰብ እና የመንግስት ተወካዮች ተገኝተዋል።

የውሃ ፕሮጀክቱ የሁለቱን ወረዳዎች 52,325 ነዋሪዎችን የመጠጥ ውሃ ችግር ያቃልላል ተብሎ ይጠበቃል።

ፎቶ፦ ሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን

@tikvahethiopia
#ነዳጅ

የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በማደያዎች የነዳጅ ግብይትን በዲጂታል የማካሄድ የሙከራ ትግበራ  ሥራ መጀመሩን አሳውቋል።

ግንቦት 1 ቀን 2015 ዓ.ም ደግሞ በመላ ሀገሪቱ የዲጂታል የነዳጅ ግብይት ይጀመራል ተብሏል።

ዛሬ በአዲስ አበባ ለሙከራ የተጀመረው የዲጂታል ግብይት በሁሉም ተሽከርካሪዎች እና በሁሉም ማደያዎች ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።

ግብይቱ በዲጂታል መሆኑ ምርት እንዳይባክን እና የተሳለጠ ግብይት እንዲኖር እንደሚያደርግ ነው ሚኒስቴሩ የገለፀው።

የነዳጅ ግብይቱ በ #ቴሌብር አማራጭ የሚከናወን ነው የተባለ ሲሆን በዚህ የዲጂታል ክፍያ ስርዓት ሁሉም የመንግስት እና የግል ተሽከርካሪዎች ቁጥጥር ይደረግባቸዋል ተብሏል።

ሚኒስቴሩ በቅርቡ የትራንስፖርት ትኬት በዲጂታል እንደሚጀመር አሳውቋል።

#ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
#ጅብ

የስልጤ ዞን ጦራ አስተዳደር ከሰሞኑን ጅብ በሰው ላይ ጥቃት እያደረሰ ስለሆነ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ማሳሰቢያ አስተላለፈ።

በስልጤ ዞን ላንፉሮ ወረዳ ሶስተሮ ቀበሌ ላይ አንድ በግምት አስር አመት የሚሆነው ህፃን ወደ ትምህርት ቤት እየሄደ በጅብ ጥቃት ደርሶበታል።

ይኸው ጥቃት ከሰሞኑን የተፈፀመ 3ኛው መሆኑ ተነግሯል።

ህፃኑ ወደ ትምህርት ቤት በመሄድ ላይ ሳለ ጅብ ይዞት ከፍተኛ ጉዳት አድርሶበት ወደ ወራቤ ሆስፒታል ሪፈር መደረጉ ተመላክቷል።

ከሰሞኑን በስልጤ ዞን ጦራ ከተማ አስተዳደር ጦራ መልታሜና ጦራ ሚሊኒዬም ቀበሌዎች ላይ በሁለት ህፃናት ላይ ጅብ ከፍተኛ ጉዳት አድርሶ ነበር።

በጦራ መልታሜ ቀበሌ ልዩ ስሙ " መናፈሻ መንደር " አካባቢ በመኖሪያ ቤቷ በር ላይ የቆመች አንዲት የሶስት አመት ህፃን ጀቡ ወደ ጫካ ይዟት ሊገባ ሲል በህብረተሰቡ ትግል ማትረፍ ተችሏል። በሚሊኒዬም ቀበሌ ደግሞ የ10 አንድ ህፃን ወደ መስጂድ እየተጓዘ እያለ በጅብ ተበልቶ በህይወት ሊተርፍ ችሏል።

የጦራ አስተዳደር ሰሞኑን ከወትሮው በተለየ መልኩ ጅብ በሰው ላይ የተለያዩ ጥቃቶችን እያደረሰ በመሆኑ ልዩ ጥንቃቄ ይሻል ብሏል።

ህፃናት ወደ ትምህርት ቤት ሲሄዱ ወላጆች ማድረስ ከትምህርት ቤት ሲመለሱም ወላጆች በጥንቃቄ ወደቤታቸው መመለስ ይኖርባቸዋል ብሏል።

ህፃናትን ብቻቸውን ጥሎ መሄድ አይገባም ያለው አስተዳደሩ፤" ማነኛውንም እንቅስቃሴ ስናደርግ ከወትሮው በተለየ ልዩ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርብናል " ሲል አሳስቧል።

@tikvahethiopia
ኡጋንዳውያኑ ለምን ኢትዮጵያ መጡ ?

ከኡጋንዳ ምሥራቃዊ ክፍል በመቶዎች የሚቆጠሩ ኡጋንዳውያን ወደ ኢትዮጵያ የተሰደዱት " የምፅዓትን ቀን ሽሽት ነው " መባሉ ሐሰት መሆኑን የኛንጋቶም ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ ሎኪኛኒጋ ሙርሌ ለቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ተናግረዋል።

ምክትል አስተዳዳሪው ሎኪኛኒጋ ሙርሌ ምን አሉ ?

" ኡጋንዳውያኑ በወረዳችን ይገኛሉ። አመጣጣቸው አካባቢውን ለማየትና የቤተክርስቲያን መልዕክት ለማድረስ ነው።

ይህንንም ከፌደራል ደኅንነት መ/ቤት ለመጡ አካላት አስተድተናል።

በቁጥር ህጻናት እና ሴቶችን ጨምሮ 277 ይደርሳሉ ፤ በቤተክርስቲያን የእንግዳ መቀበያ እና በግለሰቦች መኖሪያ ተጠልለው ነው የሚገኙት።

ወደ ኢትዮጵያ የተሰደዱት የምጽዓትን ቀን ሽሽት ነው የተባለው የተሳሳተ መረጃ ነው።

በወረዳችን ከዚህ ቀደም በተዘጋጀ ፌስቲቫል ላይ ከኬንያ ቱርካና፣ ከደቡብ ሱዳን እና ከኡጋንዳ አንድ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ተሳትፈው ነበር።

እነርሱ የመጡት በታሪክም ኛንጋቶም ማኅበረሰብ ከኡጋንዳ ነው የመጣው ብለው ስለሚያምኑ አካባቢውን ለማየት ነው።

ኡጋንዳውያኑ ታኅሳስ ወር ውስጥ ነው ወደ ኢትዮጵያ የገቡት ፤ እንመለሳለን ከማለት ውጭ መቼ እንደሚመለሱ አልገለፁም።

እነርሱ ሲመጡ ዝናብ አልነበረም። ዝናብ እስከሚዘንብ ድረስ ቆይተን ለእናንተ ዘር ሰጥተን ነው የምንሄደው እግዚአብሔር የነገረን መልዕክት ይህ ነው። ከዚያ በኋላ እንመለሳለን ነው ያሉት።

አሁን ላይ ግን በአካባቢው ከፍተኛ ዝናብ እየዘነበ ቢሆንም ኡጋንዳውያኑ አሁንም በሥፍራው ይገኛሉ። "

NB. በኢትዮጵያ በድርቅ ከተጎዱ አካባቢዎች አንዱ የደቡብ ኦሞ ዞን፣ ሲሆን በድርቁ ሳቢያ በርካታ እንስሳት ሞተዋል ፤ በሰዎችም ላይ ጉዳት ደርሷል።

የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ምንድነው ያሉት ?

አምባሳደር መለስ ዓለም ኡጋንዳውያኑ የምጽዓት ቀን በአካባቢያችን ይኖራል። ሞት መፈናቀል ይኖራል ብለው በመስጋት ወደ ኢትዮጵያ የገቡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

አናዱሉ ምን ብሎ ነበር ?

የቱርክ ዜና ወኪል አናዶሉ ከአንድ ወር በፊት ፣ የኡጋንዳን ፖሊስ ጠቅሶ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኡጋንዳውያን የአንድ ሃይማኖታዊ ቡድን ተከታዮች ወደ ኢትዮጵያ መሰደዳቸውን ዘግቦ ነበር።

በዘገባው የሃይማኖት ቡድኑ ተከታዮች የዓለም ፍፃሜ ኡጋንዳ ውስጥ ከሚኖሩበት አካባቢ ይጀምራል ብለው በማመን ከጥፋቱ ለመሸሽ እንደተሰደዱ ፖሊስ በምርመራዬ አረጋግጫለሁ ማለቱን አስነብቦ ነበር።

Via BBC NEWS AMHARIC

@tikvahethiopia
#ብርሃን_ባንክ

ለግብይትዎ የብርሃን ኤቲኤም ካርድን በመጠቀም ጊዜዎን ይቆጥቡ፤ ድካምዎን ያቅልሉ!

አዳዲስ እና ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ !

Facebook: https://www.facebook.com/berhanbanksc
Telegram: https://t.me/berhanbanksc
Instagram: https://www.instagram.com/berhanbanksc/
Twitter: https://twitter.com/berhanbanksc
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/76151001
YouTube: https://www.youtube.com/channel/UCvOxWe439dzMSvNnMrjcYVQ
TIKVAH-ETHIOPIA
የትኞቹ የህዝብ አገልግሎት መስጫ ተቋማት መስማት ለተሳናቸው ዜጎች ምቹ ናቸው? ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች መብቶች ስምምነትን በአዋጅ ቁጥር 676/2002 አጽድቃ ተቀብላለች። በስምምነቱ መሰረትም ፈራሚ ሀገራት መስማት የተሳናቸው ሰዎች የሕይወትና የማኅበራዊ እድገት ክህሎት እንዲያገኙ ብሎም በማኅበረሰባቸው ውስጥ ሙሉና ውጤታማ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የምልክት ቋንቋ…
በኢትዮጵያ የምልክት ቋንቋ ሕገ-መንግስታዊ እውቅና ሊሰጠው ይገባል !

በዓለም ላይ #ሰባ_አምስት ሀገራት የምልክት ቋንቋን እንደ ብሔራዊ ቋንቋ አድርገው ከመቀበል ጨምሮ በሰነድ የተደገፈ ሕጋዊ እውቅና ሰጥተዋል፡፡ በአፍሪካ ደግሞ ኬንያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ኡጋንዳ፣ ዙምባቡዌ ብሔራዊ ቋንቋቸው አድርገው ተቀብለውታል፡፡

በኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተጠቃሚዎች ያለው ይኽ ቋንቋ በፖሊሲም ሆነ በአፈጻጸም ትኩረት ያልተሰጠው ቋንቋ ነው፡፡

በኢትዮጵያም የምልክት ቋንቋ ሕገ-መንግስታዊ እውቅና ሊሰጠው ይገባል።

#HandsSpeakEyesListen
#እጆች_ይናገራሉ_አይኖች_ያዳምጣሉ
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የቤት ማፍረስ ዘመቻው ...

በአዲስ አበባ ዙርያ " ሸገር ከተማ " እየተካሄደ ያለውን የቤት ማፍረስ ዘመቻን በተመለከተ ኢሰመኮ የደረሰበትን የክትትል ውጤት በላከልን መግለጫ አሳውቋል።

በመግለጫው፤ በኦሮሚያ ክልል በሸገር ከተማ እየተካሄደ ያለው ቤቶችን የማፍረስ እና በግዳጅ ማስነሳት እርምጃ የመኖሪያ ቤት አልባነትን አባብሷል ብሏል።

ሕገ ወጥ የሆነ ግንባታን የማፍረስ እርምጃ ሕጋዊ ሂደትን መከተልና እርምጃው ሊያስከትል የሚችለውን ማኅበራዊ ቀውስ ከግንዛቤ በማስገባት አማራጭ መፍትሔዎችን ማመቻቸት ያስፈልጋልም ብሏል።

(ከኢስመኮ የተላከልን ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia