TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ISRAEL📸በእስራኤል ይፋዊ የስራ ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገኙት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በናዚ የተጨፈጨፉ አይሁዳውያን ማስታወሻ ማዕከልን ያድ ቫሼምን ጎበኙ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ለዑካቸው በማእከሉ የሚገኙትን የመታሰቢያ ሙዚየም፣ የህፃናት መታሰቢያን እና አዳራሽ ጎብኝተዋል። በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማእከሉ የክብር መፅሃፍ ላይ መልእክታቸውን አስፍረዋል።

ምንጭ፡-ኤፍ ቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Israel #Palestine

እስራኤል ለፍልሥጤም በቅርቡ ጊዜው የሚያበቃ አንድ ሚሊዮን ዶዝ ፋይዘር የኮቪድ-19 ክትባት ልትሰጥ ነው።

ዛሬ ይፋ በሆነው ስምምነት እስራኤል 1 ሚሊዮን የኮቪድ - 19 ክትባት ለፍልስጤም ትልካለች። ፍልስጤም በተመድ በሚደገፈው ፕሮግራም ክትባት ለሚያስፈልጋቸው ሀገራት ክትባት ሲላክላት አንድ ሚሊዮን ዶዝ ክትባቱን ለእስራኤል ትመልሳለች ተብሏል።

እስራኤል 85% ጎልማሳ ዜጎቿን የኮቪድ-19 ክትባት የከተበች ሲሆን በዌስት ባንክ እና ጋዛ ለሚገኙ 4.5 ሚሊዮን ፍልስጤማውያን ክትባት አላካፈለችም በሚል ስትተች ነበር።

ዛሬ ይፋ የሆነው ክትባት የመላክ ስምምነት በአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናፍታሊ ቤንት በሚመራው መንግስት የተደረሰ እንደሆነ ተገልጿል ፤ እስካሁን ግን ከፍልስጤም ባለስልጣናት ምንም የተባለ ነገር የለም።

በዓለማችን ካሉ ሀገራት የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በመከላከል ረገድ ከፍተኛ ስራ የሰራችው እስራኤል ዜጎቿን በመከተቡ ረገድም አመርቂ ስራን ሰርታለች ፤ በዚህ ሳምንት የሀገሪቱ ባለስልጣናት ቀሪ ነበር የተባለውን የመጨረሻ ገደብ በህዝብ መካከል ማስክ የማድረግ ገደብ እንዳነሱ ታውቋል።

@tikvahethiopia
#UAE 👉 #EGYPT #ETHIOPIA #ISRAEL

ባለፉት ቀናት የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ የኢትዮጵያን ጠቅላይ ሚኒስትር እና ከፍተኛ ባለልስጣናት፣ የግብፅ ፕሬዜዳንትን እንዲሁም የእስራኤል ፕሬዜዳንትን በሀገሯ ተቀብላ አድተናግዳለች።

ሀገሪቱ በቅድሚያ ያስተናገደችው የግብፁን ፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲን ሲሆን በመቀጠል ደግሞ የኢትዮጵያን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድን ዛሬ ደግሞ የእስራኤል ፕሬዜዳንት አይዛክ ሄርዞግን ነው።

ከሁሉም መሪዎች እና ባለስልጣናት ጋር ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል። የዛሬው የእስራኤሉ ፕሬዜዳንት ጉብኝት ግን ታሪካዊ መሆኑ ተነግሯል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#USA #Israel

የአሜሪካው ፕሬዜዳንት #ጆ_ባይደን እስራኤል ገብተዋል።

ባይደን በእስራኤል ቆያታቸው ጦርነቱ ከዚህም በላይ ከፍቶ እንዳይስፋፋ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ያደርጋሉ ተብሏል።

የአሜሪካ ብሄራዊ ደህንነት ቃል አቀባይ ፕሬዝዳንት ባይደን የቀጠለውን ጦርነት #ዓላማን በተመለከተ ለኔታንያሁ ከበድ ያሉ ጥያቄዎችን እንደሚጠይቋቸው ገልጸዋል።

ባይደን በቅድሚያ ይሄዳሉ ተብሎ የነበረው ወደ ዮርዳኖስ ነበር።

በዛም ከአረብ ሀገራት መሪዎች ጋር ይመክራሉ ተብሎ ነበር። ነገር ግን ከአሜሪካ ከተነሱ በኃላ የአረብ ሀገራት መሪዎች ከባይደን ጋር እንደማይገናኙ እና የነበረውም ስብሰባ መሰረዙ ተሰምቷል።

አሜሪካም ፕሬዜዳንቷ ወደ ዮርዳኖስ እንደማይሄዱና ይህም " የጋራ ውሳኔ " መሆኑን ገልጻለች።

" በእናተ አልተፈፀመም " - ባይደን

ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን እስራኤል በሆስፒታሉ ላይ ጥቃት አልፈፀመችም ብለዋል።

እስራኤል የሚገኙት ጆ ባይደን በጋዛ በሚገኘው " አል አህሊ ባፕቲስት ሆስፒታል " ላይ ፍንዳታ የተፈፀመው በእስራኤል ሳይሆን " በሌላኛው ቡድን " ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ባይደን ለእስራኤሉ ጠ/ሚ ኔታንያሁ ፤ " ትናንትና በጋዛ ሆስፒታል በደረሰው ፍንዳታ በጣም አዝኛለሁ " ያሉ ሲሆን " ባየሁት መሰረት፣ የተደረገው በሌላው ቡድን ይመስላል ፤ እንጂ በአንተ (እስራኤል) አይደለም " ሲሉ ተናግረዋል።

እስራኤል ፤ በሆስፒታሉ ላይ ለደረሰው ጥቃት ያልተሳካ " የኢስላሚክ ጂሃድ " ቡድን ሮኬት ነው ያለች ሲሆን " ሃማስ " እንዲሁም " የፍልስጤም ኢስላሚክ ጂሃድ " ድርጅት ጥቃቱ የተፈፀመው በእስራኤል ነው ብለዋል።

" የፍልስጤም ኢስላሚክ ጂሃድ " የእስራኤል ክስ ሀሰተኛ እና ምንም መሰረት የሌለው እንዲሁም ከጭፍጨፋው ተጠያቂነት ለማምለጥ ጣቷን በእስላሚክ ጂሃድ እና ፍልስጤማውያን ላይ የጠቆመችበት የተለመደ የሀሰት እና ቅጥፈት ፈጠራዋ ነው ብሏ

More + @BirlikEthiopia