TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.4K photos
1.39K videos
199 files
3.72K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#SUDAN #DrWorknehGebeyhu

የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በሱዳን የአንድ ቀን የስራ ጉብኝት አድርገዋል።

ዋና ፀሀፊው በስራ ጉብኝታቸው ከሱዳን ጦር አዛዥ እና የሃገሪቱ ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር ሌ/ጄ አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን ጋር ተገናኝተው መወያየታቸውን አሳውቀዋል።

በውይይቱ ኢጋድ ማክሰኞ ዕለት በኬንያ፣ ናይሮቢ ስለሚያካሂደው ስብሰባ የተነሳ ሲሆን ዶ/ር ወርቅነህ ከውይይቱ በኃላ በሰጡት መግለጫ በኢጋድ ስብሰባ ላይ የሁሉም አባል ሀገራት መሪዎች እንደሚገኙ ማረጋገጠናቸውን ገልፀዋል።

ስብሰባው እጅግ በጣም በወሳኝ ሰዓት የሚደረግ ስብሰባ ነው ተብሏል።

ስብሰባውን በተመለከት ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ፤ " እጅግ በጣም ወሳኝ ስብሰባ ነው " ያሉ ሲሆን " የሁሉም አባል ሀገራት መሪዎች እንደሚመጡ አረጋግጠውልናል ፤ የቀጣናው ጉዳይ በመሪዎችችን አማካኝነት ይመከርበታል ይህ እጅግ በጣም ትልቅ ዜና ነው " ብለዋል።

" መሪዎቻችን ቀጠናውን በሚያሳስቡ ጉዳዮች ላይ ፣ ለሰላም እና ደህንነት እንቅፋት ስለሆኑ ጉዳዮች ፣ በድርቁ ሁኔታ ላይ " ይመክራሉ ሲሉም ገልፀዋል።

ሱዳን የወቅቱ የኢጋድ ሊቅመንበር መሆኗ ይታወቃል።

@tikvahethiopia