TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ጥንቃቄ

ዛሬ ጥዋት ፤ በወላይታ ዞን #ከአረካ ወደ #ሶዶ ተሳፋሪዎችን ጭኖ ይጓዝ በነበረ አንስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ መኪና ላይ የመገልበጥ አደጋ ደርሷል።

በአደጋውም የአንድ ሰው ሕይወት ሲያልፍ 4 ሰው ላይ ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱ ታውቋል።

- አደጋ የደረሰበት ተሽከርካሪ ፦ ኮድ-3 ደቡብ 25715 በተለምዶ ሀይሩፍ እየተባለ የሚጠራው መኪና ነው።

- 17 ተሳፋዎችን ይዞ ከፍጥነት በላይ ሲጓዝ መሥመር በማሳት ከላሾ ከተማ ወረድ ብሎ በሚገኘው ካሬታ ሃታ/ወንዝ ውስጥ ገብቷል።

- በአደጋው የአንድ ሰው ህይወት ሲየልፍ በአራት ሰው ላይ ቀላል አደጋ ደርሷል።

የሶዶ ዙሪያ ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ፤ የመኪና አሽከርካሪዎች ጊዜው #የዝናብ_ወቅት ስለሆነ በክፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያሽከረከሩ ጥሪ አቅርቧል።

መረጃው የወላይታ ዞን ኮሚኒኬሽን ነው።

@tikvahethiopia @tikvah_Eth_BOT