TIKVAH-ETHIOPIA
1.47M subscribers
56.1K photos
1.4K videos
202 files
3.8K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ዛሬ በፕሪቶሪያ ፤ በኢትጵያ መንግስት እና ህወሓት መካከል የተፈረመው የሰላም ስምምነትን በተመለከተ የወጣው የጋራ መግለጫ 12 ነጥብ የያዘ ነው። ከዚህም ስምምነት መካከል ፦ - የህወሓት ቡድን #ትጥቅ_እንዲፈታ ከስምምነት ተደርሷል። - የኢትዮጵያን #ሉዓላዊነት እና #የግዛት_አንድነት ለማረጋገጥ እና የኢፌደሪ ሕገ-መንግሥቱን ለማስከበር የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ተስማምተዋል። …
#ETHIOPIA🇪🇹

#በኢትዮጵያ_መንግስት እና #በህወሓት መካከል የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ይዘት የሚገልፅ 12 ነጥብ ያለው #የጋራ_መግለጫ ከላይ ተያይዟል።

ነገ ሁለት ዓመት የሚደፍነውን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሰላማዊ መፍትሄ እንዲበጅለትና ህዝቡም እረፍት እንዲያገኝ ፤ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ፣ አርሶ አደሮችም ወደ እርሻቸው ፣ ሰራተኞችም ወደ ስራቸው፣ ነጋዴዎችም ወደንግዳቸው እንዲመለሱ አጠቃላይ የቀደመው ሁኔታ እንዲፈጠር  ሁሉም አካል ዛሬ ወደ ተደረሰው " የሰላም ስምምነት " #ተፈፃሚነት እና #ተግባራዊነት ላይ ትኩረት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።

የአፍሪካ ህብረት ፤ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ የዛሬው ስምምነት በስኬት እንዲጓዝ እና ሰላም እንዲሰፍን  የስምምነቱ ትግበራ " ወሳኝ ይሆናል " ሲሉ ነው ያስገነዘቡት።

በዚሁ አጋጣሚ ለሰላም መስፈን የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ከሚጫወቱት ሚና ባለፈ በዚህ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ጥላቻ እና እርስ በእርስ መራራቅን ከሚሰብኩ ንግግሮች በመቆጠብ በሰላም ማስፈኑ የራሳቸውን ድርሻ መወጣት አለባቸው።

@tikvahethiopia