TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Tigray

ምክትል ጠ/ሚና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዛሬ በቪድዮ መልዕክት አሰራጭተዋል።

በመልዕክታቸውም በትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ በመጠቀም የተለያዩ አካላት በኢትዮጵያ ላይ ጫና ለመፍጠር የሚያደርጉት ጥረት ኢትዮጵያን አሳዝኗል ብለዋል።

ኢትዮጵያ አሁን ላይ የሚያስፈልጋት ጠንክራ ድጋፍ መሆኑን በመግለፅ፥ የኢትዮጵያን ህዝቦችና የግዛት አንድነት አንዲሁም ትስስርን በሰብዓዊነት ሽፋን ዝቅ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት ተቀባይነት የለውም ሲሉ አስረግጠው ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ በትግራይ ክልል ሰብዓዊ ድጋፍን ከፍ ለማድረግ፣ ማህበራዊ ትስስርን መልሶ ለመገንባት እና መሰረታዊ የሆኑ አገልግሎቶችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ ከሁሉም አጋሮቿ ጋር ለመስራት ዝግጁ ናት ሲሉም ተደምጠዋል።

በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ወገኖች በሰብዓዊነት ሽፋን የኢትዮጵያን ህዝቦች እና የግዛት አንድነት እና ትስስር ለማዳከም ተልእኮ ይዘው ሲሰሩ ማየት 'የሚያሳዝን ተግባር ነው' እነዚህ ግለሰቦች እና አጋሮቻቸው ከዚህ ተግራቸው እንዲታቀቡ አሳስበዋል።

አቶ ደመቀ፥ "ኢትዮጵያ በራሷ ዜጎች ላይ ረሃብን እንደ ጦር መሣሪያነት እየተጠቀመች ነው" በሚል በሀገሪቱ ላይ የተለጠፉ ክሶች መሰረተ ቢስ ናቸው ብለዋል፤ እንደዚህ አይነት ክሶች በምንምን ስሌት ሰላምንና መረጋጋትን ለመፍጠር አይረዱም።

የኢትዮጵያ መንግስት የሰብዓዊ ድጋፍ ሰጪ አካላት በትግራይ ውስጥ በነጻነት እንዲሰሩ የሚያስችሉ አሰራሮች መዘርጋቱን ገልፀው፥ “አንዳንድ ተዋንያን ግን በሰብዓዊ ዕርዳታ ሽፋን የሽብርተኞችን ቡድን ለማስታጠቅ መሣሪያዎችን በድብቅ ለማስገባት መሞከራቸውን የሚያመለክቱ ተዓማኒ #ማስረጃዎች እንዳሉ ተናግረዋል፤ይህ አይነቱ ድርጊትት ተቀባይነት የለውም ብለዋል።

#AlAIN
@tikvahethiopia