TIKVAH-ETHIOPIA
1.4M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ለገጣፎ ለገዳዲ‼️

የለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር በህገወጥ መንገድ ተገንብተዋል ያላቸውን መኖሪያቤቶች ማፍረስ ጀምሯል። በያዝነው ሳምንት ብቻ 3,685 ቤቶች እንደሚፈርሱ የከተማው ከንቲባ ወይዘሮ #ሀቢባ_ሲራጅ ለOMN ተናግረዋል። በቀጣያ 12ሺ ቤቶችን ለማፍረስ እቅድ መያዙንም ከንቲባዋ ተናግረዋል።

ከንቲባዋ እንደሚሉት ቤቶቹን ለማፍረስ የተገደዱት የከተማው #መሪ_ዕቅድን_በመጣስ ለአረንጓዴ ቦታ (green area) በተከለለ ስፍራ በመሰራታቸው ነው። መኖሪያ ቤታቸው እንዲፈርስ የተወሰነባቸው ዜጎች በበኩላቸው በከተማው ለአመታት መኖራቸውንና በህጋዊ መንገድ ግብር ሲከፍሉ መቆየታቸውን ለዋልታ ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

Via ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢዜማ የኢዜማ የአመራሮች ምርጫ ውጤት እስካሁን (ምሽት 4:18 ድረስ) ይፋ ያልሆነ ሲሆን ፓርቲው ቆጠራው እንደተጠናቀቀ ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቋል። የጉባኤው አባላት የአመራሮችን ምርጫ ውጤት እየተጠባበቁ ይገኛሉ። ተከታትለን እናሳውቃለን ! @tikvahethiopia
#NewsAlert #ኢዜማ

ፕሮፌሰር ብርሃኑ መሪ ፤ አርክቴክት ዮሐንስ ደግሞ ምክትል መሪ ሆነው ተመረጡ።

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) አንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ ሰኔ 26 ቀን 2014 ዓ.ም ባደረገው ምርጫ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋን እና አርክቴክት ዮሐንስ መኮንንን የኢዜማ #መሪ እና #ምክትል_መሪ አድርጎ መርጧል፡፡

በጉባኤው ላይ ወደ 900 ገደማ የፓርቲው አባላት ያተሳተፉ ሲሆን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ 549 ድምፅ ማግኘታቸው ተገልጿል።

ከፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ጋር ለመሪነት የተወዳደሩት አቶ አንዱአለም አራጌ 326 ድምፅ ነው ያገኙት። አቶ አንዱአለም ከፓርቲው ምስረታ አንስቶ የፓርቲው ምክትል መሪ ሆነው ቆይተዋል።

ለምክትል መሪነት የተወዳደሩት አርክቴክት ዮሐንስ መኮንን በጉባኤው የተመረጡ ሲሆን ለቦታው በተፎካካሪነት ቀርበው የነበሩት አቶ ሀብታሙ ኪታባ ነበሩ።

@tivahethiopia
" 3 የኤጀንሲው ሰራተኞች በቁጥጥር ስር ውለዋል "

የአዲስ አበባ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ 3 የኤጀንሲው ሰራተኞች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ማድረጉን አስታወቀ።

ኤጀንሲው ፤ የህትመት ስርጭት እና አጠቃቀም ላይ መደበኛ የኦዲት ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጾ በዚህም በተገኘው ግኝት የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ  ጽ/ቤት የወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና ማስረጃ ቡድን #መሪ እና 2 ባለሙያዎች በሰሩት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል ሲል ገልጿል።

ኤጀንሲው የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት በደረሰው ጥቆማ ላይ ተመስርቶ ባሰባሰበው ማስረጃ ፦

- ለወረዳው ፈቃድ ሳይሰጥ የውጭ ዜጎችን #ገንዘብ_በመቀበል ጋብቻ በመፈፀም፣

- ባልተሟላ ማስረጃ የልደት ምዝገባ በማከናወን እንዲሁም በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ባለሙያዎችዎቹ ተጠርጥረው ከስራ እንዲታገዱ በማድረግ የወንጀል ምርመራ እንዲካሄድ አድርጓል ብሏል።

በተመሳሳይ ሁኔታ ኤጀንሲው ፤ #በለሚ_ኩራ ክ/ከተማ  ወረዳ 13 ጽህፈት ቤት 1 ቡድን መሪ እና ባለሙያዎች በወንጀል ጉዳዮቸው እየታየ መሆኑ አስታውሷል።

ነዋሪዎች የትኛውንም ዓይነት ቅሬታ ፣ ጥቆማ ወይም መረጃ ለመስጠት የኤጀንሲውን ነፃ የስልክ መስመር 7533 መጠቀም ይችላሉ ተብሏል።

@tikvahethiopia