TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.6K photos
1.39K videos
200 files
3.74K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#NewsAlert

" ከዛሬ ጀምሮም ሲሚንቶ በየትኛውም ቦታ ቁጥጥር እና ክትትል ሳይደረግበት በነጻ ገበያ ይካሄዳል " - የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር

ሲሚንቶ በነጻ ገበያ እንዲሸጥ ተወሰነ።

የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከዚህ በፊት የነበረው የሲሚንቶ ሽያጭ መመሪያ መቀየሩን ገለፀ።

መመሪያው የሲሚንቶ ዋጋ በመንግሥት ተወስኖ እንዲሸጥ መደረጉ በርካታ ቅሬታዎች ሲነሳበት እንደነበር ገልጾ በዚህም ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ሲሚንቶን በቀላሉ እንዳያገኙ አድርጓቸው እንደነበር አሳውቋል።

በተሻሻለው መመሪያ መሰረትም አከፋፋዮችን እና ቸርቻሪዎችን መምረጥ የፋብሪካዎቹ እድል ነው ተብሏል።

የፋብሪካዎቹ የመሸጫ ዋጋ ለጊዜው ምርታማነት እስከሚጨምር ድረስ የፋብሪካ ዋጋ በስድስት ወር አንድ ጊዜ በሚኒስቴሩ እንደሚወሰን ተገልጿል።

#መንግስት ከግብይቱ የወጣ ሲሆን በተሻሻለው መመሪያ መሰረትም መንግስት ሽያጩ ያለ ደረሰኝ እንዳይካሄድ ቁጥጥር እንደሚያደርግ ሚኒስቴሩ አሳውቋቃ።

በግብይቱ ውስጥም ህጋዊ ንግድ ፍቃድ እና ደረሰኝ ግዴታ መሆናቸውን የተጠቆመ ሲሆን እያንዳንዱ ፋብሪካ የተደራሽነት አድማሱን በማስፋትም አከፋፋዩን የመምረጥ ፍላጎት እንዳለው ተነግሯል።

ከዛሬ ጀምሮም ሲሚንቶ በየትኛውም ቦታ ቁጥጥር እና ክትትል ሳይደረግበት በነጻ ገበያ ይካሄዳል ብሏል ሚኒስቴሩ።

ከፋብሪካ ሲሚንቶ የሚወጣ ማንኛውም ተሽከርካሪ የመዳረሻ ሰነድ መያዝ እንደሚኖርበት የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አሳስቧል።

Credit : #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert " ከዛሬ ጀምሮም ሲሚንቶ በየትኛውም ቦታ ቁጥጥር እና ክትትል ሳይደረግበት በነጻ ገበያ ይካሄዳል " - የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሲሚንቶ በነጻ ገበያ እንዲሸጥ ተወሰነ። የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከዚህ በፊት የነበረው የሲሚንቶ ሽያጭ መመሪያ መቀየሩን ገለፀ። መመሪያው የሲሚንቶ ዋጋ በመንግሥት ተወስኖ እንዲሸጥ መደረጉ በርካታ ቅሬታዎች ሲነሳበት እንደነበር ገልጾ…
#ሲሚንቶ

ፋብሪካዎች ያቀረቡት የመሸጫ ዋጋና የተወሰነው መሸጫ ዋጋ !

👉 ዳንጎቴ

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 549.49
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 811.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤795.93

👉 ደርባ

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 590.59
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 779.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 761.55

👉 ሙገር

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 643.95
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 802.73
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 755.70

👉 ናሽናል

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል➤ 561.00
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 779.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 756.50

👉 ሀበሻ

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 683.44
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 947.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 754.48

👉 PIONEER

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 510.04
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 1783.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 753.95

👉 ኢትዮ

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 595.66
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 973.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 753.60

👉 INCHINI

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 0
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 1298.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤750.21

👉 KUYU

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 628.10
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤1019.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 752.50

👉 ኢስት

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 506.99
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 1064.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤753.82

👉 ካፒታል

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 633.38
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 905.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤751.34

#አማካይ

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 590.3
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 1014.6
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 758.1

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የፌደራል መንግስት እና የህወሓት ኃላፊዎች በአንድ ሳምንት ግዜ ውስጥ (ታህሳስ ወር ከማለቁ በፊት) የትግራይ ክልል መዲና መቐለ ላይ ተገናኝተው ቀሪ ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩ ተገልጿል።

ይህ የተገለፀው ዛሬ በናይሮቢ በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።

የቀድሞው የኬንያ ፕሬዜዳንት አሁሩ ኬንያታ ፤ " በሰላም ስምምነቱ አፈፃፀም ዙርያ በርካታ ስኬቶች እየተመዘገቡ ነው። " ያሉ ሲሆን " መጪው የኢትዮጵያ የገና በአል የሰላም በአል እንደሚሆን አንጠራጠርም። የውጪ ሀይሎች ከትግራይ መውጣትም በስምምነቱ ላይ ያለ ጉዳይ ነው፣ አካሄዱም በእሱ መሰረት የሚፈፀም ይሆናል።" ብለዋል።

ዛሬ ናይሮቢ ላይ በተጠናቀቀው ውይይት ላይ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን፣ ዶ/ር ጌድዮን ጢሞቲዎስ፣ ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ፣ አቶ ጌታቸው ረዳ፣ ሌ/ጀ ታደሰ ወረደ፣ ጄነራል ፃድቃን ገ/ተንሳይ እና ሌሎችም ተካፍለው እንደነበር ተገልጿል።

የአፍሪካ ህብረት ያወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ ሙሉ ሃሳብ ከላይ ተያይዟል።

Credit : Elias Meseret
Photo : Social Media

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

የፍ/ቤት መጥሪያ ፈርመው ወስደው ሳይቀርቡ ቀርተዋል የተባሉት የአዲስ አበባ ቤቶች ኮርፖሬሽን ኃላፊ አቶ ሽመልስ ታምራት #ታስረው እንዲቀርቡ በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት አዘዘ።

አቶ ሽመልስ "የኮንዶሚኒየም ቤቶች ዕጣ ተጭበርብሯል" ተብሎ የከባድ ሙስና ወንጀል በቀረበባቸው ተከሳሾች ላይ የዓቃቢህግ 2ኛ ምስክር ሆነው የተቆጠሩ ሲሆን መጥሪያ ፈርመው ተቀብለው ባለመቅረባቸው ምክንያት ነው ታስረው እንዲቀርቡ ፍ/ቤት ያዘዘው።

ሃምሌ 1/2014 ከኮንዶሚኒየም ቤቶች ዕጣ አወጣጥ ጋር ተያይዞ  ዕጣው ተጭበርብሯል ተብሎ የአ/አ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱንና ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አብርሀም ሰርሞሌን ጨምሮ አጠቃላይ በ11 ተከሳሾች ላይ በየደረጃው የከባድ ሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል።

ተከሳሾቹ ወንጀሉን አለመፈጸማቸውንና ጥፋተኛ አለመሆናቸውን ገልጸው የሰጡትን የዕምነት ክህደት ቃል ተከትሎ ዓቃቢህግ ምስክር እንዲሰሙለት ጠይቆ ነበር።

በዚህ መሰረት ዓቃቢህግ ከቤቶቹ ዕጣ አወጣጥ ስርዓት ጋር ተያይዞ እንዲሁም ለምቷል የተባለው ሶፍትዌርን የሚመለከትና የተደረገ የኦዲት ስርዓትን ላይ ያተኮረ ምስክርነት እንዲሰማለት የምስክር ጭብጥ ካስመዘገበ በኋላ በህዳር 22/ 2015 ጀምሮ ፍ/ቤቱ የዓቃቢህግ ምስክር ቃል መሰማት ጀምሮ ነበር።

ፍ/ቤቱ እስካሁን የ8 የዓቃቤ ህግ ምስክሮችን ቃል ያዳመጠ ሲሆን በ2ኛ የዓቃቢህግ ምስክር ሆነው የተቆጠሩት የአ/አ ቤቶች ኮርፖሬሽን ኃላፊ አቶ ሽመልስ ታምራት ግን መጥሪያ ደርሷቸው ፈርመው የወሰዱ ቢሆንም በችሎት ሳይቀርቡ ቀርተዋል።

ፍ/ቤቱም ግለሰቡ በፖሊስ ታስረው በይደር እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

ምንጭ፦ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሲሚንቶ ፋብሪካዎች ያቀረቡት የመሸጫ ዋጋና የተወሰነው መሸጫ ዋጋ ! 👉 ዳንጎቴ - በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 549.49 - አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 811.00 - የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤795.93 👉 ደርባ - በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 590.59 - አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 779.00 - የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 761.55 👉 ሙገር - በስራ ላይ…
#ሲሚንቶ

የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በልሁ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ስለሆነው የሲሚንቶ ስርጭትና ግብይት መመሪያ ምንድነው ያሉት ?

አቶ ተሻለ በልሁ ፦

" ... አዲሱ መመሪያ አንደኛ የቀየረው ሲሚንቶ በገበያ ስርዓት ይመራ ነው። በገበያ የሚመራ ሲባል ምን ማለት ነው አከፋፋዮቻቸውን ፤ ቸርቻሪዎቻቸውን የመምረጥ ነፃነት #የፋብሪካዎች ነው። እስከዛሬ ማን ነበር የሚመርጥላቸው ? ሁለቱ ከተሞች እና ክልሎች ነበሩ። ስለዚህ ይሄ መመሪያ ከዛሬ ጀምሮ #የመንግስት_አካል አከፋፋይ እና ቸርቻሪ አይመርጥም።

ለተወሰነ ጊዜ ምርታማነት እስከሚጨምር በገበያ የሚፈለገውን ያህል መጠን ፋብሪካዎቻችን አምርተው ማሰራጨት እስከሚችሉ ድረስ የፋብሪካ የብር ዋጋ ብቻ በሚኒስቴሩ ይተመናል ይሄም በ6 ወር አንዴ ብቻ ነው እንደ አስፈላጊነቱ ፤ አላስፈላጊ ከሆነ ገበያው እራሱ የሚመራው ከሆነ የዋጋ ተመን አይኖርም።

ሌሎቹን ማን ይተምናቸዋል ? መመሪያው ያስቀመጠው የትራንስፖርት ዋጋን ፣የወራጅ እና አውጪ ዋጋን፣ ውስን ትርፍ ህዳግን መነሻ በማድረግ የፋብሪካ ብር መሸጫ ዋጋን እንደ ቤንች ማርክ ወስደው ፋብሪካዎቹ እያንዳንዳቸው ያሳውቃሉ። ስለዚህ መንግስት ከፋብሪካ ውጭ ያለውን ዋጋ አይተምንላቸውም የሚተምነው ማነው ? ፋብሪካዎች ናቸው ። "

@tikvahethiopia
#መልዕክት

እድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት ፦

- የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት፣
- የቫይታሚን ኤ ጠብታ፣
- የአንጀት ጥገኛ ትላትል መድሀኒት፣
- የህፃናት የዞረ እግር ልየታ
- የምግብ እጥረት ልየታ እንዲሁም
- ለእናቶች ከወሊድ ጋር የተያያዘ ፊስቱላ ልየታ ከትላንት ታህሳስ 13 ጀምሮ በጤና ተቋማት እና በጊዜያዊ ክትባት መስጫ ጣቢያዎች መሰጠት ተጀምሯል።

ይኸው ዘመቻ የሚዘልቀው እስከ 22 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።

በተለይ የቫይታሚን ኤ ጠብታ ህፃናት #በሽታን_የመከላከል አቅማቸው እንዲጎለብት እና በዳፍንት በሽታ በቀላሉ እንዳይጠቁ ያደርጋል።

በተቀናጀ የኩፍኝ ክትባት ወቅት እድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት የቫይታሚን ኤ ጠብታ ስለሚሰጥ ወላጆች በአቅራቢ ወደሚገኝ የጤና ተቋም ወይም ጊዜያዊ ክትባት መስጫ ጣቢያ በመሄድ ልጃችሁን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ አድርጉ።

ውድ ቤተሰቦቻችን ይህን መልዕክት ላልሰሙት ይደርስ ዘንድ ሼር / ፎርዋርድ ያድርጉላቸው።

@tikvahethiopia
" ለኢትዮጵያ የሚያደርገው የልማት እና የምጣኔ ሀብት ድጋፍ ቀስ በቀስ ወደ ነበረበት እንዲመለስ ይደርጋል " - የአውሮፓ ህብረት

የአውሮፓ ህብረት ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በህወሓት መካከል የተደረሰው ስምምነት ተፈጻሚ መሆን ህብረቱ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያደርገውን ግንኙነት መልሶ ለመጀመር የሚያስችለውን ሁኔታ እንደሚፈጥር ገልጿል።

ህብረቱ ምን አለ ?

- ህብረቱ ከስምምነቱ መፈረም በኋላ ያታዩ ለውጦችን አድንቋል። ለዚህም ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።

- የስምምነቱ በዘላቂነት ተግባራዊ መሆን ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ስትራቴጂያዊ ግንኙነትን መልሶ ለመጀመር እንደሚያስችለው አሳውቋል።

ማስታወሻ ፦ የአውሮፓ ኅብረት በሰሜን ኢትዮጵያ የተጀመረውን ጦርነት ተከትሎ ወደ 110 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ የበጀት ድጋፍ እንዲዘገይ ማድረጉ ይታወሳል።

- የተኩስ አቁሙ ተግባራዊ መሆን፣ ያልተገደበ የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት እና ለመብት ጥሰቶች ተጠያቂነት መኖር ለኢትዮጵያ የሚያደርገው የልማት እና የምጣኔ ሀብት ድጋፍ ቀስ በቀስ ወደ ነበረበት እንዲመለስ ያደርጋል ብሏል።

- በሰሜን ኢትዮጵያ እና በሌሎች የአገሪቱ ክፍል ከፍተኛ የእርዳታ አቅርቦት ፍላጎት በመኖሩ ያልተገደበ የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት እና መሠረታዊ አገልግሎቶች ሙሉ ለሙሉ ወደነበሩበት እንዲመለሱ ማድረግ አስፈላጊ ነው ሲል ገልጿል።

- ኤርትራን በተመለከተ የድንበር ጦርነቱን ተከትሎ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መንግሥታት መካከል የተደረሰውን #የአልጀርስ_ስምምነት እንዲሁም ከአራት ዓመት በፊት የተደረሰውን የሰላም ስምምነትን ጠቃሚነት ገልጾ ፤ የኤርትራ ሠራዊት በአስቸኳይና ሙሉ ለሙሉ ከኢትዮጵያ እንዲወጣ ጠይቋል።

#BBC

@tikvahethiopia
#ክብሩ_ዶክተር_አጋ_ጠንጠኖ

የክብር ዶክተር አጋ ጠንጠኖ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

የክብር ዶ/ር አጋ ጠንጠኖ ማን ነበሩ ?

- በ1937ዓ.ም ነበር ከአባታቸው ጠንጠኖ ጉዬ እና ከእናታቸው ጋልጋሉ ሃላኬ የተወለዱት።

- ከ1990 ዓ.ም ጀምሮ የጉጅ ኦሮሞ አባ ገዳ በመሆን ህዝባቸውን አገልግለዋል።

- የስልጣን ጊዜያቸውን አጠናቀው በገዳ ስርዓት የአስተዳደር ጊዜያቸውን ለ73ኛው የጉጂ አባ ገዳ ዋቆ ዱቤ በ2000ዓ.ም ነበር ያስረከቡት  ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ከኋላቸው ላሉት ለገዳ ስርዓት መሪዎች እንዴት ሀገርን መምራት እና አብሮ መኖር እንደሚችሉ በመምከር እና ሰላምን በማጎልበት ትልቅ ስራ ሲሰሩ ቆይተዋል።

- የገዳን ሥርዓት ለሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብና ለዓለም በማስተዋወቅ ረገድ ከገዳ ምክር ቤት ጋር ሠርተዋል።

- በህይወት ዘመናቸው መቻቻል፣ መከባበር እና በሰላም አብሮ የመኖር ባህልን በመገንባት ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። 

- የገዳ ትምህርት በዩንቨርሲቲዎች እንዲሰጥ እና የገዳ ስርዓት በተባበሩት መንግስታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት (UNESCO) እንዲመዘገብ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክተዋል።

- በ2008 ዓ.ም ካቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ተሰጥቷቸዋል።

መረጃው ምንጭ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update #AddisAbaba

የ2ኛውን ዙር የሀገር አቀፍ ብሄራዊ ፈተና ለመፈተን #በአዲስ_አበባ ከተማ አስተዳደር የተመዘገቡ ተማሪዎች በክፍለ ከተማቸው በኩል በ16 / 4 /2015 ዓ/ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሳይንስና ቴክኖሎጂ 5 ኪሎ ካምፓስ እንዲገቡ የከተማው ትምህርት ቢሮ ዛሬ አሳስቧል።

የ2ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከታህሳስ 18 እስከ ታህሳስ 21 ቀን 2015 ዓ/ም ድረስ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ መግለፁ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba የፍ/ቤት መጥሪያ ፈርመው ወስደው ሳይቀርቡ ቀርተዋል የተባሉት የአዲስ አበባ ቤቶች ኮርፖሬሽን ኃላፊ አቶ ሽመልስ ታምራት #ታስረው እንዲቀርቡ በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት አዘዘ። አቶ ሽመልስ "የኮንዶሚኒየም ቤቶች ዕጣ ተጭበርብሯል" ተብሎ የከባድ ሙስና ወንጀል በቀረበባቸው ተከሳሾች ላይ የዓቃቢህግ 2ኛ ምስክር ሆነው የተቆጠሩ ሲሆን መጥሪያ…
#Update

የፍ/ቤት መጥሪያ ፈርመው ወስደው በቀጠሮ ቀን ሳይቀርቡ የቀሩት የአዲስ አበባ ቤቶች ኮርፖሬሽን ኃላፊ አቶ ሽመልስ ታምራት ታስረው እንዲቀርቡ ትናንት በነበረ ቀጠሮ ትዕዛዝ የወጣባቸው ቢሆንም ዛሬም ሳይቀርቡ መቅረታቸው ተሰምቷል።

አቶ ሽመልስ ታምራት " የኮንዶሚኒየም ቤቶች ዕጣ ተጭበርብሯል" ተብሎ የከባድ ሙስና ወንጀል በቀረበባቸው ተከሳሾች ላይ የዓቃቢህግ 2ኛ ምስክር ሆነው የተቆጠሩ ሲሆን መጥሪያ ፈርመው ተቀብለው ባለመቅረባቸው ምክንያት ነው ታስረው እንዲቀርቡ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ያዘዘው።

ምንም እንኳን ፍ/ቤቱ ታስረው እንዲቀርቡ ቢያዝም ኃላፊው ዛሬም እንዳልቀረቡ ተገልጿል።

በሌለ በኩል ዛሬ በነበረ ችሎት በአ/አ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ለምቷል የተባለውን ሶፍትዌር በሚመለከት በስራ ኃላፊነት ቁጥጥርና ክትትል አላደረጉም ተብለው የተከሰሱት የአ/አ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ የነበሩት ዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱ የባለቤታቸውና የራሳቸው የባንክ ሒሳባቸው መታገዱን ተከትሎ የህጻናት የልጆቻቸው ት/ቤት ሊቋረጥባቸው እንደሆነ ገልፀወል።

ዶ/ር ሙሉቀን ለህጻናቱ ምሳ መቋጠር የማይቻልበት ደረጃ ላይ መደረሱንና ችግር ላይ መሆናቸውን የዕንባ እየተናነቃቸው ለችሎቱ ገልጸዋል።

በተጨማሪ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ላይ በነበሩበት ወቅት ወላጅ አባታቸው መታሰራቸውንና ወላጅ እናታቸው በአሁን ወቅት ህመምተኛ መሆናቸውንና ችግር ላይ መሆናቸውን ገልጸው የተፋጠነ ፍትህ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

የችሎቱ ዳኞች በተቻለ መጠን ተከሳሾች የተፋጠነ ፍትህ እንዲያገኙ እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል።

ያንብቡ: telegra.ph/Tarik-Adugna-12-23

(Credit: ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ)

@tikvahethiopia
#መቐለ #ራያ #አክሱም #ዓዲግራት

ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ስድስት አባላት ያሉት የባለሙያዎች ቡድን ወደ አክሱም ዩኒቨርሲቲ በማቅናት ምልከታ ሊያደርግ ነው፡፡

በግጭቱ ምክንያት ሥራ ያቋረጡትን አክሱም፣ ራያ፣ አዲግራት እና መቐለ ዩኒቨርሲቲዎች ወደ አገልግሎት ለመመለስ ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሠራ መሆኑ ተገልጿል።

እስካሁን ባለው ሁኔታ አክሱም እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ዳግም ወደ አገልግሎት በሚመለሱበት ሁኔታ ላይ ንግግር መጀመሩን በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደር እና መሰረተ ልማት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ለፋና ተናግረዋል።

በቀጣይም ከመቐለ እና አዲግራት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ግንኙነት እንደሚጀመር ኃላፊው አመላክተዋል፡፡

በአክሱም ከተማ የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ ተከትሎ፤ ስድስት አባላት ያሉት የባለሙያዎች ቡድን ከሰኞ ጀምሮ የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ዋናውን ግቢ ጨምሮ አድዋ እና ሽረ ግቢዎችን በስፍራው በመገኘት ምልከታ ያደርጋል ብለዋል፡፡

ቡድኑ ተቋማቱ በሰው ኃይል፣ በመሰረተ ልማት፣ በቤተ ሙከራ፣ በኔትወርክ፣ በመኝታና መማሪያ ክፍሎች፣ በማስተማሪያ ሆስፒታል፣ በቤተ መጻሕፍት እና ሌሎች አገልግሎቶች ዩኒቨርሲቲው የመማር ማስተማር ሥራውን ለማስጀመር የሚያስችለውን ሁኔታ ይመለከታል፡፡ #FBC

@tikvahuniversity