TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ዓለም ስለማይናማር ምን አለ?

#Australia

የአውስትራሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ማራይዝ ፓይኔ ፤ በማይናማር ወታደራዊ ኃይሉ ስልጣን መቆጣጠሩ እና ሲቪል መሪዎች መታሰራቸውን የሚገልፁ ሪፖርቶች እንዳሳሰባቸው ገልፀዋል። ወታደሩ የህግ የበላይነትን እንዲያከብር ፣ ችግሮችን በህግ ብቻ እንዲያስተካከል፤ በአስቸኳይ የሲቨል መሪዎችን እና ሌሎችንም ያለህግ አግባብ ያሰራቸውን አካላት እንዲለቅ ጥሪ አቅርበዋል።

#UnitedStates

አሜሪካ በማይናማር እየሆነ ያለውን ጉዳይ በቅርበት እየተከታተለች መሆኑን ገልፃለች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ጉዳዩ በጣም እንዳሳሰባቸውን ገልፀዋል፤ ወታደሩም ውሳኔውን በአስቸኳይ እንዲቀለብስ አሳስባዋል። የማይማር ወታደር ሁሉንም የሲቪል መሪዎች እንዲፈታ፣ የበርማን ህዝብ ፍላጎት እንዲያከብር (Nov 8 የተካሄደውን ምርጫ ማለታቸው ነው) አሳስበዋል። ብሊንከን አሜሪካ ከበርማ ህዝብ ጎም እንደምትቆም ገልፀዋል።

#UnitedNation

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሴክሬተሪ ጀነራል አንቶኒዮ ጉተሬዝ የማይናማር የሲቪል መሪዎች መታሰራቸውን በእጅጉ አውግዘዋል። ወታደሩ ስልጣን ጠቅልሎ መያዙ እንዳሳሰባቸው ገልፀዋል። ድርጊቱ በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ሪፎርም ላይ ችግር ሊያስከትል እንደሚችልም ጠቁመዋል።

#India

የህንድ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የማይናማር ጉዳይ እንዳሳሰበው ገልጿል። ህንድ በማይናማር የዴሞክራሲያዊ ሽግግር እንደምትደግፍ ገልፃ ፤ የህግ በላይነት እና የዴሞክራሲያዊ ሂደት መከበር አለበት ብላለች፤ በሀገሪቱ ያለውን ሁኔታ በቅርብ እየተከታተለች እንደሆነ አሳውቃለች።

#Singapore

ሲንጋፖር በማይናማር እየሆነ ያለው ጉዳይ እንዳሳሰባት የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጻል። ሁኔታውን በቅርብ እየተከታተለች እንደሆነም ገልፃለች።

#HumanRightsWatch

የHRW የኤዥያ ዳይሬክተር ብራድ አዳምስ በአስቸኳይ ያላምንም ቅድመ ሁኔታ ሳን ሱቺ እና ሌሎችም ያለህግ አግባብ የታሰሩ አካላት እንዲፈቱ ጠይቀዋል። የወታደሩ ድርጊት በህዳር ወር የተካሄደውን ምርጫ እና የማይናማር ህዝብ የራሱን መንግስት የመምረጥ መብት የሚጋፋ ነው ብለዋል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#UnitedNation

የተመድ ዋና ፀሀፊ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪች ትላንት በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተው የነበረ ሲሆን በመግለጫው ላይ የሰሜን ኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይን አንስተው ነበር።

ስቴፋን ዱጃሪች ምን አሉ ?

- በሰሜን ኢትዮጵያ አሁንም ግጭት መቀጠሉን እና አሁን ላይ ያለድ ሁኔታ ውጥረት የተሞላበት እንደሆነ ገልፀዋል።

- የአፋር ክልል ከትግራይ ጋር በሚዋሰንባቸው ቦታዎች ማለትም በያሎ እና ጉሊና ወረዳዎች እየተካሄደ ባለ ውጊያ ሳቢያ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተፈናቅለዋል።

- በአፋር እና አማራ አዋሳኝ ቦታ ጭፈራ ወረዳ ሰዎች ከቀያቸው መፈናቀላቸውን የሚገልፅ ሪፖርት መኖሩን አመልክተዋል።

- በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ከሚገኘው የጃራ የተፈናቃዮች መጠለያ ተጠልለው የነበሩ 30 ሺህ ሰዎችም ለሁለተኛ ጊዜ ተፈናቅለዋል።  

- ዳግም ባገረሸው ግጭት ሰዎች እየተፈናቀሉ መሆኑ የሰብዓዊ መብት ፍላጎትን ይጨምራል ብለዋል።

(ተጨማሪ ከላይ ተይይዟል)

@tikvahethiopia