TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION ደብረ ብርሃን ! የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት ወቅታዊ የፀጥታ ስጋትን አስመልክቶ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፏል። - በከተማው አስተዳደር በተፈናቃይ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ የሚኖር ተፈናቃይ ከምሽቱ 12:00  ሰዓት በኋላ ወደ መጠለያ ጣቢያውም ሆነ ወደ ከተማው መግባት ተከልክሏል። - ሁሉም አይነት ተሽከርካሪዎች ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት በኋላ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።…
#ATTENTION

ላሊበላ !

የላሊበላ ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት ወቅታዊ ሁኔታን መነሻ በማድረግ የሰዓት ዕላፊ ገደብን ጨምሮ ሌሎች ውሳኔዎችን አሳልፏል።

ውሳኔዎቹ ፦

- ከምሽቱ 1:00 ሰዓት እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ወደ ከተማዋ መግባትም ሆነ መውጣት አይቻልም።

- ማንኛውም ተሽከርካሪ ከምሽቱ 1:00 ሰዓት በኋላ እስከ ንጋቱ 12:00 ድረስ መንቀሳቀስ አይቻልም።

- ከተፈቀደለት አካል ውጭ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በጥብቅ ተከልክሏል።

- በመንግስት ዕውቅና ካለው የፀጥታ አካል ውጭ የፀጥታ አካላትን የደንብ ልብስ ለብሶ መንቀሳቀስ በፍፁም አይቻልም።

የላሊበላ ከተማ አስተዳደር ህዝቡ በሀሰተኛ ወሬ እና አሉባልታ ሳይደናገር አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ መልዕክት አስተላልፏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ATTENTION

ሰንበቴ !

የሰንበቴ ከተማ አስተዳደር ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ከነሐሴ 26/ 2014 ዓ/ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የሰዓት እላፊ ገደብ አውጇል።

በዚህም መሰረት ፦

- የከተማ ባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎች (ባጃጆች) ከምሽቱ 12 ሰአት ጀምሮ በከተማው ውስጥ ማሽከርከር ተከልክለዋል።

- ከተመደበው የጸጥታ ኃይል በስተቀር ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ #ማንኛውም_ሰው መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

የተጠቀሰው የሰአት እላፊ ገደብ ጥሶ የተገኘ ግለሰብ ላይ አስፈላጊው የህግ እርምጃ እንዲወሰድ ታዟል ሲል የከተማ አስተዳደሩ አስጠንቅቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION ሰንበቴ ! የሰንበቴ ከተማ አስተዳደር ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ከነሐሴ 26/ 2014 ዓ/ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የሰዓት እላፊ ገደብ አውጇል። በዚህም መሰረት ፦ - የከተማ ባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎች (ባጃጆች) ከምሽቱ 12 ሰአት ጀምሮ በከተማው ውስጥ ማሽከርከር ተከልክለዋል። - ከተመደበው የጸጥታ ኃይል በስተቀር ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት…
#ATTENTION

የጎንደር ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት ወቅታዊ ጉዳዮችን ታሳቢ በማድረግ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል።

ከውሳኔዎቹ መካከል ፦

- ከተፈቀደላቸው የፀጥታ አካላት ውጭ የተለያዩ የፀጥታ አካላት አልባሳትን መልበስ ተከልክሏል።

- ከፀጥታ መዋቅሩ ውጭ፣ በከተማው በብሎክ አደረጃጀት አካባቢን እንዲጠብቅ በተሰጠው ተራው ከተሰማራው ውጭ በየትኛውም ቦታ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው፡፡

- ማህበረሰቡን የሚያውኩ አሉባልታዎች ወይም የሃሰት መረጃዎችን በተለያዩ ሚዲያዎች፣ በመጠጥ ቤቶች ወዘተ ማሰራጨት ህዝቡን ማወዛገብ፣ ማሰጨነቅ በጥብቅ ተከልክሏል።

- በከተማው ያሉ ተፈናቃዮች ከተሰጣቸው መጠለያ ካምፕ ውጭ መንቀሳቀስ የተከለከለ ሲሆን ለገበያ፣ ለህክምና፣ ለአንገብጋቢ ጉዳዮች፣ ለተለያዩ ስራዎች ከመጠለያው መውጣት ያለበት ተፈናቃይ በሚመለከታቸው የካምፕ አስተባባሪዎችና በክ/ከተማው የፀጥታ መዋቅር እውቅና እና የመውጫና የመግቢያ ፈቃድ መለያ ካርድ ይዞ ተመዝግቦ ተፈቅዶለት የሚንቀሳቀስ ይሆናል፡፡

- በአሉባልታ ወሬዎችና ስበብ በመፈለግ ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ እንደ ባንክ ቤት፣ ሱቆችና ሆቴሎች፣ የገበያ ማዕከሎች እና የመሳሰሉትን መዝጋት ተከልክሏል።

- ከነሀሴ 27 ጀምሮ የቀበሌ መታወቂያ መስጠት ተከልክሏል። አስቸኳይ የሆነ ለምሳሌ ለህክምና፣ ወደ ዩኒቨርስቲ ለመሄድ፣ ወደ ውጭ አገር ለሚደረግ ጉዞ ከገጠሙ የክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚና የክ/ከተማው ሰላምና ደህንነት በጋራ በማየት መታወቂያ ሊሰጡ ይችላሉ።

- አግባብነት የሌለው የዋጋ ንረት የሚፈጥሩ በሸቀጦች በግብርና ምርቶች ላይ ተገቢ ያልሆነ ዋጋ ጨምሮ ህዝቡን ማስቃየት በጥብቅ ተከልክሏል።

- በጫት ቤቶች ተሰብስቦ በመቃም አሉባልታና ሽብር መንዛት ተከልክሏል።

(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION ወልድያ ! የወልድያ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን አካባቢ ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ከነሐሴ 22 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ የሰዓት እላፊ ገደብ አስቀምጧል። በዚህም ፦ • ከተመደበው የጸጥታ ኃይል በስተቀር ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ ማንኛውም ሰው መንቀሳቀስ #ተከልክሏል። • ለጸጥታ ስራ ስምሪት ከተሰጠው ተሽከርካሪ ውጭ ማንኛውም ተሽከርካሪ…
#ATTENTION

ወልድያ !

በዛሬው ዕለት የወልድያ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ም/ ቤት ከዚህ ቀደም ካሳለፈው ውሳኔ ተጨማሪ ውሳኔዎችን አሳልፏል።

የከተማውን አሁናዊ ሁኔታ መነሻ ከተማ በማድረግ የሰዓት እላፊ ገደብ መውጣቱ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ሌሎች ክልከላዎችን ማስቀመጥ አስፈልጓል ተብሏል።

ከተላለፉ ውሳኔዎች መካከል ፦

- ከፀጥታ መዋቅሩ ውጭ በየትኛውም ቦታ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በፍጹም ተከልክሏል።

- ከተፈቀደላቸው የመንግስት የፀጥታ አባላት ውጭ የሰራዊቱን አልባሳትን መልበስ በጥብቅ ተከልክሏል።

- በከተማው የሚገኙ የራያና ቆቦ ከተማ ተፈናቃዮች ውጭ ሌላው አካል ወደ መጣበት አካባቢ እንዲመለስ በጥብቅ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

- ሀሰተኛ ወሬ በመልቀቅ የከተማውን ማህበረሰብ የሚያውኩ አሉባልታዎችን በሚዲያዎችና በአገልግሎት መስጫ ተቋማት በማሰራጨት ህዝቡን ማዋከብ በጥብቅ ተክልሏል።

- በከተማ  የህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ ባንክ ቤት፣ ሱቆች፣ ሆቴሎች፣ ካፌና ሬስቶራንቶች፣ የንግድ ተቋማት እና የመሳሰሉትን መዝጋት ፍጹም ተከልክሏል።

- ከነሀሴ 29/2014 ዓ.ም ጀምሮ የቀበሌ መታወቂያ መስጠት ተከልክሏል።

- አግባብነት የሌለው የዋጋ ንረት መፍጠር፣ በሸቀጦችና በግብርና ምርቶች ላይ ተገቢ ያልሆነ ዋጋ ጨምሮ ህዝቡን ማስቃየት፣ በማንኛውም ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ ውስጥ መገኘት በህግ ያስጠይቃል።

(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ወልድያ ! የወልድያ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት የሰዓት እላፊ ገደብ ላይ የማሻሻያ ውሳኔ ዛሬ መስከረም 4 ቀን 2015 ዓ/ም አሳልፏል። ሌሎች ክልከላዎች እንደቀጠሉ ሆኖ በሰዓት እላፊ ገደብ ላይ የተደረገው ማሻሻያ ፦ - ከቀኑ 12:00 ሰዓት ጀምሮ የነበረው የተሽከርካሪ የሰዓት እላፊ ወደ ምሽቱ 1:00 ሰዓት፤ - ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ የነበረው የሰዎች እንቅስቃሴ የሰዓት…
#ATTENTION

ወልድያ !

የወልድያ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ም/ቤት ነባራዊ ሁኔታን ታሳቢ በማድረግ ተጨማሪ ክልክለዎችን አስተላለፈ።

የፀጥታ ምክር ቤቱ ከዚህ ቀደም የከተማውን ወቅታዊ ሁኔታ መነሻ በማድረግ  ክልከላዎችን ማስቀመጡ ይታወሳል።

ሆኖም ነባራዊ ሁኔታ በማየት ተጨማሪ ክልከላዎች በማስፈለጉ ከነገ መስከረም 22 / 2015 ዓ.ም ጀምሮ  የሚተገበሩ ተጨማሪ ዉሳኔዎችን ማሳለፉን ገልጿል።

በዚህ መሰረት :-

1. ከነገ መስከረም 22  ቀን ጀምሮ ጫት ወደ ከተማዋ ማስገባት በጥብቅ ተከልክሏል።

2. ከነገ ጀምሮ ጫት መቃም ሆነ ማስቃም በጥብቅ ተከልክሏል።

3. ከነገ ጀምሮ የጎዳና ላይ ቁማር (ቢንጎ የመሳሰሉትን) መጫወት ተከልክሏል።

ከላይ የተዘረዘሩትን ውሳኔዎች ጨምሮ ከዚህ በፊት የተላለፉ ዉሳኔዎችን ማንኛውም አካል የማክበርና ኃላፊነቱን የመወጣት ግዴታ አለበት የተባለ ሲሆን ውሳኔዎቹን የማያከበር ግለሰብም ሆነ ድርጅት ላይ የፀጥታ መዋቅሩ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል።

መረጃው ከከተማው ኮሚኒኬሽን የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ATTENTION

" ለሕዝቡ አስቸኳይ ዕርዳታ ካልደረሰለት አደጋው ከአሁኑ ሊብስ ይችላል "

በሶማሌ ክልል ዳዋ ዞን አስተዳደር ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መሐመድ ሀቢቻ ለሪፖርተር የሰጡት ቃል ፦

" ሕዝቡ የሚኖረው በከብቶቹ ላይ ተመሥርቶ ነው፡፡ ድርቁ እስከ መቼ እንደሚቀጥል አይታወቅም፡፡

ለሕዝቡ አስቸኳይ ዕርዳታ ካልደረሰለት አደጋው ከአሁኑ ሊብስ ይችላል።

የሞተውን የእንስሳት ሀብት ቁጥር ገና እየተጠና ነው፤ በሰዎች ላይ የደረሰውንም ጉዳት እየተገመገመ ነው።

ስለጉዳቱ የተጣራ አኃዝ ባይኖረንም በምግብ እጥረት ችግር ወደ ሆስፒታል የገቡ ሰዎች መረጃ አለን። "

NB. አምና በሶማሌ ክልል ካሉ 11 ዞኖች በአሥሩ ከባድ የድርቅ አደጋ ደርሶ #ከአንድ_ሚሊዮን ያላነሱ እንስሳትን ገድሏል። የዳዋ ዞን ገና ከዚህ አደጋ ያላገገመ ሲሆን ዘንድሮም ከባድ አደጋ ገጥሞታል።

Credit : #Reporter

@tikvahethiopia
#ATTENTION

በሶማሌ ክልል በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ ቀረበ።

በሶማሌ ክልል በተከሰተው ድርቅ ከ3 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ዜጎች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚፈልጉ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

ኮሚሽኑ ይህን ያሳወቀው ለፋና ብሮድካስት ኮርፖሬሽን በሰጠው ቃል ነው።

በሶማሌ ክልል ከሚገኙ 11 ዞኖች ውስጥ በዘጠኙ ላይ ድርቅ የተከሰተ ሲሆን ድርቁ በሰዎች እና እንስሳት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ብሏል ኮሚሽኑ።

አሁን ላይ ድርቁን ተከትሎ በሶማሌ ክልሉ አዲሱን ጥናት ሳይጨምር ከ3 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ዜጎች አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ተገልጿል።

በክልሉ እየተካሄደ ያለው አዲስ ጥናት ሲጠናቀቅ የተረጂዎች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ተመላክቷል።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም በክልሉ በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ያሳወቀው ኮሚሽኑ የተረጂዎች ቁጥር ከፍተኛ እና ከቀን ወደ ቀን እያሻቀበ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞም ተጨማሪ አስቸኳይ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥቷል።

ስለሆነም ፦
- መንግስታዊ ተቋማት፣
- የግል ድርጅቶች፣
- አጋር አካላት፣
- ታዋቂ ሰዎች እና ዳያስፖራዎች በክልሉ በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች ድጋፍ እንዲያደርጉ ኮሚሽኑ ለፋና ብሮድካስት ኮርፖሬሽን በሰጠው ቃል ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
#ATTENTION

" በድርቅ እና ለረጅም ጊዜ በተከሰተ የፀጥታ ችግር ሴቶች እና ህፃናትን ጨምሮ በርካት ሰዎች ለአደጋ ተጋልጠዋል " - የአማሮ ልዩ ወረዳ

• " ከምግብ እጥረት ጋር በተያያዘ ህፃናትን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ለረሀብ፣ ለበሽታ እና ለሞት እየተዳረጉ ነው " - የቡርጂ ልዩ ወረዳ

በደቡብ ክልል አማሮ እና ቡርጂ ልዩ ወረዳዎች በተከሰተ ድርቅ ምክንያት ከ136 ሺህ በላይ ሰዎች አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ተገልጿል።

#አማሮ

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የአማሮ ልዩ ወረዳን ዋቢ አድርጎ ባሰራጨው መረጃ ፤ በልዩ ወረዳው ለረጅም ጊዜ ዝናብ ባለመጣሉ በ22 ቀበሌዎች ድርቅ ተከስቷል፡፡

በተከሰተው ድርቅ ምክንያት በልዩ ወረዳው ከ96 ሺህ በላይ ሰዎች አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል።

በድርቁ ከ3 ሺህ 500 በላይ የቤት እንስሳት በድርቁ ምክንያት መሞታቸው ተገልጿል።

በልዩ ወረዳው የተከሰቱ የፀጥታ ችግሮች የህብረተሰቡን ተጋላጭነት እንዳባባሱት ልዩ ወረዳው አመልክቷል።

በድርቁ እና ለረጅም ጊዜ በተከሰተው የፀጥታ ችግር ምክንያት ሴቶች እና ህፃናትን ጨምሮ በርካት ሰዎች ለአደጋ መጋለጣቸው ተገልጿል።

የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በተለያየ ጊዜ እርዳታ ቢያደርግም በልዩ ወረዳው ከከተከሰተው ጉዳት አንፃር ድጋፉ በቂ አለመሆኑን ልዩ ወረዳው አሳውቋል።

#ቡርጂ

የቡርጂ ሶያማ ልዩ ወረዳ በበኩሉ በልዩ ወረዳው በተከሰተው ድርቅ 83 ሺህ 528 ዜጎች አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው አሳውቋል።

በልዩ ወረዳው ከ30 ሺህ በላይ እንስሳት መሞታቸውም ተጠቁሟል።

ከምግብ እጥረት ጋር በተያያዘ ህፃናትን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ለረሀብ፣ ለበሽታ እና ለሞት እየተዳረጉ መሆኑ ተገልጿል።

ከክልሉ መንግስት በተጫማሪ የአካባቢው ተወላጆች እና ግለሰቦች እርዳታ ቢያደርጉም በልዩ ወረዳው ከተከሰተው ድርቅ አንፃር የተጎዱ ዜጎችን ለመርዳት በቂ አለመሆኑ ተመላክቷል።

በድርቅ የተጎዱ ዜጎችን ለመርዳት እና መልሶ ለማቋቋም ረጂ ድርጅቶችን ጨምሮ የሚመለከታቸው አካላት ትኩረታቸውን ወደ ልዩ ወረዳው እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

#ኮንሶ

በኮንሶ ዞን በተከሰተ ድርቅ ከ800 ሺህ በላይ ዜጎች ለአስቸኳይ ድጋፍ መዳረጋቸውን ዞኑ አሳውቋል።

ለተከታታይ 5 ዓመት የተከሰተው የዝናብ መዘግየት እና እጥረት ባስከተለው ድርቅ ለአስቸኳይ ድጋፍ የተዳረጉት 822 ሺ 526 ዜጎቻችን ናቸው።
 
የተከሰተው ድርቅ ዜጎች ላይ አስከፊ ጉዳት ከማድረሱ በፊት በችግር ውስጥ ለሚገኙ ወገኖች ድጋፍ ሊደረግ ይገባል ተብሏል።

Credit : #FBC #SRTA

@tikvahethiopia
#ATTENTION

በአማራ ክልል ፤ የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን አስተዳደር ጥብቅ ክልከላዎች ተጣሉ።

የኦሮሞ ዞን ኮማንድ ፖስት ምን ክልከላዎችን ጣለ ?

- የሰአት እላፊ ገደብ (ባጃጅ 1:00፤ የሰው እንደ አካባቢና እንደ ሚፈጠር ችግር ይወሰን ፆም በመሆኑ ተብሏል) ።

- ስምሪት ከተሰጠው ሃይል ውጭ ጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ እንደማይቻል ተገልጿል።

- በማንኛውም ሆቴል መሳሪያ ይዞ መግባት የተከለከለ ሲሆን ፤ በሁሉም ሆቴሎች ፍተሻ እንዲጠናከር ታዟል።

- የፀጥታ ሃይሉን መጠርነፍና ለግዳጅ ዝግጁ ማድረግ ፖሊስና ሚሊሻ ፤ ከፌደራልና መከላከያ ጋር በቅንጅት መስራት አለባቸው ተብሏል።

- የኬላ ላይ ፍተሻ እንዲጠናከር ታዟል።

- የህዝብ ግንኙነት ስራ በተደጋጋሚ እንዲሰራ ታዟል ፤ በዋናነት በመስመር መዝጋት እየተጎዳ ያለው ህዝብ መሆኑ ተመላክቷል።

- ህብረተሰቡ በቀበሌ፣ በመንደር፣ በሰፈር፣ በኬላ፣ በተቋማት ጥበቃ ላይ ተደራጅቶ አካባቢውን የመጠበቅና ለሰላም ለሚከፈል ዋጋ ሃላፊነቱን እንዲወጣ ታዟል።

- የተሳሳተ መረጃ የሚነዙ፣ በአሉቧልታ ህዝብን የሚያሸብሩ፣ ወንጀለኞችን ለመንግስት አጋልጦ እንዲሰጥ ሁሉም በጥብቅ ተማምኖ መንቀሳቀስ አለበት ተብሏል።

- ፈጣን የመረጃ ልውውጥ እንዲደረግ ፤ በየደረጃው ያለው አመራርና ህዝቡ ከፀጥታ ማዋቅሩ ጋር መረጃ መለዋወጥ እንዳለበት ታዟል።

- የመንግስት ተቋማት፣ ባንኮችን ፣ የሀይማኖት ተቋማትን የጥበቃ ሁኔታን እንዲጠናከር ታዟል።

- የአካባቢውን ሁኔታና የዞኑን ክልከላ በማይጣረስ መንገድ ተጨማሪ ክለከላዎችን በወረዳና ከተማ አስተዳደር ኮ/ፖስት ማወጅ እንደሚቻል ተገልጿል።

መረጃው የኦሮሞ ዞን ኮማንድ ፖስት ነው።

@tikvahethiopia
#ATTENTION🔊

በዳሰነች ወረዳ የኦሞ ወንዝ በመሙላቱ / ከመደበኛ ፍሰቱ ወጥቶ ሞልቶ በመፍሰሱ ዜጎቻችን እየተጎዱ ነው።

እንደ ዳሰነች ወረዳ አስተዳደር መረጃ ፦

- በ34 ቀበሌያትና በ7 ደሴቶች የሚኖሩ 79,828 ቤተሰብ አባላት በወንዙ ሙላት የተጎዱ ተጎድተዋል።

- በወረዳው ካሉ 40 ቀበሌያቶች 34ቱ ቀበሌያት  በውሃ የመዋጥና የመከበብ አደጋ ያጋጠማቸው ሲሆን ከዚህ ውስጥ 27ቱ ቀበሌያት ሙሉ በሙሉ በውሃ ሙላት ተውጠዋል ፤ 7ቱ ቀበሌያት ደግሞ በቀጣይ ስጋት ውስጥ ናቸው።

- በኦሞ ወንዝ ሙላት ሳቢያ 1,435.75 ሄ/ር በመስኖ የተዘራ ሰብልና 123,000 ሄ/ር የእንስሳት የግጦሽ መሬት ሙሉ በሙሉ በውሃ ተሸፍኗል።

- በደሴቶች ውስጥ የነበሩና በውሃ ሙላት የተከበቡ እንስሳት ብዛት 2,993,135 ሲሆን ከዚህ ውስጥ አስካሁን ከውኃ ሙላት የወጡ 889,454 እንስሶች ናቸው።

- በውሃ መጥለቅለቁ 8 የሰው ጤና ኬላዎች፣ 1 ጤና ጣቢያ፣ 6 ትምህርት ቤቶች፣ 6 የእንስሳት ጤና ኬላ፣ 5 የአርብቶ አደር ማሰልጠኛ ጣቢያ ፣ 4 የመኖ ቤል እስቶር እና በ14 ቀበሌያት በስራ እድል ፈጠራ በማህበራት ተደራጅተው ከተለያዩ አበዳሪ ተቋማት ተበድረው ወደ ስራ የገቡ እና በፕሮጀክት የታቀፉ 32 ማህበራትና 15 ሼዶች ሙሉ ለሙሉ በውሃ ሙላት ተውጠዋል፤ ስራም አቁመዋል።

በአደጋው ለተጎዱ ወገኖች ሁሉም ባለድርሻ አካላት በመተባበርና በመቀናጀት አፋጣኝ ምላሽ ሊሰጡ እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።

@tikvahethiopia
#Attention

የማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድ ፖስት ፤ ከዛሬ ጀምሮ የትኛውም አይነት የትራንስፖርት አገልግሎት ከደሴ - ሸዋሮቢት_ ደ/ብረሀን እንዲሁም ከደ/ብረሀን -ሸዋሮቢት - ደሴ እንዲቆም ውሳኔ መተላለፉን አሳውቋል።

የትራንስፖርት እንቅስቃሴው እንዲቆመ የተደረገው ኮማንድ ፖስቱ " ፅንፈኛ " ባላቸው ታጣቂዎች ላይ ኦፕሬሽን በመጀመሩና ቀጠናውን ነፃ ለማድረግ እርምጃ መውሰድ በመጀመሩ እንደሆነ ተገልጿል።

በመሆኑም በቀጠናው የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲቆም የተወሰነው ሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ መሆኑን ያሳወቀው ኮማንድ ፖስቱ ውሳኔው ለጊዜው ነው ብሏል።

ህብረተሰቡ ከዛሬ ጀምሮ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ #እንዲቆም የተወሰነ መሆኑ እንዲያውቅና አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ፤ የፀጥታ ሀይሉም ውሳኔው እንዲፈፀም ክትትል እንዲያደርግ ትዕዛዝ መሰጡቱ ታውቋል።

@tikvahethiopia