TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Sport

ተጋጣሚውን 9 ለ 0 ያሸነፈው የኢትዮጵያ ክለብ !

ከደቂቃዎች በፊት በተጠናቀቀው በ #CECAFA ሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ የኢትዮጵያው ንግድ ባንክ ቡድን ተጋጣሚውን ዋሪየርስ ኩዊን በሰፊ የግብ ልዩነት 9 ለ 0 አሸንፏል።

መዲና አዎል 4 ግቦችን እንዲሁም ሎዛ አበራ 5 ግቦችን ማስቆጠር ችለዋል ።

More : @tikvahethsport
TIKVAH-ETHIOPIA
#Sport ተጋጣሚውን 9 ለ 0 ያሸነፈው የኢትዮጵያ ክለብ ! ከደቂቃዎች በፊት በተጠናቀቀው በ #CECAFA ሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ የኢትዮጵያው ንግድ ባንክ ቡድን ተጋጣሚውን ዋሪየርስ ኩዊን በሰፊ የግብ ልዩነት 9 ለ 0 አሸንፏል። መዲና አዎል 4 ግቦችን እንዲሁም ሎዛ አበራ 5 ግቦችን ማስቆጠር ችለዋል ። More : @tikvahethsport
#TikvahSport | በተጋጣሚዎቻቸው ላይ የጎል ናዳ ያወረዱት 2ቱ ኢትዮጵያውያን !

በታንዛንያ ሀገር ፤ ዳሬሰላም ከተማ የ #CECAFA የሴቶች ሻሚዮንስ ሊግ ውድድር እየተካሄደ ይገኛል።

በዚሁ ውድድር ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ክለብ በመሳተፍ ላይ ሲሆን የዚሁ ክለብ ተጫዋቾች የሆኑት ሎዛ አበራ እና መዲና አዎል በታጋጣሚ ቡድኖች ላይ የጎል ናዳ አውርደውባቸዋል።

እስከሁን ባለው ከ3 ክለቦች ጋር በተደረገ ጨዋታ ሎዛ አበራ 9 ጎሎችን እንዲሁም መዲና አዎል 6 ጎሎችን አስቆጥረዋል።

የጎል ናዳው የወረደው በየትኞቹ ክለቦች ላይ ነው ?

👉 ዋሪየርስ ኩዊን በተባለው የእግር ኳስ ክለብ ላይ ሎዛ ብቻዋን 5 ጎል ፤ መዲና 4 ጎል አስቆጥረውባቸዋል።

👉 ፎፊላ በተባለው የእግር ኳስ ክለብ ላይ ደግሞ ሎዛ 3 ጎሎችን መዲና 1 ጎል አስቆጥረዋል።

👉 ኤፒ አር ኪጋሊ በሚባለው ክለብ ላይ ሎዛም መዲናም አንድ አንድ ጎል አስቆጥረዋል (ይሄ ጨዋታ ዛሬ የተካሄደ ነው)

በድምሩ ሁለቱ ተጫዋቾች ብቻ በውድድሩ 15 ጎሎችን አስቆጥረዋል።

ቲክቫህ ስፖርት👇
https://t.me/+VvwzStMNcNHmhK0x

@tikvahethsport