TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
" ውሳኔውን ማሳለፍ ከባድ ነበር " - ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣው ሙሉ በሙሉ ውድቅ እንዲደረግ የተላለፈው ውሳኔ ከባድ እንደነበር ነገር ግን ውሳኔው ባይተላለፍ ተጎጂ የሚሆነው ህዝብ እጅግ ከፍተኛ እንደነበር የአዲስ አበባ ከንቲባ ገለፁ። ይህ የገለፁ ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ጋር በነበራቸው ቆይታ ነው። ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፤ በቤቶች ዕጣ አወጣጥ ላይ የተፈፀመው ማጭበርበር እኛንም…
#Update

በቅርቡ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ እንደሚወጣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አሳውቁ።

ከንቲባዋ ትክክለኛ ቀኑን አስረግጠው ባይናገሩም የጋራ ቤቶች እጣ ባጠረ ጊዜ ውስጥ እንደሚወጣ ገልፀዋል።

ይህን የገለፁት ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ጋር በነበራቸው ቆይታ ወቅት ነው።

ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ፤ " የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ዕጣ በቅርብ ለማውጣት ተመልሰን ሶፍትዌሩ መረጋገጥ አለበት ፤ #ሌላ_ሶፍትዌር ነው የምንጠቀመው ትንሽ መታገስ ያስፈልጋል።

ቤቱን የሚጠባበቀው ህዝባችን ለጥራት ቅድሚያ ይስጥ፤ በጥራት ለመስራት ሰው የሚችለውን ሁሉ ጥረት እናደርጋለን። ጥንቃቄም እናደርጋለን። በሚመለከታቸው ተቋማት ሁሉ ማረጋገጫ እንዲሰጥበት የተለያየ አደረጃጀቶችን ፈጥረንላቸዋል ተቋማት ድርሻ ድርሻ እንዲኖራቸው።

የኢንዱስትሪ ስታንዳርድ አመራሩንም ጭምር በዚህ አጋጣሚ በደንብ ስላወቅነው እሱንም ጭምር የማስጠበቅ ሂደት እንከተላለን ነገር ግን አንዘገይም።

በጣም ለመፍጠን ብለን ስህተት ውስጥ አንገባም ፤ አዲስ ሶፍትዌር ነው በሚል በጣም complicated ነገር አድርገን ሰው የማይችለው ነገር አስመስለን ማዘግየትም አንፈልግም " ብለዋል።

አክለውም " በእርግጠኝነት የሰዎች አለመታመን ነው ይሄን ያመጣው (ባለፈው የተጭበረበረውን የቤት ዕጣ አወጣጥ ማለታቸውን ነው) ሶፍትዌሩን በትክክል አልምተውታል ካለሙ በኃላ ግን ለሚፈልጉት ነገር እንደሚጠቅም አድርገው አዘጋጅተውታል ፤ ሰዎች ያጠፉት ጥፋት ነው ይሄን ህግ በማስከበት ሂደታችን 16 የሚደርሱ ሰራተኞቻችን በህግ ቁጥጥር ስር ነው ያሉት ፍርድ ቤትም ቀርበዋል ፤ ሂደቱን ከስር ከስር የፌዴራል ፖሊስ ይዞታል እራሱ መግለጫ እየሰጠበት ይሄዳል። ሌላም መረጃ የሚመለከተው ሰው ካለም ይቀጥላል " ሲሉ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በቅርቡ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ እንደሚወጣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አሳውቁ። ከንቲባዋ ትክክለኛ ቀኑን አስረግጠው ባይናገሩም የጋራ ቤቶች እጣ ባጠረ ጊዜ ውስጥ እንደሚወጣ ገልፀዋል። ይህን የገለፁት ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ጋር በነበራቸው ቆይታ ወቅት ነው። ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ፤ " የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ዕጣ በቅርብ ለማውጣት ተመልሰን ሶፍትዌሩ መረጋገጥ አለበት ፤…
የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ መቼ ነው የሚወጣው ?

ከሳምንታት በፊት " በቅርቡ ዕጣው እንደገና ይወጣል " የተባለው የተሰረዘው  የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ የሚወጣበት እካሁን አልታወቀም።

በአዲስ አበባ ከተማ ፤ ሐምሌ 1 ወጥቶ ውድቅ የተደረገው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ በቅርቡ ይወጣል ከተባለ ሳምንታት ያለፉ ሲሆን የቤቶቹ ዕጣ መቼ እንደሚወጣ አልታወቀም።

ዕጣውን የሚጠባበቁ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ከተማ አስተዳደሩ በገባው ቃል መሰረት በፍጥነት ፤ ታማኝነት እና ግልፅነት ባለው መልኩ ዕጣውን በድጋሚ እንዲያወጣ / የሚወጣበትን ቀን እንዲሳውቅ ጠይቀዋል።

የአዲስ አበባ ከንቲባ ምንም እንኳን ትክክለኛውን ቀን አስረግጠው ባይናገሩም " የተሰረዘውን የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ በቅርብ ለማውጣት እየተሰራ ነው ሲሉ ከገለፁ ወደ አንድ ወር እየተጠጋ ይገኛል።

ከንቲባዋ ሀምሌ 15 ቀን 2014 ላይ በኤፍ ኤም አዲስ በቀረቡበት ወቅት የጋራ ቤቶች እጣ ባጠረ ጊዜ ውስጥ እንደሚወጣ እና #ሌላ_ሶፍትዌር ጥቅም ላይ እንደሚውል ገልፀው ነበር።

ይህንን ካሉ ሳምንታት ያለፉ ቢሆንም እስካሁን የቤቶቹን ዕጣ በተመለከተ አዲስ ነገር የለም/ያለውን/የደረሰበትን ሂደት የሚገልፅ መረጃ ይፋ አልሆነም።

ከንቲባዋ ሬድዮ ላይ በቀረቡበት ሰሞን አንድንድ ሚዲያዎች " ዕጣው በሁለት ሳምንት ይወጣል ብለዋል " ሲሉ አሰራጭተው የነበረው መረጃም ትክክል ያልሆነ ነው። በወቅቱ ከንቲባዋ ቀን ሆነ በዚህ ሳምንት ብለው አልተናገሩም ነበር።

በሌላ በኩል ፤ የ2005 የ20/80 የባለ ሶስት መኝታ ቆጣቢዎች ከዚህ ቀደም ላቀረቡት ጥያቄ እስካሁን ድረስ አጥጋቢ ምላሽ የሚሰጣቸውን ባለማግኘታቸው ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ግፊት እያደረጉ ሲሆን በቀጣዩ ዕጣ እነሱም ሊካተቱ እንደሚገባ እየገለፁ ናቸው።

@tikvahethiopia