TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሲቪል አቪዬሽን ሕግና አሠራር ጥሰዋል በማለት በቁጥጥር ስር አውሎ የሽብር ወንጀል ምርመራ የከፈተባቸውን 6 ተጠርጣሪ ግለሰቦችን ማንነት የሚያሳይ ፎቶ ይፋ አድርጓል። ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ያዋልኳቸው በሀገራችን ካለው የክረምት ወቅት ጋር ተያይዞ በተፈጠረው የአየር መዛባት ምክንያት " ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ አውሮፕላን…
#Update

የአቪዬሽን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግርና ወከባ ፈጥረዋል የተባሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ በእነ ዮሐንስ ዳንኤል ላይ በጠየቀው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ላይ የግራቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ብይን ለመስጠት ለነገ ነሐሴ 21ቀን 2016 ዓ.ም ቀጠሮ ይዟል።

ተጠርጣሪዎቹ በጠበቆቻቸው በኩል የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል። #ኢብኮ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአቪዬሽን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግርና ወከባ ፈጥረዋል የተባሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ በእነ ዮሐንስ ዳንኤል ላይ በጠየቀው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ላይ የግራቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ብይን ለመስጠት ለነገ ነሐሴ 21ቀን 2016 ዓ.ም ቀጠሮ ይዟል። ተጠርጣሪዎቹ በጠበቆቻቸው በኩል የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው…
#Update

የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግር እና ወከባ ፈጥረዋል ተብለው በቁጥጥር ስር የዋሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀን የግዜ ቀጠሮ ፈቅዷል።

ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው በጠበቆቻቸው አማካኝነት ጠይቀዋል።

ፍርድ ቤቱ ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል።

የፖሊስን የምርመራ ውጤት ለመጠባበቅ ለጳጉሜ 4 ቀን 2016 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray አሜሪካ በህወሓት እና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር መካከል ያለው ውጥረት እንዲረግብ ጠየቀች። ትላንት ትግራይ ፣ መቐለ የገቡት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር ተወያይተዋል። በዚህም ወቅት በህወሓትና በጊዚያዊ አስተዳደሩ መካከል የተፈጠረው ውጥረት መርገብ እንዳለበት አሳስበዋል።  አምባሳደሩ ውጥረቱ እንዲረግብ ከሰጡት…
#Update
 
የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ከሚመራው የህወሓት ቡድን ጋር መወያየታቸው ተሰምቷል።

በህወሓት የማህበራዊ  የትሰስር ገፅ የተሰራጨው መረጃ እንዳለው ፤ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ዛሬ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አፈፃፀም ዙሪያና በክልሉ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ከድርጅቱ ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር (ማለትም በቅርቡ በተካሄደው ጉባኤ ከተመረጡት አቶ አማኑኤል አሰፋ) እና ሌሎች አመራሮች ጋር ተወያይቷል። 

አምባሳደሩ በውይይቱ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ እንዲፈፀም አገራቸው አሜሪካ እንደምትደግፍ ተናግረዋል።

አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ትላንት " በህወሓት እና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር መካከል ያለው ውጥረት እንዲረግብ " በማስመልከት ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር መወያየታቸውን መዘገባችን ይታወቃል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሪልስቴት #አዲስአበባ ° “ ብራችንን እኔ አውጥተን ተሰቃየን ” - የኖህ ሪልስቴት ቤት ገዥዎች ° “ የመብራት፣ የውሃ፣ የውሃ ታንከር ጥያቄ አለ ትክክል ነው ” - ኖህ ሪልስቴት በአዲስ አበባ ከተማ ፤ በኖህ ሪልስቴት ' የኖህ አያት ግሪን ፖርክ ቤት ' ገዢዎች ኖህ የገባውን ውል በመዘንጋት የቤት መሠረተ ልማቶችን እያሟላ እንዳልሆነ እና በጠበቃቸው በኩል ምላሽ እንዲሰጣቸው ቢጠይቁም መፍትሄ እንዳላገኙ…
#ሪልስቴት #Update

" ቤት ገብተው የሚኖሩ ሰዎች አሉ በጣም ነው የሚያሳዝኑት መብራትና ውሃ ስለሌለ እንጀራ ጋግረው አያውቁም እሱን እያየን ለመግባት ተቸግረል " - የኖህ ሪልስቴት ቤት ገዢዎች

"...ለፕሬስ መግለጫ አልሰጥም  " - ኖህ ሪልስቴት

የኖህ ሪልስቴት ሀያት ግሪን ቤት ገዢዎች ድርጅቱ በውሉ መሠረት የቤቱን መሠረተ ልማት እንዳላሟላላቸው በድጋሚ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ቅሬታ አቀረቡ፡፡

ቅሬታቸውን ያቀረቡ በርካታ ገዢዎች፣ ድርጅቱ በገባው ውል መሠረት መብራት፣ ውሃ፣ ጀነሬተር መሠረተ ልማቶች ባለሟሟላቱ ችግር ላይ እንደወደቁ ገልጸዋል።

መሠረተ ልማቱ ሳይጠናቀቅ የቤት ኪራይ ሽሽት ቤታቸው የገቡ ገዢዎች ያለ መሠረተ ልማት ከ1 ዓመት በላይ እንተቀመጡ በምሬት ተናግረዋል፡፡

መሠረተ ልማቱ እስከሚጠናቀቅ በኪራይ ቤት ሆነው እየጠበቁ ያሉ ገዢዎችም፣ ቤቱን ለመግዛት እስከ 4 ሚሊዮን ብር አውጥተው ሳለ መሠረተ ልማቱ ባለመጠናቀቁ አሁንም በቤት ኪራይ ወጪ እየተበዘበዙ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ወደ ቤታቸው ያልገቡበትን ምክንያት ሲያስረዱም፣ " ቤት ገብተው የሚኖሩ ሰዎች አሉ በጣም ነው የሚያሳዝኑት መብራትና ውሃ ስለሌለ እንጀራ ጋግረው አያውቁም እሱን እያየን ለመግባት ተቸግረል " ነው ያሉት።

ከዚህ ቀደም መሠረተ ልማቱን በወር ከ15 ቀን ውስጥ እንደሚያጠናቅቅ በሚዲያ በኩል ቃል ገብቶላቸው እንደነበር አስታውሰው፣ ግን ምንም ሳይሰራ ወራቶች እንደጠቆጠሩ ተናግረዋል።

ውሃው ግቢ ውስጥ ገብቷል ከተባለ ብዙ ጊዜ እንዳስቆጠረ፣ ነገር ግን አገልግሎት ላይ እንዳልዋለ፣ በዚህም የከፋ ችግር ለማሳለፍ እንደተገደዱ ነው የገለጹት፡፡

ድርጅቱ ይባስ ብሎ ቤቱ ሳያጠናቅቅ ጥበቃዎችን እያስወጣ መሆኑን፣ የከተማዋ ከንቲባ ሳይቱን የመረቁት ሳይጠናቀቅ መሆኑንም ተናግረዋል።

ላደረባቸው ቅሬታ ምላሽ ቢሮ ድረስ ሂደው ቢጠይቁም አጥጋቢ ምላሽ እንዳልተሰጣቸው አስረድተው፣ አሁንም መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅናቸው የኖህ የህግ አማካሪና ጠበቃ አቶ የሴፍ ደስታ፣ አጭር የመከላከያ ሀሳብ ከመስጠት ውጪ በቀጥታ ለቅሬታው ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

" በጠበቃቸው አማካኝነት እየተከታተሉ ስለሆነና ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት የመሄድ ዕድል ስላለው የድርጅቱን የመከራከር መብት የሚያጣብብ ስለሚሆን ለፕሬስ መግለጫ አልሰጥም " ነው ያሉት።

ድርጅቱ ከዚህ ቀደም ስለቅሬታው ጠይቀነው በሰጠን ምላሽ፣ " ትክክል ነው የመብራት፣ የውሃ፣ ታንከር ጥያቄ አለ " ብሎ ይህ የገጠመው በተለያዩ ችግሮች እንደሆነ ገልጾ ነበር።

በወቅቱ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤቱን መቼ አጠናቃችሁ ታስረክቧቸዋላችሁ? ስንል ጠይቀናቸው በሰጡት ምሌሽ፣ " ነገ ቢሆን ደስ ይለኛል፡፡ 654 ቤቶችን ሰርተን መብራት ለማስገባት የምንዘገይበት ምክንያት እኔ ራሱ አልገባኝም " ነበር ያሉት።

" ስለዚህ በጣም በጣም ባጠረ ጊዜ ውስጥ ለመስራት እየሞከርን ነው " ማለታቸው ይታወሳል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#ትኩረት🚨

ዛሬም ድረስ የሰው ህይወት የሚቀጠፍባቸው የመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች ነዋሪዎች " በፈጣሪ ስም መፍትሄ ይፈለግልን ፤ ተሰቃየን ህይወታችን በሰቀቀን መግፋት ደከመን " ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጥሪ አቅርበዋል።

" ተደጋጋሚ እርቅ ይፈጸማል ግን ሳይቆይ ያገረሽና ደም ይፈሳል፣ ሰው ይገደላል የምንገባበት አጣን ድምጻችን ይሰማ " ብለዋል።

ከሰሞኑን በመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች የ9 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎ የአካባቢዉ ባለስልጣናት መታሰራቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።

ባለፉት ጊዜያት የነበረዉ የንጹሀን ግድያ  ለተወሰነ ጊዜ ረገብ ቢልም ከሰሞኑ እንደገና ባገረሸ ግጭት የ9 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 4 ሰዎች ደግም ቆስለዋል።

ይህን ተከትሎ አካባቢዉ ውጥረት ዉስጥ በመግባቱ አሁን ላይ በአካባቢዉ የሚኖሩ ንጹሀን በፍርሀት ውስጥ ናቸው።

" ኢንሴኖ ከተማና አካባቢው በየጊዜው በሚነሳው ግጭት ገጠራማው ቀበሌ የሚኖረው ምስኪን ግድያ ሲፈጸምበት ቆይቷል " የሚሉት ነዋሪዎቹ " በአካባቢው ሲስተዋል የነበረዉ የበቀል መጠፋፋት አሁንም በከፋ ሁኔታ ተመልሶ ይመጣል በሚል ተጨንቀናል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከሰሞኑ በማረቆ ልዩ ወረዳ በሌሊት በተፈጸመ ጥቃት የ7 ሰዎች ህይወት (4ቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት) እንዲሁም በመስቃን ደግሞ 2 ሰዎች ህይወታቸው መቀጠፉን የሚናገሩት ነዋሪዎቹ ሁኔታውን የመንግስት አካላት ቶሎ ካልተቆጣጠሩት ግጭቱ ከፍ ሊል ይችላል ሲሉ ፍርሀታቸውን አስረድተዋል።

ስለሁኔታዉ የጠየቅናቸዉ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ ኃላፊዉ አቶ ተካልኝ ንጉሴ ስለሁኔታው መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ይሁንና በልዩ ወረዳዎቹ ግድያ መፈጸሙን ተከትሎ አካባቢውን ለማረጋጋት ወደቦታው ያቀናው የጸጥታ ኃይል ጥቂት የአካባቢው ግለሰቦችን ጨምሮ ግጭት በተፈጠረባቸዉ አካባቢዎች ለጊዜዉ ስማቸዉ አይጠቀስ የተባሉ የወረዳ ከፍተኛ ባለስልጣናትን በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን ለማወቅ ተችሏል።

አሁን ላይ ኢንሴኖን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች የፌደራልና የክልል የጸጥታ አካላት ተሰማርተው ህዝቡን እያረጋጉ ሲሆን የህዝቡ እንቅስቃሴ ግን በጅጉ መቀዛቀዝ ይስተዋልበታል።

ይህ አካባቢ በተደጋጋሚ የሰዎች ህይወት የሚቀጠፍበት ፣ ዜጎች የሚፈናቀሉበት ሲሆን ዘላቂና አስተማማኝ መፍትሄ ሳይገኘ ዛሬም በዛው ቀጥሏል።

#Update : ከመሸ ስልክ ያነሱልን የምስራቅ ጉራጌ ወንጀል መከላከል ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር መሀመድ ሀሰን " አሁን ላይ ሁሉም አካባቢ ሰላም " መሆኑን ጠቅሰው ስለሁኔታው አሁን ላይ መረጃ መስጠት ከባድ መሆኑን ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" በረራውን ለማቋረጥ የተገደድኩት ገንዘብ እንዳላንቀሳቅስ በመታገዴ ነው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ

የኤርትራ ሲቪል አቬሽን ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ የሚያደርገው በረራ ከመስከረም 20፣ 2016 ዓ.ም ጀምሮ እንዲቆም የሚያሳውቅ ደብዳቤ ጽፎ እንደነበር ይታወሳል።

ዛሬ አየር መንገዱ በሰጠው መግለጫ ውሳኔው ይሻሻላል በሚል ሲጠብቅ እንደነበር እና የኤርትራ የሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣንን ለማናገር በተደጋጋሚ ያደረገው ሙከራ አለማሳካቱን አስታውቋል።

የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በመግለጫው እንደጠቀሱት በአስመራ የሚገኘው ተወካያቸው ከሽያጭ የተሰበሰበ ገንዘብ ለማስገባት ሲል ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ መላክ እንደማይቻል ተነግሮታል። ይህ የሆነው ሐምሌ 18/2016 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ አማካኝነት ነው።

" ' ከነሐሴ 25/ 2016 ዓ.ም በኋላ ሂሳባችሁ ታግዷል ለሀገር ውስጥ ወጪም (oppration fee) መጠቀም አትችሉም ' መባሉን ተከትሎ ከዛሬ ጀምሮ በረራውን ለማቋረጥ ተገደናል። የበረራ ወጪያችንን መሸፈን ባለመቻላችን ተገደን ወጥተናል " ሲሉ ነው የገለጹት።

አየር መንገዱ እንዳያንቀሳቅስ የታገደበት ገንዘብ መጠን ስንት ነው ?

ይህ ጥያቄ ከጋዜጠኞች የቀረበላቸው ዋና ሥራ አስፈጻሚው የገንዘቡን መጠን ከመግለጽ ተቆጥበው ማብራሪያ ሰጥተዋል።

አየር መንገዱ በኤርትራ ሁለት አካውንት እንዳለው የገለጹት አቶ መስፍን፥ አንዱ የናቅፋ አካውንት ሲሆን የቆየ እንዲሁም ወደ ዶላር መቀየር ያልተቻለ የማይንቀሳቀስ የሂሳብ አካውንት መሆኑን ገልጸዋል።

ሌላኛው የባንክ አካውንት ደግሞ የዶላር ሲሆን ባለፉት ጥቂት ዓመታት ትኬት ሲሸጥ የነበረው በውጭ ምንዛሬ መሆኑን ገልጸው ይህንን ገንዘብም እገዳው እስከተላለፈበት ቀን ድረስ በተለያዩ ጊዜዎች ገንዘቡን ሲያንቀሳቅስ እንደነበረ ገልጸዋል።

" የበረራ እገዳውን ካወጡብን በኋላ ነው Block ያደረጉብን " ሲሉ ነው የገለጹት።

አቶ መስፍን አክለውም ፥ "ለእኛ ገንዘቡ ካልተለቀቀልን ከዚህ በኋላ የሁለቱ ሀገራት ጉዳይ ነው የሚሆነው " ሲሉ ጉዳዩን ለኢትዮጵያ ለሲቪል አቬሽን ባለሥልጣን እና ለውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ማስታወቃቸውን ገልጸዋል።

" አየር መንገዱ ከኤርትራ የወጣው ተገዶ ነው " ያሉት አቶ መስፍን ዋናው ችግሩ ለምን እንደታገድን አለማወቃችን ነው፤ በተጻፈው ደብዳቤም ላይ ምንም የተገለጸ ነገር የለም ብለዋል።

" ከዚህም በተጨማሪ በደብዳቤም በስልክም ለማናገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም " ሲሉ ገልጸዋል።

የአየር ቀጠናውን አስመልክቶ ጥያቄ የቀረበላቸው ዋና ሥራ አስፈጻሚው አሁን ባለው ሁኔታ በኤርትራ የአየር ክልል መብረር እንዳልተከለከሉ ገልጸው የሚያስገድድ ጉዳይ ካለ ግን አማራጭ መጠቀም እንደሚችሉ አንስተዋል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#UPDATE

በኤሌክትሪክ አገልግሎት ታሪፍ ላይ የተደረገው ማስተካከያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሰኔ 13/2016 ዓ.ም መጽደቁ ይታወሳል።

ይህ ተከትሎ  የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አግልግሎት የታሪፍ ማሻሻያው ከመስከረም 1/2017 ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ሽፈራው ተሊላ የታሪፍ ጭማሪው የደንበኞችን የኃይል የአጠቃቀም መሰረት ያደረገ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም፦

የቤት ደንበኞች፤ የንግድ ተቋማት፤ ዝቅተኛ ኢንዱስትሪ፤ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ እንዲሁም የመንገድ መብራት ተጠቃሚዎች በሚል መከፋፈሉን አስታውቀዋል።

የቤት መብራት ተጠቃሚዎችን በተመለከተ " እንደ አጠቃቀማቸው አሁን ከሚከፍሉት እና ጭማሪ ከተደረገበት መካከል ያለውን ልዩነት ሲከፍሉ እንደ አጠቃቀማቸው ድጎማ ተደርጓል " ሲሉ አስረድተዋል።

ድጎማው ምን ይመስላል ?

50kW በታች ለሚጠቀሙ ደንበኞች ያለውን ልዩነት 75 በመቶ የሚሆነውን ይደጎማሉ፤

ከ50kW - 100KW ለሚጠቀሙ ደንበኞች ያለውን ልዩነት 40 በመቶ የሚሆነውን ይደጎማሉ፤

200kW - 300 Kw ለሚጠቀሙ ደንበኞች ያለውን ልዩነት 4 በመቶ የሚሆነውን ይደጎማሉ፤

400kW - 500 KW የሚሆነውን ማሻሻያውን ያለምንም ድጎማ ይከፍላሉ

ከ500kW በላይ የሚሆነውን ደግሞ ሌላውን ተጠቃሚ የሚደግፉበት የጎንዮሽ ድጎማ ሥርዓት ተግባራዊ ይደረጋል።

የአከፋፈሉ ሁኔታ ምን ይመስላል ?

እንደ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ ይህ የተደረገው የታሪፍ ማሻሻያው (የተጨመረው 6 ብር) የሚከፈለው በአንድ ጊዜ ሳይሆን በ16 ዙር በሚደረግ የሂሳብ ማስተካከያ [ከመስከረም 1 /2017 ጀምሮ] በአራት ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደሆነ ገልጸዋል።

ኢንጂነር ሽፈራው ይሄንን ሲያስረዱ 50KW የሚጠቀሙ ደንበኞች አሁን የሚከፍሉት 27 ሳንቲም እንደሆነ ገልጸው ከመስከረም ጀምሮ የሚከፍሉት 35 ሳንቲም ይሆናል ብለዋል።

ከአራት ዓመታት በኋላ ደግሞ [በ16 ዙሮች በሚደረግ ማስተካከያ] 1.56 ብር መክፈል ይጀምራሉ ሲሉ አስረድተዋል።

ከኑሮ ውድነት ጋር ተያይዞ ያለው ጫና ተጠንቷል ወይ ?

ይህ ጥያቄ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከጋዜጠኞች የቀረበላቸው ሲሆን በሰጡት ምላሽ በዚህ ላይ ጥናት መደረጉን ጠቅሰው ይህም #ከአራት_ዓመት በኋላ የሚኖረው ተጽዕኖ 2 በመቶ እንደሆነ አንስተዋል።

" ከአከራይ ተከራይ ጋር ያለው ተጽዕኖም በጣም አነስተኛ ነው፤ የሚያጣላቸው ነገር አይኖርም " ሲሉ አስረድተዋል።

ዋና ሥራ አስፈጻሚው አክለው ይህ የታሪፍ ማሻሻያው በዋነኛነት የወጣበትን ወጪ ለመሸፈን (A cost reflective tariff) መሰረት ያደረገ መሆኑን አንስተዋል።

#ማብራሪያ: ከላይ የተያያዘው ሰንጠረዥ ድጎማ የተደረገበት የሂሳብ ታሪፍ ሲሆን። በዓመት 4 ጊዜ በ4 ዓመት ደግሞ 16 ጊዜ የሚተገበር የሂሳብ ማስተካከያ የያዘ ነው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray አቶ ጌታቸው ረዳ የጤና አክል ገጥሟቸዋል። ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት ዛሬ ጳጉሜን 2/2016 ዓ.ም የወጣ መግለጫ እንዳመለከተው ፥ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ባጋጠማቸው የጤና እክል ምክንያት ዛሬ በአክሱም ሊካሄድ የታቀደው ህዝባዊ ውይይት ተሰርዟል። ፅ/ቤቱ ፕሬዜዳንቱ ባጋጠማቸው የጤና እክል ምክንያት ከአክሱም ከተማና አከባቢዋ ነዋሪዎች ጋር ሊካሄድ እቅድ የተያዘለት…
#UPDATE

" የጤናዬ ሁኔታ ብዙ የሚያሳስብ አይደለም " - አቶ ጌታቸው ረዳ 

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ ጳጉሜን 2/2016 ዓ.ም በ X ገፃቸው ባሰፈሩት ፅሑፍ የአዲስ ዓመት መልካም ምኞት በማስቀደም " የጤንነት ሁኔታየና ድህንነቴ ያሳሰባችሁና ያስጨነቃችሁ ሁላችሁም ደህና ነኝ " ብለዋል። 

" ተደጋጋሚ ረጅም መንገድ በመኪና መጓዝና ደካም ተደራርቦ የፈጠረው ጊዚያዊ ችግር እንጂ በሚያሳስብ ሁኔታ እንዳልሆንኩ በፈጣሪና በፅዮን ማርያም ስም እገልፅላችኃለሁ " ሲሉ ፅፈዋል።   

ቀጣይ ህዝባዊ መድረኮች ከተወሰኑ ቀናት በኋላ እንደሚቀጥሉ የገለፁት አቶ ጌታቸው " በመድረኩ ለመሳተፍ አክሱም ድረስ ለተንገላቱ ተሳታፊዎች ደግሜ ይቅርታ እጠይቃለሁ " በማለት አክለዋል።   

ዛሬ ጳጉሜን 2/2016 ዓ.ም ከጊዚያዊ  አስተዳደሩ የፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት የወጣ መግለጫ ፕሬዜዳንቱ የጤና እከለ እንደገጠማቸው በመግለፅ በአክሱም ከተማ ሊካሄድ እቅድ የተያዘለት ህዝባዊ ውይይት ለሌላ ጊዜ መተላለፉና ይቅርታ መጠየቁን መዘገባችን ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግር እና ወከባ ፈጥረዋል ተብለው በቁጥጥር ስር የዋሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀን የግዜ ቀጠሮ ፈቅዷል። ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው በጠበቆቻቸው አማካኝነት ጠይቀዋል። ፍርድ ቤቱ ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል። የፖሊስን የምርመራ…
#Update

ፍ/ቤት የክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቀደ።

" የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል ፤ የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግር እና ወከባ ፈጥረዋል " ተብለው የተጠረጠሩ 6 ግለሰቦች ላይ የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ክስ መመስረቻ ጊዜ መፍቀዱ ተሰማ።

የፌደራል መርማሪ ፖሊስ የምርመራ ቡድን፦
- ዮሃንስ ዳንኤል
- አማኑኤል መውጫ፣
- ናትናኤል ወንድወሰን፣
- ኤልያስ ድሪባ፣
- ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ በተባሉ ግለሰቦች ላይ ሲያከናውን የቆየውን የምርመራ ማጣሪያ ስራ አጠናቆ መዝገቡን ለዐቃቤ ሕግ ማስረከቡን አስታውቋል።

የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ህግ በችሎት ተሰይሞ የምርመራ መዝገቡን ከፖሊስ ጳጉሜን 1 ቀን 2016 ዓ.ም መረከቡን ጠቅሶ፤ ማስረጃ ተመልክቶ ክስ ለማቅረብ እንዲያስችለው ክስ ለመመስረቻ ጊዜ 5 ቀን እንዲሰጠው ጠይቋል።

የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች " ዐቃቤ ህግ ምርመራውን ሲመራ ቆይቶ እንደአዲስ መዝገቡን ተመልክቼ ክስ ለመመስረት፣ ለመወሰን እንዲያስችለኝ የክስ መመስረቻ ጊዜ ይሰጠኝ ማለቱ " ተገቢ አይደለም በማለት ተከራክረዋል።

ጠበቆቻቸው ደንበኞቻቸው ተጨማሪ ጊዜ በእስር ሊቆዩ እንደማይገባ ገልጸው፤ የዋስ መብታቸው እንዲከበር ጠይቀዋል።

የግራ ቀኝ ክርክሩን የመረመረው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ዐቃቤ ህግ ክስ የመመስረቻ ጊዜ መፍቀድ ስነ ስርዓታዊ መሆኑን በማመን የተጠርጣሪዎችን የዋስትና ጥያቄ በማለፍ ለዐቃቤ ህግ የ5 ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ መፍቀዱን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

በዚህም መስከረም 3 ቀን 2017 ዓ/ም ክስ ይመሰረታል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" እንደ ባሪያ ነው የምንታየው ፤ እባካችሁ ጭሁልን !! " - በማይናማር የሚገኙ ወጣቶች ማይናማር እና ታይላንድ ድንበር ላይ ከሚገኙ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የበየነ መረብ ማጭበርበር (Online Scam) ተግባራት ከሚፈጸምባቸው አንዳንድ ቦታዎች ቲክቫህ ኢትዮጵያ መልዕክቶችን በቴሌግራም እየተቀበለ ይገኛል። እነዚህ ቦታዎች ላይ በርካታ የሀገራችን ወጣቶች ያሉ ሲሆን " ታይላንድ እንልካችኋለን " በሚል…
#Update

° " ብዙ አካላቸው የጎደለ ሰዎች አሉ፡፡ አካል እስከ ማጉደል ድረስ ነው ቅጣቱ " - ኢትዮጵያዊያን በማይናማር

° " መረጃው ትክክል ነው፡፡ ዜጎች ችግር ላይ ናቸው ተቋሙም ኃላፊነት ወስዶ ለወገኖቻችን ለመድረስ ጥረት እያደረገ ነው " - ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር

በማይንማርን ጨምሮ በአካባቢው የሚገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን በከፋ ችግር ውስጥ እንደሆኑ ከወራት በፊት በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ድምጻቸውን አሰምተው እንደነበር ይታወሳል።

አሁንም ኢትዮጵያውያኑ የኢትዮጵያ መንግስት እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል።

መጀመሪያ ከአገር ሲወጡ የተዋዋሉት የሆቴል ቤት ሥራ አስኪያጅ፣ ሀኪም እና የመሳሰሉትን ሥራዎች ሊሰሩና ዳጎስ ያለ ክፍያ ሊፈጸምላቸው እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

ይሁን እንጅ ከዚያ ከደረሱ በኋላ ሽፍታ ወዳለበት የማይናማር ክልፍ እንደወሰዷቸው፣ ጭራሽ ደመወዝ እንደማይፈጽሙላቸው ፣ ከውላቸው ውጪ ዶላር ማጭበርበር እንደሚያሰሯቸው አስረድተዋል፡፡

የሌሎች አገር ዜጎች በአገራቸው መንግስት አማካኝነት እየተለቀቁ ቢሆንም ኢትዮጵያዊያኑ ግን የከፋ ስቃይ ውስጥ እንደሆኑ ገልጸው መንግስት እንዲደርስላቸው በአንክሮ ጠይቀዋል፡፡

ቤተሰቦቻቸው በበኩላቸው፣ መንግስት የልጆቻቸውን ሕይወት እንዲያተርፍላቸው ተማጽነዋል፡፡

ኢትዮጵያዊያኑ በዝርዝር ምን አሉ ?

" እያንዳንዱ ሰው የግድ በቀን 17 ሰዓት መስራት አለበት፡፡ የተሰራበት ደመወዝ ግን አይከፈልም፡፡ ገቢ ካላስገባ ቅጣት አለ፡፡ አለንጋም አላቸው ይገርፋሉ፡፡ ጨለማ ቦታ ላይ ወስደውም ያስራሉ፡፡

በአንድ ጊዜ ሦስት 20፣ 20 ሊትር ጀሪካን ያሸክማሉ፡፡ ሁለቱን በሁለቱ ትክሻቸው፣ አንዱን በእግርና እግር መካከል እንዲሸከሙ የሚገደዱ ኢትዮጵያዊያን አሉ፡፡

በተጨማሪ ብዙ ሰዎች ባሉበት አካባቢ ፊት ለፊት እንደ ማሳያ ተደርገን እንገረፋለን፡፡ በቀን አምስት ሰዓት ብቻ ነው የሚታረፈው፡፡

እጅና ኮምፒዩተር ለአፍታ ከቦዘኑ፣ የሆነ ስህተት ከተሰራ ድብደባ አለ፡፡ ምንም ነጻነት የሌለበት አገር ነው፡፡

ብዙ አካላቸው የጎደሉ ሰዎች አሉ፡፡ አካል እስከማጉደል ነው ቅጣቱ፡፡ እግራቸው፣ እጃቸው፣ ሁሉ ነገራቸው የተጎዳ ሰዎች አሉ " ሲሉ አስረድተዋል።

ኢትዮጵያዊያኑን ካሉበት የከፋ ችግር ለማውጣት ምን እየተሰራ እንደሆነ ጥያቄ ያቀረብንላቸው  የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ ለጉዳዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

" በማይናማር የሚገኙ ዜጎቻችን ጉዳይ ይታወቃል፡፡ በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል በተለይ ሳወዝ ኤዢያ ካሉ ኤምባሲዎቻችን ውስጥ አንዱ ጃካርታ ነው፤ ኢንዶኖዢያ፡፡ ጉዳዩ እነርሱም ደርሷቸው እየጠከታተሉ ነው " ብለዋል።

" ይሄ መስመር በአጠቃላይ እንደ አዲስ የሕገ ወጥ ፍልሰት መንገድ ሆኖ ነው እየታዬ ያለው፡፡ እስከሁን ባልተለመደ ሁኔታ ወደዚህ አቅጣጫ ከዚህ ቀደም ከምናውቃቸው ትንሽ ወጣ ያለ ነው። ጉዳዩም ጥናት የሚፈልግ ሆኖ ነው የተገኘው " ሲሉ ተናግረዋል፡፡

" ዜጎች የትም አገር፣ የትም ቦታ ይሁኑ የመጀመሪያው መዳረሻ ችግራቸውን ለመፍታት ውጪ ጉዳይ እንደመሆኑ መጠን ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ክትትል እየተደረገበት ነው " ብለዋል።

ኢትዮጵያዊያኑ የአካል ጉዳት ጭምር እየደረሰባቸው በመሆኑ በፍጥነት እንዲደረስላቸው እየጠየቁ እንደመሆኑ  ከኤምባሲዎቹ ጋር ያለው ንግግራችሁ ተስፋ አለው ? በምን ደረጃ ላይ ነው ? የሚል ጥያቄ ቲክቫህ ለአምባሳደሩ አቅርቧል።

አምባሳደሩ በምላሻቸው፣ " እንደ አጋጣሚ ሆኖ ኢትዮጵያ ማይናማር ውስጥ ኤምባሲ የላትም፡፡ ምንም አይነት ዲፕሎማሲክ ውክልና የለንም " ብለዋል።

" ስለዚህ ከእርቀት ሆነው ነው ይህን ነገር የሚከታተሉት፡፡ መረጃው ትክክል ነው፡፡ ዜጎች ችግር ላይ ናቸው። ተቋሙም ኃላፊነት ወስዶ ለወገኖቻችን ለመድረስ ጥረት እያደረገ ነው " ሲሉ አክለዋል።

በችግር ላይ እንደሆኑ የሚነገርላቸው
ከ3000 በላይ ኢትዮጵያዊያን እንደሆኑ ነው፡፡ ተቋምዎስ ስንት እንደሆኑ ያውቃል? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄም ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።

" ቁጥር ልንሰጥ አንችልም፡፡ ነገር ግን ቁጥራቸው 3000ም ሆኑ ሦስት ኢትዮጵያዊያን ችግር ላይ እስካሉ ድረስ ችግራቸው ችግራችን ሆኖ ተቋሙ ዜጎችን ለመታደግ ይንቀሳቀሳል " ነው ያሉት።

ጉዳዩን የምንከታተለው ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia