TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ፦ "ዛሬ ሀምሌ 12ቀን 2013 ዓ/ም የሁለተኛውን አመት የህዳሴ ግድብ ሙሌት ተገባዶ ውሃው በግድቡ አናት ላይ ፈሶአል። ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆችም እንኩዋን ደስ አላችሁ: ይህ ውጤት ማለት 2 ተርባይኖችን ለማንቀሳቀስ የሚያስፈልገውን የውሃ መጠን ማለት ነው። በዘንድሮው አመት እየዘነበ ያለው ውሃ መጠን እጅግ ከፍተኛ ነው። ይህም ከፈጣሪ የተሰጠን…
#SUDAN #EGYPT #GERD

ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ፦

"... ሁሉ ነገሩ ፊዚክስ ነው፤ ውሃ ይገባል ይጠራቀማል ሲሞላ መያዝ የሚችለውን ያህል በአናቱ ይፈሳል ከዚህ የተለየ ነገር የለውም። ኒውክሌር ፊሲክስ አይደለም፤ ኖርማል ፊዚክስ ነው ፤ ይህንን ማየት ይቻላል።

ሁሉ ጊዜም እኛ ትክክለኛ ሳይንስ እና ያንን መሰረት ያደረገ ፖሊሲ ይዘን ነው የምንክተለው፤ ይህንኑ ነው በድርድሩ ወቅት ለማስረዳት የሞከርነው።

ነገር ግን ይህንን አልምተን የመጠቀም የኛ የኢትዮጵያውያን ሙሉ መብት ነው፤ ይህን እንድሄድበታለን፤ አስፈላጊ የሆነውን ክርክር እንቀጥልበታለን ክርክር የሚያስፈልግ ከሆነ። ነገር ግን ምንም አይነት መጥፎ እና በጎ ያልሆነ ተፅእኖ ስለማያሳድር ይልቅ ተባብረን ቶሎ ግድቡ የሚያልቅበትን ፣ ኔጌቲቭ ተፅእኖዎች በየማያስፈልግ ቦታ ሄደን ክርክር ከመግጠም ይልቅ እዚሁ አንድ ላይ አፍሪካ ውስጥ ቁጭ ብለን ሶስት ወንድማማች/እህትማማች ሀገሮች ተነጋግረን የሚገጥሙንን ችግሮች በጋራ እየፈታን ይልቅ ሪጅናችንን አስተሳስረን፣ እንዴት አድርገን በኢኮኖሚ ብልፅግና ማምጣት እንችላለን የሚሉት ነገሮች ላይ ትኩረት ሰጥተን መስራት ነው የሚያስፈልገን፤ ያ ነው የሚያዋጣው።

ዓለም ተመንጥቆ ሄዶ ይኸው ማርስና ሌሎች ፕላኔቶች ላይ ለማረፍ ይጥራሉ ፤ በቅርቡ ሰዎች ተመንጥቀው ሄደው ተመልሰው ያርፋሉ እኛ ግን ግድብ ስለሰራን እንደአዲስ ነገር አምጥተን ህዝባችንን ማስጨነቅ ፣ ተገቢ ባልሆኑና ፖለቲካዊ በሚመስሉ ንግግሮች ተጠምደን #መመቀኛኘት አይኖርብንም።

መተጋገዝ ፣ አብሮ ማደግ ለአፍሪካውያኖች በጣም አስገላጊ ነው፤ እኛ ይሄን ይዘን ነው የምንቀጥለው"

@tikvahethiopia
#GERD🇪🇹

የኢትዮጵያ አየር ኃይል የታላቁ ህዳሴ ግድብን ደህንነት በንቃት እየጠበቀ መሆኑን አሳወቀ።

የአየር ኃይል ዋና አዛዥ ሜ/ ጀኔራል ይልማ መርዳሳ፥ "ከታላቁ የህዳሴ ግድብ ዓይናችንን ለአፍታ ሳንነቅል ደህንነቱን እየጠበቅን እንገኛለን" ሲሉ ተናግረዋል።

ሜጄር ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ፥ ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጋር ተያይዞ የተከሰቱ የውጭ ጫናዎችና የውስጥ ትንኮሳዎች የኢትዮጵያ ወቅታዊ ፈተናዎች ሆነው ቆይተዋል ብለዋል።

"ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን ተጽእኖ የማይፈልጉ የውጭ ኃይሎች ከውስጥ ባንዳዎች ጋር ተቀናጅተው የተለያዩ ጫናዎችን ሲያደርጉ ቆይተዋል" ሲሉ አስረድተዋል።

የእነዚህ ኃይሎች ዋነኛ ዓላማ የኢትዮጵያ ህዝብ በራሱ ወጪ እየገነባው ያለው የህዳሴ ግድብ በከንቱ ማስቀረት መሆኑንም ገልፀዋል።

ሜጀር ጄነራል ይልማ ፥ "የኢትዮጵያ አየር ኃይል በግድቡ ላይ ሊጋረጡ የሚችሉ "ውጫዊ ስጋቶችን ጠንቅቆ ይገነዘባል" ያሉ ሲሆን በዚህም "ዓይናችንን ከግድቡ ላይ ለአፍታ ቢሆን ሳንነቅል ደህንነቱን የመጠበቅ ተልዕኳችንን እንወጣለን" ብለዋል።

በሌላ በኩል የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. አየር ኃይል መንግስት በሚሰጠውን ትእዛዝ መሰረት ሀገር ለማፍረስ በሚጥር የትኛውም ኃይል ላይ በሚፈለገው ቦታና ጊዜ ጥቃት ለመፈጸም ዝግጁ መሆኑንም መግለፃቸውን ከኢዜአ ድረገፅ ላይ ተመልክተናል።

@tikvahethiopia
#GERD #FDREDefenseForce

ሀገር መከላከያ ሰራዊት፥ ኢትዮጵያ እየገነባች ያለውን ግዙፉን የታላቁ ሕዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ ለማደናቀፍ ከሱዳን በአልምሃል ሰርጎ ለመግባት የሞከረውን የህወሓት ቅጥረኛ ሃይል ደመሰስኩኝ አለ።

የግድቡን ግንባታ ለማደናቀፍ ተልዕኮ ውስደው የተንቀሳቀሱና ሰራዊቱ የማያዳግም እርምጃ የወሰደባቸው ኃይሎች (የተገደሉ) በቁጥር 50 ሲሆኑ ፤ ከ70 በላይ የሚሆኑት ቁስለኛ ሆነዋል።

መከላከያ ሰራዊት ፥ እርምጃ የወሰደበት ኃይል የተለያዩ ፀረ ሰው እና ፀረ ተሽከርካሪ ፈንጂዎችን ለማጥመድ መሞከሩን ነገር ግን መቋቋም ተስኖት መበታተኑን አሳውቋል።

ይኸው ጥፋት ሊፈፅም የነበረው ኃይል ይጠቀምባቸው የነበሩ ቀላል እና ከባድ የቡድን መሳሪያዎች፣ ፈንጂዎች ወድመዋል ፤ የተቀሩትን ሰራዊቱ ተቆጣጥሯቸዋል።

የመተከል ዞን የተቀናጀ ግብረ ሃይል ኮማንድ ፖስት የኦፕሬሽን ዘርፍ አሰተባባሪ ኮ/ል ሰይፈ ኢንጊ ፣ "አሸባሪው ሕወሃት በግንባር ድል አልቀና ሲለው አብዛኝው ጦር ወደ ሰሜኑ ክፍል አቅንቷል በሚል ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ተቀናጅቶ የህዳሴ ግድባችንን ስራ ለማስተጓጎል ለማጥቃት ቢሞክርም አልተሳካለትም" ብለዋል።

በአሁን ሰዓት የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሃይል፣ እግረኛና ሜካናይዝድ ክፍለጦሮች እንዲሁም የክልል ልዩ ኃይሎች አስፈላጊውን ዝግጁነት በማረጋገጥ ግዳጃቸውን እየፈፀሙ እንደሚገኙ ተገልጿል።

@tikvahethiopia
#GERD : በህዳሴው ግድብ 2ኛ ዙር የደን ምንጣሮ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ከ40 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸው ተገለጸ።

ይህ የተገለፀው የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቴክኒክ እና ሙያ ስራ እድል ፈጠራ ኤጀንሲ የስራ አፈጻጸሙን በክልሉ መዲና አሶሳ በገመገመበት ወቅት ነው።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ በሽር አብዱራሂም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ተጠቃሚ መሆን ጀምሯል ያሉ ሲሆን በ2ኛው ዙር የግድቡ ውሃ ሙሌት ደን ምንጣሮ ስራ በክልሉ የሚገኙ በ149 ኢንተርፕራይዞች የተደራጁ ከ1 ሺህ 300 በላይ ስራ አጦች ተሳታፊ መሆናቸውን ገልፀዋል።

አክለውም ፥ የኢንተርፕራዞቹ አባላት 2 ሺህ 736 ሄክታር መሬት የደን ምንጣሮ ስራ ማካሄዳቸውንና በዚህም ከ40 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን ገልጸዋል፡፡

ዘጠኝ ሚሊዮን የሚጠጋ ብር በመቆጠብ ወደ ቋሚ ስራ መሸጋገራቸውን ዋና ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።

Credit : ENA

@tikvahethiopia
#GERD

ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በተመለከተ በአፍሪካ ህብረት በኩል የሚደረገው የሶስቱ ሀገራት ድርድር ውጤት ያመጣል ብለን እናምናለን ይህንንም እንደግፋለን አሉ በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ህብረት የኒውዚላንድ አምባሳደር ሚካኤል አፕተን።

አምባሳደሩ ይህ ያሉት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ተገኝተው ከሚኒስቴሩ ሚኒስትር ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ በመከሩበት ወቅት ነው።

በዚሁ ግዜ ነው አምባሳደሩ የአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነትን እንደሚደግፉ አሳውቀዋል።

በቀጣይ ግዜም የዜሮ ካርበን ልቀት መጠን ግብን ለማሳካት በአፍሪካ ህብረት በኩል የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ሃገራቸው ማቀዷን ገልጸው ከዚህ ውስጥ #ኢትዮጵያ አንዷ መሆኗን ጠቁመዋል።

ሚኒስትሩም በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አህመድ መሪነት ባለፉት ሁለት አመታት ከ4 ቢሊየን በላይ የተለያዩ አይነት ችግኞት መተከላቸውን ገልጸው ይህ ተግባር የአባይ ወንዝ ጨምሮ በሃገሪቱ ያሉ የውሃ አካላትን ደህንነት ለመጠበቅ የሚያስችል ነው ብለዋል።

የህዳሴ ግድብም ለሱዳንና ልግብፅ ያለውን ጥቅም አስረድተዋቸዋል።

ሚኒስትሩና አምባሳደሩ በቀጣይ በጋራ በሚሰሯቸው ታዳሽ ሀይል ልማት፤ የውሃና ሳኒቴሽን፤ ድርቅን፣ የአከባቢ ጥበቃና እንክብካቤ እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ መምከራቸው ተገልጿል።

@tikvahethiopia
#GERD

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ምክትል ጠ/ሚና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የታላቁ ህዳሴ ግድብን የግንባታ ሂደት ጎበኙ፡፡

በጉብኝት መርሀ ግብሩ የተለያዩ የፌዴራል መስሪያ ቤቶች ሚኒስትሮች ተሳትፈዋል፡፡

የሁሉም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የ100 ቀናት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት በህዳሴ ግድብ መገኛ በሆነችው ጉባ እየተካሄደ ነው፡፡

Credit : FBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ItsMyDam🇪🇹 ሀገራችን ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. ከ2022 ጀምሮ ከታላቁ የኅዳሴ ግድብ በዓመት 700 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት እንደምትጀምር የኢትዮጵያ የኢኖቬስን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የአይሲቲ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ሚኒስትር ደኤታ ሁሪያ አሊ ማህዲ አስታወቁ። ኢትዮጵያ በዚሁ ከመጀመሪያ ዙር እንደምታመነጭ ከሚጠበቀው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አጠቃላይ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት…
#GERD🇪🇹

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ስለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በዚህ ሳምንት በሰጡት መግለጫ ከተናገሩት ፦

(ከሪፖርተር)

" ... የታላቁ ህዳሴ ግድብ ኤሌክተሪክ ማመንጨት የሚጀምርበትን ቀን ይህ ነው ብሎ መነገር ባይቻልም፣ በጣም በቅርብ ጊዜ ይጀምራል።

የግድቡ ጉዳይ ሊለወጥ የማይችልና ያለቀ ነገር በመሆኑ፣ የታችኛው ተፋሰስ አገሮች ከዚህ ካለቀ ጉዳይ ጋር አብረው መቆም አለባቸው።

ከዚህ በኋላ ግድቡ ሲያመነጭ ለግብፆችም ሆነ ለሱዳኖች ጠቃሚ ከመሆኑም በላይ ፣ በሚመነጨው ኃይል ሌሎችም አገሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ እነዚህ አገሮች ቢሠሩ መልካም ነው። ነገር ግን የሦስትዮሽ ድርድሩ ይቁም ማለት አይደለም።

ሱዳን እና ግብፅ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ከጀመራቸሁ ችግር ይፈጠራል፣ ሰማዩ ይገለባበጣል የሚሉት ነገር አዲስ አይደለም፡፡

ቀድሞውንም ሙሌት ከጀመራችሁ አደጋ ይፈጠራል፣ ጉድ ይፈላል ሲሉ ነበር ይህ ፉከራ የተለመደ ቢሆንም አሁን ግን ያረጀና ጊዜው ያለፈበት ሆኗል።

በህዳሴ ግድቡ ውኃው ተርባይኑን አንቀሳቅሶ አልፎ ስለሚሄድ መጠኑ ስለማይቀንስ፣ ሱዳኖች የግድቡ ኃይል ማመንጨት መጀመር ሊያስደስታቸው እና ሊያከብሩት ይገባል። "

@tikvahethiopia
#GERD #ItsMyDam 🇪🇹

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ለአል-አረቢያ ሚዲያ የተናገሩት ፦

" ... ሀገራችን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን በፍጥነት እንድታጠናቅቅ ግብፅ ማበረታታት አለባት።

ግድቡ ግብፅን በድርቅ ወቅት እንኳ የውሃ ቋት ሆኖ የሚያገለግል እንደመሆኑ ፕሮጀክቱን ልትደግፈው ይገባል።

ሱዳን በአነስተኛ ግድቦቿ ላይ ይደርስብኛል ብላ የምታነሳውን የደህንነት ስጋት በሚመለከት መደበኛ የሆነ የመረጃ ልውውጥ ለማድረግ ኢትዮጵያ ዝግጁ እንደሆነች አቋሟን አስርድታለች።

ሀገሪቱ ግን አሁን ላይ የራሷን ብሄራዊ ጥቅም ከማስጠበቅ ይልቅ የሶስተኛ ወገን ጉዳይ አስፈፃሚ አየሆነች መጥታለች።

ኢትዮጵያ አንድ ወገን ብቻ ከአባይ ሀብት ተጠቃሚ ሲሆን ዘላለም አለሟን መጠበቅ አትችልም። በመሆኑም ሱዳን እና ግብፅ አሁን ላይ ከያዙት ግትር አቋም መላቀቅ አለባቸው።

ኢትዮጵያ የግድቡን ግንባታ በሚመለከት ብዙ አዎንታዊ የሆኑ እድሎችን አቅርባ ነበር። ግብፅና ሱዳን ባለመቀበላቸው ምክንያት ግን ሳይሳኩ ቀርተዋል።

የህዳሴ ግድብ ከጭቅጭቅ ይልቅ የቀጠናዊ ህብረትና አንድነት ማሳያ ነው። ኢትዮጵያ በታችኞቹ ተፋሰስ ሀገራት ላይ ምንም አይነት የጎላ ጉዳት ሳታደረስ የራሷን ሀብት መጠቀም ትችላለች "

(ኤፍቢሲ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጉዳይ ? ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ "የታላቁ ህዳሴ ግድብ ኃይል ማመንጨት ጀመረ" የሚሉ በርካታ መልዕክቶች እየተዘዋወሩ ይገኛሉ። መንግስት በዚህ ጉዳይ በይፋ ያሳወቀው ነገር ባይኖርም ከዚህ ቀደም የታላቁ ህዳሴ ግድብ ኃይል ለማመንጨት መቃረቡ በተደጋጋሚ ተገልጿል። ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሲሰራጩ ለነበሩት የግድቡ መረጃዎች ምንጫቸውን ለማወቅ ብናስስም ልንደርስበት…
#GERD

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ነገ እሁድ የካቲት 13 ቀን 2014 ዓ.ም የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት እንደሚጀምር አጀንስ ፍራንስ ፕሬስ (AFP) ሁለት ስማቸው ያልተገለፀ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናትን ዋቢ አድርጎ በዛሬው ዕለት ዘግቧል።

ዛሬ አንድ ከፍተኛ የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣን [ስማቸው ያልተገለፀ] " ነገ የግድቡ የመጀመሪያው የሃይል ማመንጫ ይሆናል" ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል።

አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ (AFP) ሌላ ሁለተኛ ከፍተኛ ባለስልጣን መረጃውን ማረጋገጣቸውን ገልጿል።

ሁለቱም ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉት ጉዳዩ በይፋ ስላልተገለፀ ነው ተብሏል።

ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ መንግስት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በቅርቡ ኃይል ማመንጨት እንደሚጀምር የገለፀ ሲሆን መቼ ? ለሚለው ግን መረጃ አልሰጠም ነበር።

ይኸው ጉዳይ ባለፉት ቀናት በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ሲዘዋወር ነበር፤ ነገር ግን በመንግስት በኩል ይፋዊ መረጃ አልተሰጠም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#GERD የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አንደኛው ሁኒት [ ዩኒት 10 ] ኃይል ማመንጨት መጀመሩን የግድቡ ሰራተኞች ለብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ተናግረዋል። @tikvahethiopia
#GERD

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ክፍሌ ሆሮ ፦

"... ማመንጨት ተጀመረ እንጂ ፕሮጀክቱ ተጠናቀቀ ማለት አይደለም።

ፕሮጀክቱን ለመጠናቀቅ አሁን ብለው ሁኔታ ከሁለት ዓመት ተኩል እስከ ሶስት ዓመት ሊፈጅብን ይችላል።

ስለዚህ ህዝቡ ከመጀመሪያውም ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያውያን ፕሮጀክት ነው። ፋይናንስ ሚደረገው በመንግስትና በኢትዮጵያ ነው ስለዚህ ይሄን ተገንዝበን ፕሮጀክቱን እስከመጨረሻው ፋይናንስ ማድረግ አለብን።

የኢትዮጵያን እውነታ አሁን ተርባይኑን መቶ ነው ውሃ እየፈሰሰ ያለው ስለዚህ ኢትዮጵያ ከዚህ ውሃ ምንም የምትቀንሰው ነገር ስለሌለ ዓለምም ይህን እንዲረዳ እያንዳንዳችን ተረባርበን ለፕሮጀክቱ ዲፕሎማት ሆነን መንቀሳቀስ አለብን። "

@tikvahethiopia
#GERD

" ግድቡን እኛ ሳንሆን እነሱ ናቸው የሚጠብቁት " - የቀድሞ የሀገራችን ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ

@tikvahethiopia