TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.6K photos
1.39K videos
200 files
3.74K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"አንዳንድ የግብፅ አመራሮች በግድባችን ላይ የሰነዘሩት ተቃውሞ እና ዛቻ ኢትዮጵያውያን በፍቅር እንጂ በማስፈራራት ማሸነፍ አይቻልም ታሪካችን ምስክር ነው፤ በመሆኑም ግብፅም ሆነ ሌላ ሀገር የአባይን ግድብ ለማስቆም አቅም የለውም የምንለው ኢትዮጵያውያን የፖለቲካ ሊህቃን የፖለቲካ ልዩነት ቢኖርብንም ለውጭ ጠላት ተከፈፍለን እንደማናውቅ ከታሪካችን ሊረዱ አለመቻላቸውን ያሳያል።" - ምክክር ፓርቲ

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ በተለምዶ 7ኛ ተብሎ ሚጠራው አካባቢ ልዩ ልዩ የተሰረቁ ንብረቶች መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቋል፡፡

በአነስተኛና ጥቃቅን ተደራጅተው ከሚሰሩበት ኮኒቴነር ውስጥ 203 የመኪና ቴፕ አናቶች፣ 102 የመኪና ቴፖች፣ የተለያዩ የጎማ መፍቻዎች፣ የኤሌክትሪክ ገመዶች እና የሰልቫትዮ ክዳን ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ነው ፖሊስ ያስታወቀው፡፡

የመርካቶ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የወንጀልና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ማስተባበሪያ ሃላፊ ምክትል ኢንስፔክቴር ብርሀኑ አለሙ ንረቶቹ ከህብረተሰቡ በሰጠ ጥቆማ መሰረት የፍርድ ቤት የመበርበርያ ትዕዛዝ በማውጣት የተያዘ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ስርቆት የተፈጸመባቸው ግለሰቦች መርካቶ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ በመምጣት ንብረታቸው መሆኑን አረጋግጠው መውሰድ እንደሚችሉም ምክትል ኢንስፔክቴር ብርሀኑ አለሙ ገልጸዋል፡፡

[የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን]

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሶሪያዊቷ ህፃን ቱርክ ገብታለች!

አባቷ ባለማመዳት መሠረት ቦንብ ሲፈንዳ የምትፈነድቀው ሶሪያዊት ሕፃን ከጦርነት ቀጣና ወጥታ ቱርክ መግባቷ ተሰማ።

ከቀናት በፊት በተሠራጨው ቪድዮ አማካይነት ታሪኳ በዓለም የናኘው ሳልዋ በቱርክ መንግሥት እርዳታ ወደ ድንበር አቋርጣ በጦርነት የታመሰች ሃገሯን ጥላ ሄዳለች።

በየደቂቃው ቦንብ በሚፈነዳባት ሶሪያ ልጁን የሚያሳድገው የሳልዋ አባት ልጁ ቦንብ በፈነዳ ቁጥር መሳቀቋን በመመልከት በሰቀቀን ፈንታ እንድትስቅ አለማምዷት ነበር። ሳልዋም የቦንብ ፍንዳታ በሰማች ቁጥር ትፈነድቃለች።

ኢድሊብ በተሰኘችው የጦርነት ቀጣና መኖሪያቸውን ያደረጉት ሳልዋና አባቷ ከቀናት በፊት በተሰራጨው ተንቀሳቃሽ ምስላቸው ምክንያት ታዋቂ ሆነዋል። ቪድዮው በተለቀቀ በሳምንቱ የቱርክ ባለሥልጣናት ሕፃኗ ኢድሊብን ለቃ እንድትወጣ አድርገዋል።

#BBC #TheTelegraph

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE

የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በአንጋፋው የማስታወቂያ ባለሞያ አቶ ውብሸት ወርቃለማሁ ሕልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ገልጿል፡፡

ለረጅም ጊዜ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን አባል የነበሩት አቶ ውብሸት ቡድኑ ወደተለያዩ ሃገራት በተጓዘበት ጊዜ የቡድኑን መንፈስ በማነቃቃት ጎልህ አስተዋፅኦ ነበራቸው ብሏል ሚኒስቴሩ፡፡

ሚኒስቴሩ በኢትዮጵያ በተለይ በብሮድካስት ሚድያ ማስታወቂያ ፈር ቀዳጅ ለነበሩት ለአቶ ውብሸት ቤተሰቦች፣ ጓደኞች እና ለኢትዮጵያ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን አባላት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን በመግለጽ ለሁሉም መጽናናትን ተመኝቷል፡፡

#ShegerFM

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

ኬኒያ ከሰሜን ጣሊያን ወደ ሃገሯ የሚደረጉ በረራዎችን አገደች፡፡ የሃገሪቷ ባለስልጣናት ዛሬ እንዳስታወቁት በጣሊያን በተለይም ሰሜናዊ የሃገሪቷ ክፍል ቬሮና እና ሚላን እየጨመረ በመጣው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ምክንያት በረራዎችን አግዳለች፡፡

ውሳኔው የተላለፈው በኬኒያ የጣሊያን ኤምባሲ የሰጠውን የአደጋ ጊዜ ማስጠንቀቂያ ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ኬኒያ ወረርሽኙ አሳሳቢ ወደሆነባቸው ሃገራት የምታደርገውን በረራ ከማቋረጥ በተጨማሪ ከጣሊያን፣ደቡብ ኮሪያና ኢራን ወደ ሃገሯ የሚገቡ ሰዎችን ለ14 ቀናት በለይቶ ማከሚያ ክፍል ውስጥ እንዲቆዩ እያደረገች መሆኑን ሲጂቲኤን ዘግቧል፡፡

#ኢትዮኤፍኤም #አባይነሽሽባባው
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ሹመት!

አቶ ሙሉቀን አማረ የፌደራል የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ሆነው ከየካቲት 20 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ በጠቅላይ ሚኒስቴር አቢይ አህመድ ተሹመዋል፡፡አቶ ሙሉቀን በተለያዩ የስራ ኃላፊነቶች ከ 2003 ዓ.ም ጀምሮ ተቋሙን አገልግለዋል።

#EsheteBekele
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EthiopianCatholicSecretariat የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ብፁዕ ካርዲናል ሊቀ-ጳጳስ ብርሀነ የሱስና የመርዋቸው መልእክተኞች ኤርትራ እንዳይገቡ መከልከላቸውን የቤተክርስትያንዋ ሴክረታርያት አርረጋግጧል። ካርዲናሉና ቡድናቸው የኤርትራ ካቶሊካዊት ቤተክርስተያን ባደረገችላቸው ጥሪ መሰረት ባለፈው ቅዳሜ ወደ ኤርትራ ተጉዘው እንዳነበር ነገር ግን የፀጥታ ኃይሎች አውሮፕላን ማረፍያ…
የኤርትራ መንግስት ማብራሪያ እንዲሰጥ ተጠየቀ!

ከሁለት ሳምንት በፊት ወደ ኤርትራ እንዳይገቡ አሥመራ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ የታገዱት የኢትዮጵያው የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጳጳስ ካርዲናል ብርሃነእየሱስ ጉዳይን በማስመልከት የኤርትራ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የኤርትራ መንግሥትን ማብራሪያ መጠየቋን ቫቲካን ኒውስ ዘገባ አመልክቷል።

የኤርትራ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጥ ጥያቄ ያቀረበችው ለኤርትራው ብሔራዊ የሐይማኖት ጉዳዮች ቢሮ ነው። ለቢሮው የቀረበው 'ማብራሪያ ይሰጠን' ደብዳቤ በኤርትራ የጳጳሳት ጉባኤ ዋና ፀሃፊ አባ ተስፋጊዮርጊስ ክፍሎም የተፈረመ ነው።

#BBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#WolloUniversity

ትላንት በቀን 24/06/2012 ከምሽቱ 1:20 አከባቢ በወሎ ዩኒቨርሲቲ ኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢኒስቲትውት የተማሪዎች መኝታ ብሎክ ውስጥ በሚገኝ ፑል ቤት በሁለት ተማሪዎች መካከል በተፈጠረ ጸብ ምክንያት የአንድ ተማሪ ህይወት ማለፉ ግቢው ለተማሪዎች በለጠፈው ማስታወቂያ ገልጿል፡፡ ለተማሪው ህይወት መጥፋት ምክንያት የሆነው ተማሪም በህግ ቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተካሄደበት መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አያይዞ ገልጿል፡፡

[Tikvah-family]
@tikvahethmagazine @tikvahethiopia
አጭር መረጃ ስለሞጆ-ሀዋሳ የፍጥነት መንገድ!

- የሞጆ ሀዋሳ የፍጥነት መንገድ አካል የሆነው የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ 88 በመቶ ተጠናቋል።

- ከሞጆ መቂ ከሚዘልቀው 56 ኪሎ ሜትር ውስጥ የ50 ኪሎ ሜትሩ የግንባታ ሂደቱ ተጠናቋል።

- የሞጆ – ሀዋሳ የፍጥነት መንገድ 202 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን 13 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በጀት ተይዞለታል።

- የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ ከአምስት ወራት በኋላ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

#ኢቢሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"የኤርትራ ህዝብ ከትግራይ ህዝብ ጋር መዋጋት አይፈልግም ፤ ኢሳያስ እና ጥቂት የህግደፍ አባላት ፍላጎት ሊኖራቸው ይችላል" - ሌ/ጀነራል ፃድቃን ገብረትንሳይ

📹#7MB #EthioForum #TPLF
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE

ኤክሳይስ ታክስ የተካተተበት አዲሱ ደረሰኝ ከመጋቢት 1 ቀን ጀምሮ ስራ ላይ እንደሚውል የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ።

አዲሱን የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ገቢራዊ ለማድረግ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን የገቢዎች ሚኒስቴር ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 አስታውቋል።

የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ቁጥር 1186/2012 የካቲት 5 ቀን 2012 ዓ.ም ፀድቆ ወደ ስራ መግባቱ የሚታወስ ነው፡፡

ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrTedrosAdhanom

'ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ኮሮናን በመዋጋት ሀላፊነታቸውን እየተወጡ ያሉ መሪ' ሲል ቢቢሲ አድንቋቸዋል፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር በመሆንእያገለገሉ ያሉትን ኢትዮጵያዊ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም በዚህ ከባድ ወቅት ሀላፊነታቸውን በአግባቡ እየተወጡ ያሉ ታላቅ ሰው በማለት ጠቅሷቸዋል።

ዶክተር ቴዎድሮስ የስርጭት አድማሱን እያሰፋና በተለያዩ የዓለም ሀገራት እየተስፋፋ ያለውን ኮሮና ቫይረስ አስጊ በሆነበት በዚህ ጊዜ ሃላፊ መሆን ፈታኝ ቢሆንም በትኩረት እየሠሩ ነው ብሏል ዘገባው፡፡

የዶክተር ቴድሮስ የሥልጣን ዘመን በመጀመሪያ በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ በተከሰተው ኢቦላ አሁን ደግሞ በኮሮና የተፈተነ ቢሆንም ዶክተር ቴዎድሮስ ግን ጠንክረው በመስራት ላይ መሆናቸው ሚያስመሰግናቸው ነው ሲል ገልጿል፡፡

የዓለም ጤና ድርጅት የመጀመሪያው አፍሪካዊ መሪ የሆኑት ዶክተር ቴዎድሮስ ከሁለት አመት በፊት ወደ ሃለፊነት የመጡ ሲሆን በየአመቱ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ሰዎች ህልፈት ምክንያት የሆኑትን ወባ፣ኩፍኝ፣የሳንባ ምች እና ኤችአይቪ ለመቀነስ እየሠሩ እንደሚገኙ ቢቢሲ በዘገባው አስታውሷል።

#ENA #BBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ወልቃይት ስኳር ፋብሪካ!

ከመንግሥት የልማት ድርጅቶች መካከል አንዱ የሆነውን የወልቃይት ስኳር ፋብሪካ ወደ ግል ይዘዋወራሉ ተብለው ከሚጠበቁ ፋብሪካዎች መካከል መሆኑን ተከትሎ፣ የትግራይ ንግድ እና ዘርፉ ማኅበራት ምክር ቤት ሀብት በማሰባሰብ ለመግዛት ፍላጎት እንዳለው ገለፀ።

የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት አሰፋ ኃይለ ሥላሴ ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ እንደተናገሩት፣ የአዋጪነት ጥናት በምክር ቤቱ ተጠንቶ በመጠናቀቁ የክልሉን ምሁራን፣ ባለሀብቶች እና በውጪ የሚኖሩ ዳያስፖራዎችን በማሳተፍ እና ሀብት በማሰባሰብ ጨረታውን ለማሸነፍ እንደሚሠሩ ተናግረዋል።

ይህንን እቅድ ምክር ቤቱ ይፋ ካደረገ ገና አንድ ሳምንቱ መሆኑን የገለፁት የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት አሰፋ በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ግን ከፍተኛ ፍላጎቶች መምጣታቸውን ገልፀዋል።

ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ ጋዜጣ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE

በሠው ማገት ወንጀል በተሠማራ ግለሠብ ላይ የ12 ዓመት ፅኑ እሥራት መወሠኑ ተገለፀ። ወንጀለኛ ፈንታሁን ቡቃያ እድሜው 26ዓመት የሳርና ቀበሌ ነዋሪ ሲሆን የተከሰሰበት የወንጀል ዓይነት ሠው አግቶ 33, ሽህ ብር በመቀበሉ ነው። ወንጀለኛውም በፈፀመው ወንጀል ምክንያት 27/3/2012 ዓ/ም በፀጥታ ሀይል ቁጥጥር ስር ወሎ በሶሮቃ ፍ/ቤት ክስ ተመስርቶበታል። ፍ/ቤቱም ተከሳሹ የፈፀመው ወንጀል በማስረጃ የተደገፈ በመሆኑ የ12 ዓመት ፅኑ እሥራት ውሣኔ የተፈረደበት መሆኑን ኢንስፔክተር መላክ ከሣ ተናግረዋል።

ምንጭ፦ Tegedie Communication
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ItsMyDam

አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የተናገሩት፦

"ግድቡን የምንገነባው በራሳችን መሬት ላይ፤ ከራሳችን ሀገር የመነጨ ውሃ ፣ በራሳችን ገንዘብ ፤ ውሃ እንዳትሞሉ ብሎ ነገር አሜሪካኖቹ ከእነሱ በሚፈሰው ወንዝ በየትኛውም ያላደረጉትን ኢትዮጵያ እንድታደርግ የሚጠይቅ ስለሆነ በምንም መንገድ ተቀባይነት የለውም። ተስፋ የምናደርገው ግን ይሄንን አባባል ያስተካክላሉ ብለን ነው። እኛ ግን ግንባታችን ይፋጠንና ለዛ ይድረስ እንጂ የእኛው የራሳችን ግድብ ስለሆነ እንሞላለን ማንን ፍቃድ እንጠይቃለን?"

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ የማስታወቂያ አባት ስርዓተ ቀብር...

በኢትዮጵያ የማስታወቂያ ሥራ ፈር ቀዳጅነት የሚታወቁት አንጋፋው ሁለገብ የኪነጥበብ ባለሙያ ውብሸት ወርቃለማሁ የቀብር ሥርዓት ዛሬ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል፡፡

#ዋልተንጉስዘሸገር
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የሙስጠፌ ወንድም ለከፍተኛ ህክምና አ/አ መጡ!

የሶማሌ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዘዳንት ሙስጠፌ ዑመር መሐመድ ታናሽ ወንድም የሆኑት አብዲራህማን ዑመር በደገሃቡር ከተማ በደረሰባቸው በስለት የመወጋት አደጋ ለከፍተኛ ህክምና ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ ገብተዋል።

የፕሬዝዳንቱ ኮሚኒኬሽን አማካሪ መሐመድ ኦላድ ጥቃቱ የደረሰባቸው በትላንተናው እለት መሆኑን ገልፀው ለግዜው የጤንነታቸው ሁኔታ ላይ እና የጥቃቱን ምክኒያት በተመለከተ ማብራሪያ መስጠት እደማይችሉ ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ ተናግረዋል።

[በአዲስ ማለዳ ጋዜጣ]
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ኦነግ መንግሥትን አስጠነቀቀ!

በሰላም ከምንኖርበት ስፍራ እጅግ በሚያስደነግጥ ሁኔታ በታጠቀ ኃይል በአመራሮቻችን ላይ ወረራ ተፈጽሞብናል። በወቅቱ የመጣብን ኃይል ጥቂት ሲቪሎችን ለመያዝ የመጣ ሳይሆን አንድ ጦር ለመማረክ የመጣ ይመስል ነበር።»

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ኦነግ «በሀገሪቱ ታሪክ እስከ ዛሬ ያልተፈጸመ» ያለው ግፍ እየተፈጸመብኝ ነው ሲል አማረረ። ኦነግ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ «የፖለቲካ ምህዳሩ የሰፋ መስሎን ወደ ሀገር ቤት ብንመለስም፣ መንግሥት በጦር ሠራዊቱ እና በሃብቱ (በከፍተኛ መዋዕለ ንዋዩ) በመተማመን በፓርቲያችን ላይ ግፍ እየፈጸመብን ነው» ብሏል። 

More https://telegra.ph/ETH-03-04-4

#DW
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የካቲት 29 በኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል እንገናኝ!

Feminist Front ሃገር በቀል በጾታ እኩልነት ላይ የሚሰራ የፌሚኒስት ወጣቶች ማህበር ነው። በአሁን ወቅት Feminist Front ከግጥማዊ ቅዳሜ ጋር በመተባበር ‘ላንቺ’ የተባለ የድጋፍ መዋጮ ለአይነ ስውራን ሴቶች በየካቲት 29, 2012 አዘጋጅቷል።

ይህ የድጋፍ መዋጮ እነዚህ ሴቶች የሚያሳልፉትን ተደራራቢ ችግር ለመጋፈጥ እና ከማህበረሰቡ የሚደርስባቸውን መገለል ለመዋጋት የሚደረግ ነው።

የኛ ማህበር የነዚህን ሴቶች ለራሳቸው እና ለማህበረሰባቸው ለውጥን የማበርከት ተስጦ ሲያምን፣ እርሶም የዚ ድጋፍ ተሳታፊ እንዲሆኑ ተጋብዘዋል።

Contact us: @FeministFront to get your tickets

#Lanchi
#የእኩልነትትውልድ
#FeministFront
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#HAWASSA

የሐዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ፦

- ሐሰተኛ የብር ኖቶች ህትመት ሲያካሂድ የነበረ አንድ የውጭ ዜግነት ያለው ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሏል።

- ፖሊስ ሰሞኑን ባካሄደው ክትትል በተደራጀ መንገድ የተሰረቁ ስምንት ሁለት እግር ብስክሌቶች እና አራት መኪኖችም በቁጥጥር ስር በማዋል በ27 ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ እያካሄደ ይገኛል።

- ተሸከርካሪዎቹ ከተሰረቁ በኋላ ህጋዊ ሰውነት ያላቸው ለማስመሰል ሰነድ ተዘጋጅቶላቸው ለአገልግሎት እንዲውሉ ይደረግ ነበር።

- ተለይቶ ያልተገለፀ የውጭ አገር ዜግነት ያለው ግለሰብም ሐሰተኛ የብር ኖቶች ህትመት ሲያካሂድ ከነሙሉ ቁሳቁሱ መያዙን መምሪያው ያስታወቀ ሲሆን ምርመራም እየተካሄደበት ነው።

- አብዛኞቹ የስርቆት ወንጀሎች በረቀቀ መንገድ የተፈፀሙ መሆናቸውን የጠቆመው ፖሊስ፤ ወንጀለኞቹን በቁጥጥር ስር ለማዋል በተደረገው ጥረት የህብረተሰቡ ሚና ከፍተኛ እንደነበርም ተገልጿል፡፡

[የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር፣ ኢቢሲ]
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia