TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#DrTedrosAdhanom

ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የግድያ ዛቻና የዘረኛ ንግግር ጥቃት እየተሰነዘረባቸው መሆኑን ዛሬ በሰጡት መግለጫቸው ተናግረዋል።

“I can tell you personal attacks that have been going on > 3 months. Racist comments, black or Negro. I’m proud of being black, proud of being Negro. I don’t care, to be honest ... even death threats. I don’t give a damn."

MORE : https://telegra.ph/BBC-04-08

#SamiraSawali
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrTedrosAdhanom #WHO #DonaldTrump

ትላንት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሀገራቸው ለWHO የምትሰጠውን ከፍተኛ ገንዘብ እንደምታቅብ ተናገረዋል። የዓለም የጤና ድርጅት ኮቪድ-19 የዓለም አቀፍ ወረርሽኝ መሆኑን በጊዜ አልተናገረም ብለዋል ፕሬዘዳንቱ።

ድርጅቱ ይህን ያደርገው በሽታው ለተጀመረባት #ቻይና ሲል ሊሆን ይችላል ሲሉ ግምት አዘል አነጋገር ተናግረዋል። "በጣም ቻይና ተኮር ይመስላሉ ፣ ይህን ማጤን ይኖርብናል' ሲሉ ተደምጠዋል ዶናልድ ትራምፕ።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ወረርሽኝ ባለበት በዚህ አይነት ሁኔታ ለጤናው ድርጅት /WHO/ የሚዋጣ ገንዘብ መከልከ ተገቢ ነው ወይ? ተብለው ከጋዜጠኛ የተጠየቁት ትራምፕ 'እኔ አንሰጥም አላልኩም፣ እናጤነዋለን ነው ያለኩት' ሲሉ መልሰዋል።

ከፍተኛ ዘመቻ እየተካሄደባቸው የሚገኙት የዓለም የጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ዛሬ በሰጡት ዕለታዊ መግለጫቸው ላይ የግድያ ዛቻ እንደደረሰባቸው ፤ እሳቸው ግን ግድ እንዳልሰጣቸው ተናግረዋል። በማን ይህ ሊደረግ እንደቻለ ግን አልተናገሩም።

ከሁለት (2) እና ከሦስት (3) ወር በላይ #ዘረኛ ጥቃቶች ተሰንዝረውብኛል ያሉት የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተሩ ዶ/ር ቴድሮስ 'ጥቁር ተብያለሁ። እውነቱን ለመናገር እኔ በጥቁርነቴ እኮራለሁ። የሚባለው ነገርም ግድ አይሰጠኝም' ሲሉም ተደምጠዋል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ፣ ቪኦኤ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#WorldHealthOrganization ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኮሮናቫይረስ የሰጠው ምላሽ ቀርፋፋ ነው፤ በአካሄዱም ቻይናን ማዕከል አድርጓል ላሉት የዓለም ጤና ድርጅት አገራቸው የምታበረክተውን የገንዘብ መዋጮ እዲቋረጥ አዘዋል። ይህም ማለት አሜሪካ ለድርጅቱ በየዓመቱ ለድርጅቱ ትሰጥ የነበረው ገንዘብ እንዲቆም የሚያደርግ ነው ተብሏል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ የትራምፕን…
#DrTedrosAdhanom

የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድኃኖም አሜሪካ ለድርጅታቸው የምታደርገውን ድጋፍ አቋርጣለሁ ማለቷ እንዳሳዘናቸው ተናገሩ።

በውሳኔው ቅር ተሰኝተናል ያሉት ኃላፊው፤ "ለህብረተሰብ ጤና፣ ለሳይንስ እና ለሁሉም የዓለም ሕዝብ ያለ አድልዎ እና ፍርሃት ማገልገላችን ይቀጥላል" ብለዋል።

ዶክተር ቴድሮስ አሜሪካ የምትሰጠውን ፈንድ ማቋረጧ በድርጅታቸው ላይ የሚያስከትለውን ጉዳት እንደሚያጤኑት እና ሥራዎች ሳይቋረጡ መከናወናቸውን እንደሚያረጋግጡ መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ፣ ኢቢሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrTedrosAdhanom

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክትር ዶክትር ቴድሮስ አድኃኖም በፖለቲካዊ አለመግባባት ሳቢያ የሰውን ህይወት ለማዳን የሚደረገው ጥረት ሊደናቅፍ እንደሚችልም አስጠነቀቁ።

ከአሜሪካ ጋር አለምግባባት ውስጥ ስለገባው ድርጅታቸው በተመለከተ ዶክተር ቴድሮስ በስሜት ተሞልተው በሰጡት መግለጫ ላይ እንደተናገሩት "በዓለም የጤና ድርጅት ውስጥ ምንም ምስጢር የለንም፤ የህይወት ጉዳይ በመሆኑ መረጃን ባገኘን ጊዜ ሁሉ እናጋራለን" ሲሉ ለጋዜጠኞች ገልጸዋል።

ዋና ዳይሬክተሩ ጨምረውም "ከየት እንደመጣሁ ታውቃላችሁ፤ ስለጦርነት አውቃለሁ። ድህነትንም አውቃለሁ። ሰዎችን ለስቃይ ስለሚዳርጉ ነገሮች አውቃለሁ። ሰዎች እንዴት በድህነት ምክንያት ለሞት እንደሚዳረጉ አውቃለሁ" ሲሉ በስሜት ተናግረዋል።

"ይህን ሁሉ የማያውቁ ይኖራሉ. . . በቀላል የህይወት ጎዳና ላይ አልፈው ይሆናል። ምናልባትም ጦርነት ማለት፤ ድህነት ማለት ምን እንደሆኑ ላያውቁ ይችላሉ። ለዚህም ነው ስሜታዊ የሆንኩት" ብለዋል ዋና ዳይሬክተሩ።

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድኃኖም ድርጅታቸው የኮሮናቫይረስን የተመለከተ ምንም አይነት መረጃ ከየትኛውም አገር አለመደበቁን በዘርዝር አብራርተዋል።

ዶክትር ቴድሮስ በቴሌቪዥን በተላለፈው መግለጫቸው ላይ እንዳሉት ከአሜሪካ የበሽታ መቆጠጠሪያና መከላከያ ማዕከል የተወከሉ 15 ባለሙያዎች ከጥር ወር ጀምሮ ስለበሽታው ያሉ መረጃዎችን በሙሉ እንዲያውቁ ሲደረጉ ቆይተዋል ብለዋል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrTedrosAdhanom

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም በአፍሪካ ፣ በማእከላዊ እና በደቡብ አሜሪካ እና በምስራቅ አውሮፓ እየጨመረ የመጣው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ አዝማሚያዎች አሳሰቢ ነው ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡

ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም በጄኔቫ በቪዲዮ ኮንፈረንስ እንደገለጹት፣ በምዕራብ አውሮፓ ወረርሽኙ እየተረጋጋ ወይም እየቀነሰ ቢታይም፣ ለብዙ አገሮች በሽታው ገና እየጀመረ መሆኑንና በወረርሽኙ የመጀመሪያ ደረጃዎች ላይ ጥሩ ሆነው የተገኙት አንዳንድ አገራት በአሁኑ ወቅት ቫይረሱ እየተስፋፋባቸው መምጣቱን ዶ/ር ቴድሮስ ተናግረዋል፡፡

“ብዙ አገራት አሁንም በወረርሽኙ የመጀመሪያ ደረጃዎች ላይ ናቸው፤ በወረርሽኙ መጀመሪያ ላይ የተጎዱት የተወሰኑ አገራት አሁን መልሶ መቋቋም ጀምረዋል” ብለዋል ዋና ዳይሬክተሩ፡፡

ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም "ምንም ስህተት መስራት የለብንም፣ የምንጓዘው ረዥም መንገድ አለ፣ ይህ ቫይረስ ለረጅም ጊዜ ከእኛ ጋር ይቆያል" ማለታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ምንጭ፦ ቢቢሲ፣ ኢቢሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#WHA73 የዓለም የጤና ድርጅት አመታዊ ጉባኤ በቪዲዮ ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው። ጉባዔው በዋናነት አባል ሀገራቱ ያቀረቡትን ጥሪ ተከትሎ በኮሮና ቫይረስ ዙሪያ የሚያተኩር ነው ተብሏል። በጉባዔው መክፈቻ ላይ የቻይናው ፕሬዚዳንት ዢ ጂንፒንግ ሃገራቸው ቫይረሱን ለመቆጣጠር አበረታች ስራ መስራቷን ጠቅሰው፥ አስፈላጊው ግምገማ ቫይረሱን መቆጣጠር ከተቻለ በኋላ ይደረጋል ብለዋል። አያይዘውም ሃገራቸው ቫይረሱን…
#WHA73 #DrTedrosAdhanom

በትንሹ 320 ነርሶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ሞተዋል!

በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት የሚሞቱ የጤና ባለሙያዎች ቁጥር ከፍተኛ አደጋን ደቅኗል ሲሉ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ተናገረዋል።

ዓለም አቀፉ የነርሶች ምክርቤት በስሩ ካሉት ማህበራት ባሰባሰበድ መረጃ መሰረት በአንዳንድ ሃገራት የሚስተዋለው የነርሶቹ የተጠቂነት ቁጥር በ20 በመቶ አሻቅቧል፤ በዓለም አቀፍ ደረጃም በትንሹ 320 ነርሶች ሞተዋል፡፡

ዶ/ር ቴድሮስ መረጃዎች በወጉ ሊሰበሰቡ ቢችሉ ቁጥሩ ከዚህም በላይ ሊሆን እንደሚችልም ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም የድርጅቱ አባል ሃገራት የጤና ባለሙያዎቻቸውን ከወረርሽኙ #ሊጠብቁ ፣ አስፈላጊውን የህክምና ግብዓቶች ሊያሟሉላቸው እና መረጃዎችን ስርዓት ባለው መልኩ ሊሰበስቡ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ምንጭ፦ አል ዓይን
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrTedrosAdhanom

የዓለም ጤና ድርጅት /WHO/ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) መድሃኒት ለማግኘት ሲጠቀምበት የነበረውን የፀረ ወባ መድሃኒት ፣ ሃይድሮክሲክሎሮክዊን ለጊዜው #አቋረጠ

የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ቦርድ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው ከአምስት ቀን በፊት በታተመው ላንሰት የሕክምና መጽሔት ላይ የወጣውን የጥናት ሪፖርት መሰረት አድርጎ ነው። በዚህ ጥናት መሰረት መድሃኒቱ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎችን ሞት #ያፋጥናል ይላል።

የዓለም ጤና ድርጅት [WHO] ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት "የከፍተኛ አመራሮቹ ቡድን አባላቱ #የሃይድሮክሲክሎሮክዊን ሙከራ ደህንነቱ ዳግም በደህንነት ቁጥጥር ቦርዱ እስኪመረመር ድረስ ለጊዜው እንዲቋረጥ ወስነዋል" ብለዋል። ሌሎቹ የምርምር ስራዎች ግን መቀጠላቸውን ገልፀዋል።

'ሃይድሮክሲክሎሮክዊን' (የፀረ ወባ መድሃኒት) በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና ሌሎች መሪዎች ለኮሮና ቫይረስ ሕሙማን ቢሰጥ በፍጥነት እንዲያገግሙ ያደርጋል በሚል ሲወደስ ቆይቶ ነበር።

#BBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrTedrosAdhanom

"የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እየተባባሰ ነው " - WHO

ምንም እንኳን የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሥርጭት በአውሮፓ እየቀነሰ ቢሆንም በዓለም አቀፍ ደረጃ ግን እየተባባሰ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድኃኖም አስታወቁ።

ዳይሬክተሩ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ፤ ባለፉት 10 ቀናት ውስጥ ከ100 ሺህ በላይ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ገልፀዋል።

ትናንት ከተመዘገበው ከ136,000 በላይ ኬዝ 75 በመቶ የሚሆነው የተገኘው በአስር (10) አገራት ሲሆን አብዛኞቹ አሜሪካ እና ደቡብ እስያ ውስጥ የተገኙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ በበርካታ አገራት የታየው አዎንታዊ ለውጥ አበረታች እንደሆነ ዳይሬክተሩ ዶክተር ቴድሮስ አድኃኖም አክለዋል።

"አሁን ላይ የእነዚህ አገራት ትልቁ ችግር #ግድየለሽነት ነው። ምን ያህል ሕዝብ ለቫይረሱ እንደተጋለጠ የሚያሳዩ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት አሁንም በዓለም ላይ ያለ አብዛኛው ሰው ለበሽታው ተጋላጭ እንደሆነ ያሳያል" ሲሉም አስጠንቅቀዋል።

#BBC #GoaChronicle
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Dexamethasone 'ዴክሳሜታሰን' የተባለው መድሃኒት በኮሮና ቫይረስ በሽታ በፅኑ የታመሙትን ሰዎች ህይወት ለመታገድ እንደሚረዳ የብሪታንያ ተመራማሪዎች ገለፁ። ሳይንቲስቶቹ በህክምና ላይ ያሉና በቬንትሌተር የሚተነፍሱት ታማሚዎችን የመሞት እድል በአንድ ሶስተኛ እንደሚቀንስ የገለጹ ሲሆን በኦክስጅን ውስጥ ያሉትን የመሞት ዕድላቸውን በአንድ አምስተኛ እንደሚቀንስ ተናግረዋል፡፡ ይህ መድሃኒት የኮቪድ…
#DrTedrosAdhanom

በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ 'ዴክሳሜታሶን' በተባለው መድኃኒት ላይ የተደረገው ሙከራና ያስገኘውን ውጤት በበጎ እንደሚመለከተው የዓለም ጤና ድርጅት ማስታወቁን #ቢቢሲ ዘግቧል።

በሙከራው ይህ መድኃኒት በኮቪድ-19 በጽኑ ከታመሙ ሰዎች የአንድ ሦስተኛውን ሕይወት መታደግ እንደሚችል እና በወረርሽኙ ሰበብ ኦክስጂን በሚያስፈልጋቸው ሰዎች ላይ የሚያጋጥምን ሞት በአንድ አምስተኛ ሊቀንስ እንደሚችል ለድርጅቱ የቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ ግኝት አመልክቷል።

ድርጅቱ እንዳለው የዴክሳሜታሶን ጠቀሜታ በኮቪድ-19 በጸና በታመሙ ሰዎች ላይ እንጂ ቀለል ያለ ህመም ባለቸው ላይ እንዳልሆነ አመልክቷል https://telegra.ph/T-06-18-2

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia