TIKVAH-ETHIOPIA
1.42M subscribers
55.2K photos
1.38K videos
199 files
3.7K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ኢትዮጵያዊ ነኝ ዘረኝነትን ተጠይፌ ከፍቅር ጋር ተደምሬ ሀገሬን ለመለወጥ ተነስቻለሁ!

#ETHIOPIA ሼር!
#ኢትዮጵያዊ ነኝ ዘረኝነትን ተጠይፌ ከፍቅር ጋር ተደምሬ ሀገሬን ለመለወጥ ተነስቻለሁ!

#ETHIOPIA ሼር!
#update አዲስ አበባ⬇️

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የነዋሪዎች ምዝገባና የመታወቂያ አሰጣጥ መመርያ ቁጥር 3/2010 በማሻሻል፣ #ብሔር_የማይጠቀስበት መታወቂያ ለነዋሪዎች መስጠት ሊጀምር ነው፡፡

የተሻሻለው መመርያ የከተማውን ነዋሪዎች የመታወቂያ አሰጣጥ ከማነዋል ወደ ዲጂታል የሚያሸጋግርና በአሻራ የተደገፈም ስለሚሆን፣ በሐሰተኛ ሰነድ መታወቂያ የያዙ ግለሰቦችን መለየት ያስችላል ተብሏል፡፡

ይህንን አሠራር ተግባራዊ ለማድረግ በክፍላተ ከተሞችና በወረዳዎች የሚገኙ አመራሮችና ሠራተኞችን ያካተተ ሥልጠና፣ ቅዳሜ ነሐሴ 19 ቀን 2010 ዓ.ም. ተሰጥቷል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች መታወቂያ ብሔርን የሚጠቅስ በመሆኑ፣ ይህም ከአንድነት ይልቅ ልዩነቶችን የሚያጎላ ስለሆነ በተገኘው አጋጣሚ ቅሬታ ሲቀርብበት ቆይቷል፡፡

ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) ሥልጣን በያዙ ማግሥት ይህንን ጉዳይ በሚመለከት እንደገለጹት፣ የመታወቂያ ጉዳይ ቀላል ቢመስልም ከፍተኛ ቅሬታ እየተነሳበት በመሆኑ አሰጣጡን ማስተካከል ይገባል፡፡

በዚህ መሠረት መመርያው የተሻሻለ በመሆኑ በመታወቂያ አሰጣጥ ላይ በሁለት መሠረታዊ ጉዳዮች ለውጥ ያመጣል ተብሏል፡፡

የመጀመሪያው በመታወቂያ ላይ ከብሔር ስያሜ ይልቅ #ኢትዮጵያዊ ሲባል፣ በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ አሰጣጡ ዲጂታል ስለሚሆን ሕገወጦችን መለየት እንደሚያስችል ተገልጿል፡፡ በተለይ ሕገወጥ ጥቅም የሚሹ ግለሰቦች፣ በተለያዩ ዘዴዎች መታወቂያ በማውጣት ሲያገኙ የቆዩትን ጥቅም እንደሚያስቀር ታምኗል፡፡

ለአብነት በክልል ከተሞች የግል መኖሪያ ቤት እያላቸው በሕገወጥ መንገድ  የአዲስ አበባ ነዋሪነት መታወቂያ በመያዝ ኮንዶሚኒየም ቤት የተቀራመቱትን ዕርምጃ መውሰድ ያስችላል ተብሏል፡፡

የተሻሻለው መመርያ የኮምፒዩተር አመዘጋገብ፣ የነዋሪዎች ምዝገባ ሒደት፣ የነዋሪዎች መታወቂያ ይዘትና የመሸኛ ጉዳይን በዝርዝር ይዟል ተብሏል፡፡

ምንጭ፦ ሪፖርተር ጋዜጣ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
🏆የሰላም እና ወዳጅነት ዋንጫ🏆

የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ወጣት ብሔራዊ ቡድኖችን የሚያገናኝ ውድድር በቅርቡ አስመራ ላይ ይደረጋል።

“የሰላም እና ወዳጅነት ዋንጫ” በሚል ስያሜ በየካቲት ወር መጀመሪያ ይደረጋል ተብሎ የሚጠበቀው ውድድር የ10 ቀናት እድሜ የሚኖረው ሲሆን የኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ሶማሊያ እና ጅቡቲ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኖችን ያሳትፋል።

የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዘዳንት አቶ #ኢሳይያስ_ጅራን ጨምሮ የቀጠናው የእግርኳስ አመራሮች ከሳምንት በፊት በአስመራ በነበራቸው ስብሰባ ውድድሩ በሚደረግበት ሂደት ላይ ተነጋግረዋል።

የአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) በበኩሉ 25,000 ዶላር ለኤርትራው ፌዴሬሽን በመስጠት ዝግጅቱን ለማገዝ ተስማምቷል።

የኤርትራ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ለዚህ ውድድር ከወዲሁ ዝግጅቱን እያደረገ የሚገኝ ሲሆን ዛሬ #ኢትዮጵያዊ ዳኞች በሚመሩት የወዳጅነት ጨዋታ የሱዳን አቻውን ያስተናግዳል።

ሁለቱ ሀገራት በቅርቡ ሰላማዊ ግንኙነት ከቀጠሉ በኋላ በብሔራዊ ቡድን እና በክለቦች ደረጃ የወዳጅነት ጨዋታዎችን ለማድረግ ቢታሰብም በተለያዩ ምክንያቶች ሳይሳካ እንደቀረ ይታወሳል።

ምንጭ፦ ሶከር ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቴላቪቭ‼️

በሺህዎች የሚቆጠሩ ቤተ እስራኤላውያን አንድ #ኢትዮጵያዊ በእስራኤል ፖሊስ መገደሉን በመቃወም ቴላቪቭ ውስጥ ትናንት የተቃውሞ ሰልፍ አካሄዱ። የ24 ዓመቱ ኢትዮጵያዊ ይሁዳ ባይድጋ ከሁለት ሳምንት በፊት ነበር በፖሊስ ተተኩሶበት #የተገደለው#ሰልፈኞቹ የቴላቪቭ ዋና ጎዳናን #በመዝጋት እና በዋና ዋና መንገዶች በማለፍ ባካሄዱት ሰልፍ በእሥራኤል ዘረኝነትን እና ፖሊስ የሚፈጽመውን ከመጠን ያለፈ ጥቃት እና አድልዎ #ተቃውመዋል። በእስራኤል ምክር ቤት የሰብአዊ ሐብት ሎጂስቲክ አስተባባሪ አቶ ዮናታን ታከለ ለጀርመን ድምፅ ራድዮ እንደተናገሩት ኢትዮጵያዊውን የገደለው ፖሊስ አሁንም በስራ ላይ ነው። ይህም ቤተ እስራኤላውያንን በእጅጉ አስቆጥቷል። የዐአእምሮ ህመምተኛው ልጃቸው ይሁዳ ከቤቱ ስለት ይዞ ሲወጣ ፣እንዲደርስላቸው እናቱ ደውለው የነገሩት ፖሊስ ተኩሶ እንደገደለው ተዘግቧል። በእሥራኤል ጦር ውስጥ ማገልገሉ የተነገረውን የይሁዳን አሟሟት የእስራኤል የፍትህ ሚኒስቴር እያጣራሁ ነው ብሏል።

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 23/2011 ዓ.ም.

ከትራንስፓርት ሚንስቴርና ከሌሎች ሚንስቴር መስሪያ ቤቶች የተወጣጣው የሉኡካን ቡድን የጅቡቲ ወደብን ጎብኝቷል።
.
.
ባሳለፍነዉ ሳምንት መጨረሻ በምዕራብ እንዲሁም ምሥራቅ ጉጂ በኢትዮጵያ መከላከያ ኃይልና በኦሮሞ ነጻነት ግንባር ታጣቂዎች መካከል በታካሄደ ግጭት የሰው ህይወት ማለፉን በርካቶች ከቤታቸው መፈናቀላቸው ተናግረዋል።
.
.
ከአመት በፊት ሳውዲ አረቢያ ጀምራው የነበረውን መጠነ ሰፊ የፀረ-ሙስና ዘመቻ እንዳጠናቀቀች አስታውቃለች፡፡ የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት 100 ቢሊዮን ዶላር በጥሬ ገንዘብ እና በቁስ መልክ በቁጥጥር ሥር ከዋሉት ሰዎች መሰብሰቡን አስታውቋል።
.
.
የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር በቅርቡ የፀደቀውን #የስደተኞች_አዋጅ በመቃወም ነገ በጋምቤላ ከተማ ሊደረግ ለታሰበው የተቃውሞ ሰልፍ ፈቃድ #ከልክሏል
.
.
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለ6 ሺህ ነጋዴዎች ግብር ሰርዣለሁ ብሏል፡፡ ግብር ስረዛው ከ2003 እስከ 2010 ዓ.ም ባለው ጊዜ ከፍተኛ የግብር ተመን ተጥሎባቸው አቤቱታ ሲያቀርቡ የቆዩትን ነጋዴዎች ያካትታል፡፡
.
.
4ኛው የህዝብና ቤት ቆጠራ ከመጋቢት 29 ቀን ጀምሮ ይካሄዳል።
.
.
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ህግን ተከትለው የሚሰሩ የሪል ስቴት አልሚዎችን እንደሚደግፍ ነገር ግን ህገወጥ የሆኑት ላይ #ዕርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል።
.
.
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ጃማ ወረዳ በጫነው አሸዋ ላይ 31 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ ሲኖትራክ ተሽከርካሪ ተገልብጦ የሰዎች ህይወት እና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።
.
.
በቴፒ ከተማ ከትንላንት ጀምሮ ዳግም #ያገረሸው #አለመረጋጋት ዛሬም ቀጥሏል። የንግድ እና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ተቋርጦ ውሏል። ከተማዋ በፀጥታ ሃይሎች በከፍተኛ ደረጃ እየተጠበቀች ነው።
.
.
ዛሬ በስራ ላይ የሚውለውን የነዳጅ ዋጋ መጨመር ተከትሎ ምንም አይነት #የትራንስፖርት_ታሪፍ  ጭማሪ #እንደማይኖር የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ገልጿል።
.
.
ጅቡቲ በተካሄደው 15ኛው የሚኒስትሮች የጋራ ኮሚሽን ስብሰባ ላይ የተካፈሉ የኢትዮጵያ ልዑካን ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያይተዋል።
.
.
በኦሮሚያ ክልል ለመንግስት ሰራተኞች #አዲስ የስራ ምደባ እየካሄደ መሆኑን የክልሉ የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታውቋል።
.
.
#ኮማንድ_ፖስቱ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 3 ወረዳዎች ላይ በቁጥጥር ስር ካዋላቸዉ 528 ተጠርጣሪዎች 440 የሚሆኑትን በነፃ አሰናብቷል።
.
.
የአዋሽ ወልድያ ሃራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት የመጀመሪያው ምዕራፍ የሆነው ከአዋሽ እስከ ኮምቦልቻ ያለው 270 ኪሎ ሜትር የባቡር መንገድ ግንባታ 97 በመቶ #መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ገልጿል።
.
.
በሱማሌ ክልል ከምሽቱ 4 ሰዓት ጀምሮ ሰዓት ዕላፊ ገደብ ተጥሏል፡፡ የአደባባይ ስብሰባም ተከልክሏል፡፡
.
.
#ቴዎድሮስ_አዲሱ(ቴዲ ማንጁስ) በ80 ሺህ ብር ዋስ ቢፈቀድለትም #በሙስና_ወንጀል ተጠርጥሮ በእስር ላይ እንደሚገኝ ተሰምቷል።
.
.
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በኩል ለሚያልፉ ዐለም ዐቀፍ መንገደኞች #የነጻ ጉብኝት መርሃ ግብር ማዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡
.
.
የኢትዮጵያ ሚዲያ ካውንስል፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ዘርፍ ማህበር እና #የሰላም_ሚኒስቴር በጋራ በመሆን የሰላም ሚዲያ ህብረት ትስሰር ለመፍጠር የሚያስችል ውይይት ዛሬ ማምሻውን አካሂደዋል።
.
.
የሐረሪ ክልል የሰላምና ጸጥታ ሁኔታ #መሻሻል ማሳየቱን የክልሉ ፍትህና ጸጥታ ጉዳይ ቢሮ  አስታውቋል።
.
.
#ብሄሬን መሰረት ተደርጎ ጥቃት ተፈፅሞብኛል በሚል በሀሰት የሽንት መሽኛ #ብልቱን በፋሻና ፕላስተር በመጠቅለል ግጭት ለመቀስቀስ የሞከረው ግለስብ ድሬ ፖሊስ በቁጥጥር ስር አውሏል።
.
.
በአዲስ አበባ ከተማ በዳቦ ላይ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ አግባብነት የሌለውና ህብረተሰቡን ያላማከለ ነው ሲሉ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
.
.
በሺህዎች የሚቆጠሩ ቤተ እስራኤላውያን አንድ #ኢትዮጵያዊ በእስራኤል ፖሊስ መገደሉን በመቃወም ቴላቪቭ ውስጥ ትናንት የተቃውሞ ሰልፍ አካሂደዋል።
.
.
በአሜሪካ በተከሰተው ከፍተኛ ቅዝቃዜ እስካሁን ቢያንስ ስምንት ሰዎች #መሞታቸው ተገለጸ፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው በአሜሪካ ሜድ ዌስት የተከሰተው ቅዝቃዜ በአስር አመታት ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ አደገኛ ነው፡፡
.
.
ምንጭ፦ etv፣ የጀርመን ራድዮ፣ ኢ.ፕ.ድ.፣ ዋዜማ ራድዮ፣ fbc፣ ኢዜአ፣ bbc፣ VOA፣ የሰላም ሚኒስቴር፣ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት
.
.
ሰላም እደሩ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
#TikvahEthiopia #ቲክቫህኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አና ጎሜዝ🔝

ሁሉም #ኢትዮጵያዊ ለሀገሩ አስተዋጽኦ ስላለው አንዱ የበላይ አንዱ የበታች ነኝ ብሎ ማሰብ እንደሌለበት #አና_ጎሜዝ ተናገሩ። በኢትዮጵያ በ1997 ዓ/ም በተደረገ ምርጫ ታዛቢ የነበሩት አና ጎሜዝ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ስለአንድነት እንጂ ስለመከፋፈል ማሰብ የለባቸውም ብለዋል።

የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት አባል የሆኑት ጎሜዝ አሁን ላይ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ለውጥ መጥቷልም ብለዋል። ይሁንና በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ግጭቶች ሚሊዮኖች #እንዲፈናቀሉ አድርገዋል ብለዋል። አና ጎሜዝ ኢትዮጵያውያን አንድነት ላይ ከሰሩ ሁሉንም ነገር ማድረግ እንደሚችሉ ዕምነት እንዳላቸው ገልጸዋል።

ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UpdateSport በበርኒግሀም የቤት ውስጥ ሩጫ ውድድር በሴቶች 3 ሺህ ሜትር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንደኛ እስከ አራተኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀቁ፡፡ በዚህም #አልማዝ_ሳሙኤል በ8 ደቂቃ 54 ሰከንድ 60 ማይክሮሰከንድ አንደኛ ደረጃን በመያዝ  አጠናቅቃለች፡፡ #አክሱማዊት_እምባየ በ8 ደቂቃ 54 ሰከንድ ከ97 ማይክሮሰከንድ እና #መስከረም_ማሞ በ8 ደቂቃ ከ55 ሰከንድ ከ03 ማይክሮሰከንድ በመግባት ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል፡፡ ሌላኛዋ #ኢትዮጵያዊ አትሌት #እጅጋየሁ_ታየ በ8 ደቂቃ ከ55 ሰከንድ ከ28 ማይክሮሰከንድ በመግባት የአራተኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቅ ችላለች፡፡

Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጉዞ ሉሲ~ለሰላምና ለፍቅር!

‹‹ጉዞ ሉሲ ለሰላምና ለፍቅር መርሀ-ግብር›› ትላንት ምሽት በሚሊኒዬም ተጀምሯል፡፡ በዝግጅቱ መክፈቻ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኢፌዴሪ ባሕልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር #ሂሩት_ካሰው ‹‹ዘረኝነት፣ መለያዬት፣ ማግለልና ንፉግነት የኛ የኢትዮጵያዊነት ባሕል አይደለም፡፡ ከዛሬ ጀምሮ የነበረንን መተዛዘን፣ #ፍቅርና #አንድነት ወደ ነበረበት እንዲመለስ ለውጥ የሚጀምረው ከራስ ነውና ለለውጥ እዘጋጃለሁ፤ ለለውጥ እንዘጋጅ›› በሚል #የአንድነት ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡

በመርሀ-ግብሩ ከአፋር ክልል ጀምሮ በተለያዩ ክልሎች ሉሲ የአምስት ቀናት ቆይታ እያደረገች ሕዝቡ #በአንድነቱ ዙሪያ እንደሚወያይ የገለጹት ሚኒስትሯ ‹‹ሉሲንና ሌሎች አንድ የሚያደርጉን በዩኔስኮ የተመዘገቡ ቅርሶችን በታላቅ ክብር ከብሔራዊ ሙዚዬም ወደ ፓርላማ አጓጉዘን ወደ አፋር በመሸኘት ይጀመራል›› ነው ያሉት፡፡

ሉሲ የእገሌ የሚባል ሃይማኖት፣ ብሔር፣ አስተሳሰብ ወይም ሌላ #ወካይ_ያልሆነች የሁሉም የሰው ዘር ግንድ መሆኗን የጠቀሱት ሚንስትሯ ‹‹ደግነትና አብሮነት ስላልተለየን በጎ ትሩፋት ሳይሠራ የሚውል #ኢትዮጵያዊ የለም፡፡ የትኛውም ኢትዮጵያዊ የተራበ ሳያበላ፣ የተጠማ ሳያጠጣ፣ የወደቀ ሳያነሳ፣ የሞተ ሳይቀብር አይውልም፤ ኢትዮጵያዊነትም ይህ ነው›› ብለዋል፡፡ እንኳን እርስ በእርስ ከሌላውም ዓለም ጋርም ኢትዮጵያዊ በሉሲ የተዛመደ መሆኑንና #ዘረኝነት የኢትዮጵያዊነት ባሕል አለመሆኑን ነው ዶክተር ሂሩት ያስገነዘቡት፡፡

በመርሀ-ግብሩ መክፈቻ ዝግጅት በአዲስ አበባ ሚሊኒዬም አዳራሽ አንጋፋና ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ዝግጅቶቻቸውን አቅርበዋል።

Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ታዳሚውን ያስለቀሰው የብሩክ የሺጥላ ንግግር...

"ከዛሬ ጀምሮ ይህቺ ምደገፍባት ነገር አታስፈልገኝም ለምን መሰላችሁ ሲደክመኝ ሚደግፈኝ #ኢትዮጵያዊ_ወንድም አለኝ፤ ሲርበኝ አይዞህ ብሎ የሚያበላኝ እህትና ወንድም አለኝ፤ እኔ ማውቃት ኢትዮጵያ ይህቺን ነው፤ እኔ #የኖርኩባት ኢትዮጵያ ይህቺ ነች፤ ልጄም ይህንን እውነት እንዲኖረው እፈልጋለሁ፤ #ልጆቻችንም ይሄንን እውነት የሆነ ኢትዮጵያ ኖረው እንዲያልፉ ሁሉንም ነገር #እናመቻችላቸው፤ ችግርን ከመፍጠር ይልቅ ብዙ ችግሮች አሉብን ስለ ችግሮቻችን ካወራን ችግሮቻችን አያልቁም። መሪዎቻችን ደግሞ ገና #በተመቻቸ ሁኔታ ላይ አይደሉም፤ እነሱ ላይ ብዙ ችግር አንፍጠርባቸው፤ እኛ የምንችለውን ችግር እንፍታ እነሱም ደግሞ መፍታት የሚችሉትን ያህል ችግር ይፍቱልን። የሚቀጥለው መሪ የተሻለ ወንበር እንዲያገኝ፤ የተመቻቸ ወንበር እንዲያገኝ፤ እኛንም ከዚህ በተሻለ በደንብ መምራት እንዲችል ሁሉን ነገር እኛ እናመቻችለት።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#GERD🇪🇹

"...በሚመጣው ነገር ሁሉ መስዋእትነት ለመክፈል ዝግጁ ነን" - የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት

የመከላከያ ሰራዊት አባላት የታላቁ ህዳሴ ግድብ 2ኛ ዙር ሙሌት እንዲሁም አጠቃላይ ስራው እስኪጠናቀቅ ድረስ አስፈላጊውን መስዋእትነት ለመክፈል መዘጋጀታቸውን ገለፁ።

የሰራዊቱ አባላት ይህን ሲገልፁ የተሰማው ሀገር መከላከያ ባሰራጨው የ1 ደቂቃ ከ50 ሰከንድ ርዝማኔ ባለው ቪድዮ ላይ ነው።

የመከላከያ አባላት የግድቡ ስራ ለሰከንድም ሳይቆም ይሰራል፣ ሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌትም ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።

"እኛ በህይወት እስካለን የግድባችን ስራ ለሰከንድ አይደናቀፍም" ብለዋል።

ሁሉም #ኢትዮጵያዊ ከጫፍ ጫፍ ሆ ብሎ በመነሳት የገነባው ግድብ መሆኑን የተናገሩት የሰራዊቱ አባላት ስራው እስኪጠናቀቅ ድረስ ለሚመጣው ነገር ሁሉ ቀድመን መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነን በዚህም ህዝቡ በምንም መልኩ ሊጠራጠር አይገባም ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ተጨማሪ ማዕቀብ እንዲጣል አዘዙ። የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከትግራይ ክልል ቀውስ ጋር በተገናኘ ተጠያቂ ባደረጓቸው ፦ - የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት - የአማራ ክልል ባለስልጣናት - የህወሓት አመራሮች - የኤርትራ መንግስት አመራሮች ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ እንዲጣል አዘዙ። ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ዛሬ በፈረሙት የስራ አስፈጻሚ አካል ትዕዛዝ (executive order) የትግራይ…
#DrAbiyAhmed #JoBiden

የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ለአሜሪካው ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ግልፅ ደብዳቤ ✉️ ፃፉ።

ዶክተር ዐቢይ አህመድ ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በፃፉላቸው ግልፅ ደብዳቤ በአሁን ሰዓት በኢትዮጵያ 🇪🇹 ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ ፥ ሕወሓት በአፋርና አማራ ያፈናቀላቸው ንፁሃን ዜጎች በከፋ ችግር ውስጥ ወድቀው እንደሚገኙ የገለፁ ሲሆን ቡድኑ ቤተሰቦቻቸውን እንደገደለባቸው እንዲሁም የአገልግሎት መስጫ ተቋማትን ጨምሮ ንብረት እንዳወደመ አስረድተዋል።

በኢትዮጵያ ላይ እየደረሱ ያሉ የውጭ ጫናዎች ተገቢ አለመሆናቸውንም አሳውቀዋል።

ዶ/ር ዐቢይ ፥ በቅርቡ የተመሰረተው አዲሱ የባይደን አስተዳደር ከዚህ ቀደም ከነበረው የተሻለ እንደሚሆን ኢትጵያውያን ተስፋ እንደነበራቸው አውስተዋል።

አሜሪካ ሌሎች ሃገራት ላይ በነበራት የተሳሳተ የውጭ ፖሊሲ በሃገራቱ ላይ ያስከተለውን ቀውስ አስታውሰዋል፡፡

ኢትዮጵያ 🇪🇹 ተስፋ በቆረጡ እና ስልጣን ከሚሊዮኖች ደህንነት በላይ በሚያሳስባቸው ግለሰቦች አትሸነፍም ሲሉም ገልጸዋል፡፡ #ኢትዮጵያዊ እንዲሁም #አፍሪካዊ ማንነታችን እንዚህ ግለሰቦች እንዲያሸንፉ አይፈቅድልንም ብለዋል፡፡

@tikvahethiopia
#Kenya

የኬንያ ፖሊስ 41 ኢትዮጵያውያንን ናይሮቢ ውስጥ በቁጥጥር ስር መዋሉን ገለፀ።

ግለሰቦቹ ወደ ደቡብ አፍሪካና ሌሎች አገራት ለመዘዋወር በአንድ ቤት ውስጥ ለአራት ቀናት ያህል ሲጠባበቁ ሰኞ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም መያዛቸውን ገልጿል።

ኢትዮጵያውያኑን በሕገ ወጥ መንገድ ሊያዘዋውሩ ነበሩ የተባሉ ሁለት አዘዋዋሪዎችም በዚሁ አጋጣሚ የተያዙ ሲሆን አንደኛው #ኢትዮጵያዊ መሆኑም ፖሊስ አሳውቋል።

ፖሊስ ጥቆማ ደርሶት በቁጥጥር ሥር ያዋላቸው እነዚህ የሕገ ወጥ ሰዎች አዘዋዋሪዎች በአገሪቱ ውስጥ ካሉ ሌሎች በርካታ ዝውውሮች ጀርባ እንዳሉበት ተገልጿል።

ኢትዮጵያውያኑ በዚህ ሳምንት ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን ወደ ኬንያ እንዴት እንደገቡ ተጨማሪ ምርመራ እስኪደረግ ድረስ ለተጨማሪ ስድስት ቀናት በእስር እንዲቆዩ መታዘዙን #ቢቢሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፤ በ2014 ዓ.ም እና 2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው የትምህርት ሚኒስቴር ያወጣውን የዩኒቨርስቲ መግቢያ መቁረጫ ውጤት ያመጡ እና በፖሊስ የሙያ ዘርፍ ሀገራቸውን ለማገልገል #የሚፈልጉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር እንደሚፈልግ አሳውቋል።

ተቋሙ ለ4  አመታት በ " ፖሊስ ሳይንስ ዲግሪ " አስተምሮ በመኮንንነት (ረዳት ኢንስፔክተር ማዕረግ) በማስመረቅ በተለያዩ የፌደራል ፖሊስ የስራ ክፍሎች አስመድቦ ለማሰራት እንደሚፈልግ ነው የገለፀው።

በተጨማሪ በ "ፎረንሲክ ሳይንስ ዲግሪ" አስተምሮ በመኮንንነት (ረዳት ኢንስፔክተር ማዕረግ) በማስመረቅ በፎረሲክ ምርመራ የላብራቶሪ ሙያተኝነት (ኤክስፐርት) በማስመደብ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡

በተቋሙ በ  " ፖሊስ ሳይንስ ዲግሪ " ለመማር የሚያስፈልጉ የመመልመያ መስፈርቶች ከላይ በምስሉ የተዘረዘሩ ሲሆን ከነሱም ውስጥ ፦

- አመልካቾች ከማንኛውም ወንጀል ነፃ ስለ መሆኑ ከሚኖርበት ወረዳ ፖሊስ ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው።

- ለፖሊስ አካል ብቃት ስልጠና ብቁ የሆነ አካላዊ አቋምና አዕምሮ ጤንነት ያላቸው ሊሆኑ ይገባል።

- በ2014 ዓ/ም እና 2015 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባ የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስተር መቁረጫ ውጤት ያላቸው  የትምህርት ማስረጃቸውንም ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።

- የ #ሪሚዳል_ትምህርት ወስደው የማለፊያ ውጤት ያመጡ ከሆነም ማስረጃ ማቅረብ አባቸው።

- አመልካቾች እድሜያቸው ከ18 እስከ 28 ዓመት መሆን አለበት።

- ቁመት ለወንድ 1.65 እና ከዚያ በላይ፣ ለሴት 1.55 እና ከዚያ በላይ፣
ሲሆን የተስተካከለ የሰውነት ክብደት 18.5-24.9 kg/m) ያለቸው ሊሆኑ ይገባል።

- ከተመረቁ በኋላ 7/ሰባት/ አመት በተማረበት የፖሊስ ሙያ በየትኛውም የአገሪቱ ክልልና የፖሊስ የስራ መደቦች ላይ ተመድቦ ለመስራት ፍቃደኛ መሆን አለበት።

- ሴት አመለካቾች ከእርግዝና ነፃ መሆን አለባቸው።

- ሁሉም አመልካቾች ከዚህ በፊት የፖሊስ ወይም የመከላከያ ሰራዊት ስልጠና ያልወሰዱ መሆን ያለባቸው ሊሆኑ ይገባል።

ለ " ፎረንሲክ ሳይንስ ዲግሪ " ከላይ ያሉት አብዛኛው መስፈርቶች እንደተጠበቁ ሆነው ፦
- ዜግነት #ኢትዮጵያዊ
- የ12ኛ ክፍል #በተፈጥሮ_ሳይንስ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው በ2014 ዓ/ም እና በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ያወጣውን መቁረጫ ውጤት ያላቸው
- በተፈጥሮ ሳይንስ የሪሚዳል ትምህርት ወስደው የማለፊያ ውጤት ያመጡና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ሊሆኑ ይገባል።

በሁለቱም የዲግሪ ትምህርት ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲውን የሚቀላቀሉት በራሱ በተቋሙ የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና ማለፍ ሲችሉ ብቻ ነው።

የት እና እስከመቼ መመዝገብ ይቻላል ?

ማመልከት የሚቻለው እስከ ጥቅምት 22/2016 ዓ/ም ድረስ ባሉት ተከታታይ የስራ ቀናት ነው።

ተማሪዎች በአካባቢያቸው በሚገኝ በሁሉም የክልል እና የከተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽኖች በአካል በመገኘት መመዝገብ ይችላሉ።

ለመዝገባው የትምህርት ማስረጃቸውን የ8ኛ ፣ የ10ኛና 12ኛ ክፍል ካርድ እና ትራንስክርፕት ኦርጅናል ከማይመለስ አንድ ፎቶ ኮፒ ጋር ይዘው መቅረብ አለባቸው።

#ደመወዝ / #ክፍያን በተመለከተ

ዕጩ መኮንኖች በትምህርት ላይ በሚቆዩበት ጊዜያት ከ3 ወር የሙከራ (recruit) ጊዜ ቆይታ በኋላ እስከሚመረቁ ድረስ የኪስ ገንዘብ/ደመወዝ ታስቦ ይከፈላቸዋል ተብሏል።

ስልክ ካስፈለጋችሁ ፡ 0116735564

(ተጨማሪ ዝርዝር ጉዳዮችን ከላይ በምስሉ ያንብቡ)

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

" የ2024 ESP ማመልከቻ ማስገባት ይቻላል " - የአሜሪካ ኤምባሲ በኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ የEducation USA Scholars Program (#ESP) 2024 ማመልከቻ ክፍት መሆኑን አሳውቋል።

ESP በአካዳሚክ ጠንካራ የሆኑ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ወደ አሜሪካ ኮሌጆች እና ዩኒቨርሲቲዎች #እንዲያመለክቱ የሚረዳ የአራት ሳምንታት የሥልጠና መርሃ ግብር ነው።

ዓላማውም ደግሞ የነገዋን ኢትዮጵያ ለመገንባት የሰለጠኑ እና ከፍተኛ የትምህርት ዝግጅት ያላቸውን መሪዎችን ማፍራት እንደሆነ ኤምባሲው አመልክቷል።

ከአመልካቾች 20 ከፍተኛ የአካዳሚክ ብቃት ያላቸውን ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በኤምባሲው ይለያሉ። ተማሪዎቹ በአካዳሚክ ሪከርዳቸው፣ እንዲሁም በኢንተርቪው እንዲለዩ ይደረጋል።

ከጠቅላላው 20 የመጨረሻ እጩዎች መካከል፣ 15 ከፍተኛ ብቃት ያላቸው፣ በኢኮኖሚ የተቸገሩ ተማሪዎች ከመደበኛ ፈተናዎች፣ ከአሜሪካ ቪዛ ክፍያ ጋር የተያያዙ ወጪዎችን በሚሸፍነው የOpportunity Program Fund (#OPF) ፕሮግራም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይመረጣሉ።

የመጀመሪያዎቹ ጥቂት ስኬታማ ዕጩዎች ወደ አሜሪካ የራውንድ ትሪፕ ትኬት ያገኛሉ።

ቀሪዎቹ 5 ተማሪዎች በስልጠና ፕሮግራሙ ላይ #በነጻ ይሳተፋሉ ነገር ግን የዝግጅት ወጪን ከራሳቸው ምንጭ ይሸፍናሉ። የሞባይል ዳታ ወጪዎች ለሁለቱም የፕሮግራም ተሳታፊዎች በኤምባሲው ይሸፈናሉ።

ማመልከቻ እስከ ሚያዚያ 10/2024 (5:00 pm EAT) ማስገባት ይችላል ተብሏል።

ለማመልከት አስፈላጊ መስፈርቶች ምንድናቸው ?

ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩና ትምህርታቸውንም እዚሁ ኢትዮጵያ እየተከታተሉ ያሉ።

ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበ/ች #ኢትዮጵያዊ ተማሪ፣

በዚህ የትምህርት አመት መጨረሻ 11ኛ ክፍልን ያጠናቅቁ እና ከመስከረም 2024 ጀምሮ 12ኛ ክፍል የሚማሩ፣

በጠቅላላ 4 ሳምንታት የESP መርሃግብር ለመሳተፍ ቃል መግባት የሚችሉ መሆን አለባቸው።

ስታመለክቱ የሚያስፈልጉ ፦
1ኛ. የሁለተኛ ደረጃ ትራንስክሪፕት (9፣ 10፣ 11)
2ኛ. ከትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ
3ኛ. የኢኮኖሚ ችግር ያለባቸውና ለOpportunity Fund Program (OFP) የሚያመለክቱ ከትምህርት ቤት ወይም ከቀበሌ የቤተሰብን #ዝቅተኛ የኢኮኖሚያ ሁኔታ የሚያረጋግጥ ደብዳቤ ማቅረብ ያስፈልጋል።

የማመልከቻ ሊንክ እና ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ በዚህ ይመልከቱ ፦ https://sites.google.com/amspaceseth.net/educationusa-esp2024

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ

ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች አንድ አባት  በጎረምሶች ተከበው ሲመቱ ፣ ሲሰደቡ ፣ ሲዘለፉ ፣ ሲዋከቡ በቪድዮ ታይቷል።

ይህን እጅግ አሳፋሪና በምን አይነት ሁኔታ ላይ እንዳለን ሚያሳይ ቪዲዮ ያጋሩት ደግሞ እራሳቸው የድርጊቱ ፈጻሚዎች ናቸው።

ድርጊቱ ብዙዎችን ክፉኛ አስቆጥቷል። በርካቶች ስለ ነገ በማሳብ ፍርሃት ውስጥ ከቷቸዋል።

በእርግጥ በሀገራችን ያላየነው ግፍ ፣ ያልሰማነው ክፉ ተግባርና ጭካኔ ምን አለ ? እንዘርዝር ብንልስ ቦታው፣ ጊዜው  ይበቃናል ? በፍጹም !

ከዚህ በፊትም እንደምንለው በቪዲዮዎች ተቀርጾ የምናየው ምናልባትእድለኞች ሆነን ከብዙ አንዱ እንጂ ስንት ያላየነው ይኖራል።

ወደ ቪድዮው ስንመለስ ተከበው ሲመቱ፣ ሲዋከቡ ፣ ሲዘለፉ የነበሩት አባት ' እንጀራ ፍለጋ እግር ጥሏቸው እንደመጡ ' ይገልጻሉ የሚጠይቀን የለም ባዮች ጎረምሶች ' እዚህ አካባቢ ምን ትሰራለህ ? ለምን እዚህ መጣህ ? ከመጣህበት ቦታስ እንጀራ የለም ? ' ሲሉ እጅግ በንቀት ያዋክቧቸዋል።

ይህን ተግባራቸውን እንደ በጎ ስራ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ አጋርተውታል።

የትኛውም ዜጋ በገዛ ሀገሩ የመንቀሳቀስ መብት አለው ? ካልሆነ ስለምን #ኢትዮጵያዊ ይባላል ? ጥፋት ካለበት ፣ ከተጠረጠረ የሚጠይቀው ህግ እንጂ የሰፈር ጎረምሳ አይደለም። ግለሰቦቹ ጥርጣሬ አለን ካሉ ህግን ማሳወቅ እንጂ ማነው ፤ የትኛው ህግ ነው ይህንን መብት የሰጣቸው ? 

ይህ ተግባር በተለይ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየተነዛ ያለው የጥላቻ ስብከት ምን ያህል ስር እንደሰደደ እንደሆነ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ሲሆን ነገን እጅግ አስፈሪ ያደርገዋል።

ግልጽ የሆነ የብሄርና የግለሰቦች ጥላቻ ፣ ልብም አእምሮም በጥላቻ መሞላት፣ አይንም በጥላቻ መታወር ፦
- ሌላው ይቅር ታላላቆቻችን እንዳናከብር
- ለእምነታችን ፣ ለሃይማኖታችን ቦታ እንዳይኖረን
- ለሰው ልጅ ትንሽ እንኳን ቦታ እንዳንሰጥ
- ለህግ እና ስርዓት ቅንጣት ታክል ደንታ እንዳይኖረን
- ባህል፣ ወግ ፣ አብሮነት ለሚባለው ጉዳይ ቦታ እንደሌለን
- ነገ እኔስ ምን ይገጥመኛል ? ምን እሆን ይሆን ? በህይወት አጋጣሚ የት እሄዳለሁ ፣ ምን አካባቢ እገኛለሁ የሚለውን ለማገናዘብ እንኳን እንዳንችል ያደርገናል።

ሰዎች ወደው ሳይሆን በስርዓት፣ በግለሰቦች፣ በአንቂዎች ፣ በሚዲያዎች... አማካኝነት ነው ጥላቻ እንዲውጣቸው እና ማገናዘብ ፣ ቆም ብሎ ማሰብ የሚባለውን መሰረታዊ ነገር እንዲያጡት የሚሆነው።

ሰዎች ከመሰል ድርጊታቸው እንዲታቀቡ አብሮነት ፣ ፍቅር ፣ መግባባት፣ መከባበር ፣ ህግ ፣ ስርዓት፣ ወንድማማችንነትን ከማስተማር ባለፈ በህግ ማረም ፣ ነገ መዘዙ የከፋ እየሆነ ስለሚሄድ ከወዲሁ እንዲገታ በአንድ ላይ ማውገዝ ፣ ተበዳይን መካስ ፣ እውነት ህግ የበላይ ነው የምንል ከሆነም ለራሳችን ስንል ህግን ሁሌም ማስከበር ነው።

ዛሬ ላይ እንዲህ ያሉና ከዚህ ቀደምም በየሀገሪቱ ክፍሎች የሰማናቸው ፍጹም አደገኛ የሚባሉ ጉዳዮች የሳምንት አጀንዳ እየሆኑ እያለፉ ይመስለን ይሆናል ግን በእርግጠኝነት መዘዛቸው የከፋ ሊሆን ይችላል።

ውጤታቸው ዛሬ ሳይሆን ውሎ አድሮ ምናልባትም አመታትን አልፎ ይታይ ይሆናል ስለሆነም እናስብበት ! ትውልዱን ከስህተቱ እናርመው ፤ ወገኑን እንዲጠላ ሳይሆን እንዲወድ ፣ እንዲያከብር እናስተምረው።

በሁሉም ዘንድ አውቀናል ታውቀናል ፣ ዛሬ ስልጣን አለን፣ ሚዲያውም የኛው ነው የምንል ሰዎችም ' አይ የኔ ወገን ስለሆነ ፍጹም ጻዲቅ ነው ፣ አይሳሳትም ፣ ጀግና ነው ፣ ቢሳሳትም ምንም ችግር የለውም እኔ እከላከልለታለሁ ' ከሚል አደገኛ እና ብዙ መዘዘ ካለው አመለካከት መራቅ ይገባናል።

#TikvahFamily
#Ethiopia

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

ገንዘብ ለማግኘት ሲሉ ብቻ ምንም ሳይታመሙ " ታመናል " ወይም ልጃቸው / ቤተሰባቸው ሳይታመም እንደታመመ አስመስለው እርዳታ የሚጠይቁ ሰዎች በትክክል ሊረዱ የሚገባቸው ሰዎችን እንዳይረዱ ያደርጋሉ።

ከዚህ ቀደም በውሸት ገንዘብ በእርዳታ መልክ ሲሰበስቡ ስለተያዙ ሰዎች መረጃ መለዋወጣችን አይዘነጋም።

ትላንት ደግሞ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጤናማ ልጁን " የካንሰር ህመምተኛ ነው " በማለት ሲለምንበት የተገኘ ወላጅን እና ግብረ-አበሩን ይዞ ምርመራ እያጣራ መሆኑን አሳውቋል።

በወንጀሉ የተጠረጠረው አባት (ጃዋር አብዱላሂ) ልጁን የካንስር ህመምተኛ በመሆኑ ለማሳከም ከአዋሽ 7 ወደ አዲስ አበባ መምጣቱንና ልጁን ለማሳከም እና ለምግብ እንዲሁም ለማደሪያ መቸገሩን በመግለፅ ከግብረ-አበሩ (አህመድ ከሊፈ) ጋር በመሆን በአ/አ በተለያዩ ቦታዎች ሲለምን ቆይቷል።

ትላንት ግን አንድ የፖሊስ አባል ነገሩን ተጠራጥሮ የህክምና ማስረጃ ሲጠይቃቸው ማሳየት አልቻሉም።

ፖሊስም ይዞ ፖሊስ ጣቢያ አስገብቷቸዋል።

የህፃኑ አባት እና ግብረ አበሩ ልጁ ታማሚ እንዲመስል አንገቱ ላይ ፕላስተር ለጥፈውበት የነበረ ሲሆን ፕላስተሩ ሲነሳ አንገቱ ላይ ምንም ቁስል የለም።

ህፃኑ በፖሊስ ጣቢያ  ሲጠየቅ ጤነኛ መሆኑን ገልጿል።

#ኢትዮጵያዊ የተቸገረን ሰው መርዳት ባህሉ ነው፤ ካለው ሰው ሲለምነው ጥሎ መሄድን አያውቅም ፤ ነገር ግን በውሸት / በማጭበርበር የሚካሄድ ተግባር እውነተኛ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች እንዳይረዱ ያደርጋል።

እርዳታ ሲሰጥ የህክምና ማስረጃዎች መጠየቅ ይገባል።

@tikvahethiopia