TIKVAH-ETHIOPIA
1.42M subscribers
55.2K photos
1.38K videos
199 files
3.7K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #Ethiopia #Sudan " መረጃው ውሸት ነው " - ዶ/ር ለገሰ ቱሉ " በእግረኛ የሚመጡ ከሆነ የአካባቢው ታጣቂ በተጠንቀቅ ቆሟል " - አቶ አብራራው ተስፋ " ሱዳን ትሪቡን " የተባለው የሱዳን ሚዲያ የሱዳን ጦር ሰራዊት ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ኃይሎች ተወሰደብኝ ያለውን እርምጃ ለመበቀል የይገባኛል ጥያቄ በሚናሳበት የአልፋሽጋ አካባቢ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ስር የነበሩ " ካላ…
#Update

ከ1 ወር በፊት ተዘግቶ የነበረው የጋላባት ድንበር ተከፈተ።

ሱዳን ከ1 ወር በፊት ዘግታው የነበረውን እና ከኢትዮጵያ የሚያዋስናትን ቁልፍ የድንበር በረ ከፍታለች።

ሱዳን ድንበሩ የተከፈተው ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ገንቢ የሆነ ውይይት ከተደረገ በኋላ ነው ብላለች።

ከአንድ ወር በፊት ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር በሚያወስነኝ አካባቢ በተፈጸመ ጥቃት የጦር አባላቶቼ ተገድለውበኛል ስትል ክስ ማሰማቷ ይታወሳል።

ሱዳን በኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት ተፈጽሟል ባለችው ጥቃት 6 ወታደሮቿ እና አንድ ሲቪል መገደሉን ገልጻ ነበር።

የኢትዮጵያ መንግሥት/የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በሰዎች ህይወት መጥፋት ሀዘን እንደተሰማው ገልጾ ነገር ግን በሱዳን የተሰራጨው መረጃ ትክክል እንዳልነበር መግለፁ ይታወሳል።

በመጀመሪያ ደረጃ በቦታው በነበረው ግጭት የአገር መከላከያ ሠራዊት ተሳትፎ እንዳልነበረው የተገለፀ ሲሆን ጉዳቱ ያጋጠመው ደግሞ እራሳቸው የሱዳን ኃይሎች የኢትዮጵያን ድንበር ጥሠው አልፈው ከገቡ በኋላ ከአካባቢው ሚሊሻ ጋር በተደረገ ግጭት ነው።

አሁን የገላባት ድንበር በር እንዲከፈት የተወሰነው ድንበር ላይ ያጋጠመውን ችግር የሁለቱ አገራት መሪዎች ለመፍታት ከተስማሙ በኋላ መሆኑን ሱና የሱዳን ደኅንነት እና መከላከያ ምክር ቤት ቴክኒክ ኮሚቴን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

በድንበር አካባቢ የታጠቁ ኃይሎችን ለመቆጣጠር "በኢትዮጵያ በኩል የታየው በጎ ፍቃድ" የድንበር በሩ እንዲከፈት ምክንያት ከሆኑት መካከል አንዱ መሆኑ ተገልጿል።

ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና የሱዳኑ መሪ ሌ/ጄኔራል አብደል ፋታህ አል ቡርሐን ከሳምንታት በፊት ለኢጋድ ስብሰባ በኬንያ በተገኙበት ወቅት ስለሁለቱ ሀገራት እና ቀጠናዊ ጉዳዮች የጎንዮሽ ውይይት ማድረጋቸው አይዘነጋም። #ሱና #ቢቢሲ

@tikvahethiopia