الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
21.8K subscribers
374 photos
17 videos
7 files
913 links
﴿وَمِنْ آيَاتِهِ أَنْ خَلَقَ لَكُم مِّنْ أَنفُسِكُمْ أَزْوَاجًا لِّتَسْكُنُوا إِلَيْهَا وَجَعَلَ بَيْنَكُم مَّوَدَّةً وَرَحْمَةً﴾

ለማንኛዉም አስተያየት☞☞ @Tidarbaislam_bot
ለይ ያድርሱን

ለጥያቄ ☞☞ t.me/Hayatbintkedir
Download Telegram
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
☞:::ትዳር በኢስላም::::☜ #ክፍል_ሀያ_አንድ/②① 2#አንድ_ወንድ_ከአንድ_በላይ_የሚያገባ_ከሆነ_በእያንዳንዱ_ቤት_ያለው_ቤተሰብ_አንዱ_ለሌላው_የጠላትነት_ስሜት_እንድኖር_ያደርጋል_ይላሉ #መልስ፣ በመሰረቱ ይህን ሙስሊም የሚባሉትም ሰዎች እንደሚያነሱ አሳልፈናል። ይህ ሁሉ ፈር የለቀቀ አስተሳሰብ ኢስላምን በቅጡ ካለመረዳት የመነጨ ነው።በመካከላቸው አንድ የሚያደርጋቸው አባት መኖሩ በሁሉም ቤተሰብ ውስጥ…
=>ትዳር~በኢስላም

    
#ክፍል_ሀያ_ሁለት/②②ት

#የነብዩ_ሰአወ_ከአንድ_በላይ_ሚስት_የማግባታቸው_ጥበብ

    ነብዩ ﷺ ቁጥብ እና ንፁህ ሆነው ለሀያ አምስት አመታት ከቆዩ በኃላ በ15 አመት የምትበልጣቸውን እናታችን ኸዲጃን አግብተው በርካታ ልጆችን ከእናታችን ለመውለድ የቻሉ ሲሆን ሌላ ተጨማሪ ሚስት ሳያገቡ ከኸዲጃ ጋር የወጣትነት ጊዜያቸውን በማሳለፍ ለ23 አመት በፍቅር እና በሰመረ ህይወት አብረው ቆይተዋል።ማለትም እድሜያቸው 48 አመት እስኪሆን ድረስ ሌላ ባል ፈታ ከአገቧት እናታችን ኸዲጃ ጋር ታላቅ የሆነ የትዳር ህይወትን ኑረዋል። የአላህ ውሳኔ ደረሰና ከተጋቡ ከ23 አመት በኃላ ያቺ የኢስላም ታላቅ ባለውለታ የነብዩﷺየጭንቅ ቀን ጓደኛ የሆኑት እናታችን ኸዲጃ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ! ኸዲጃ በመሞታቸው ነብዩ ሰአወ በጣም አዘኑ።

   እናታችን ኸዲጃ  ከሞቱ በኃላ ነብዩ ﷺ ልጆቻቸውን እንደልጅ አድርጋ የምትይዝ በእድሜያቸው የገፉትን እና ባላቸውን በሁለተኛው የሀበሻ ስደት በሞት ያጡ እና ያለታዛቢ የቀሩትን የ55 አመት አዛውንት እናታችን ሰውዳን  አገቡ።አንድ መረሳት የሌለበት መሰረታዊ ነጥብ የነብዩ ﷺእድሜ 53 በሆነበት ጊዜ ታላላቅ የኢስላም ህግጋቶች የተደነገጉበት ሰአት ነበር።ልብ በሉ ነብዩ ﷺ ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት በታዘዙበት ሰአት ሶስት ወሳኝ ነገሮች አብረው በተጓዳኝ ነበሩ።

1) በጊዜው ሙስሊም ወንዶች ወደ ጀሀድ እንዲሄዱ የታዘዙበት፣
2) ነብዩ ﷺአብዛኛውን ሌሊት በመቆም እንድያሳልፉ የታዘዙበት ነበር።
3) ከሚስቶች ጋር ቁጭ ብሎ ለመጫወት ብዙ ረፍት የማያገኙበት እና የወጣትነት ጊዜያቸውን ካለፈ ወይም እድሜያቸው 53 ከሆነ በኃላ ነው።

     ☞ በዚህ ሰአት ነብዩ ﷺ የተወሰኑ ሚስቶችን አግብተዋል ነገር ግን ሙስሊሞች ከነበረባቸው ኢስላምን የበላይ የማድረግ ስራ ግቡን ከመታና የሙስሊሞች ሰራዊት ተጠናክሮ የወንዶች ሞት ከቀነሰ በኃላ ሌላ አዲስ ሚስት እንዳያገቡ አላህ በእርሳቸው ላይ እርም አደረገ። በቁርአኑም እንዲህ ይላል፣

لَّا يَحِلُّ لَكَ النِّسَاءُ مِن بَعْدُ وَلَا أَن تَبَدَّلَ بِهِنَّ مِنْ أَزْوَاجٍ وَلَوْ أَعْجَبَكَ حُسْنُهُنَّ إِلَّا مَا مَلَكَتْ يَمِينُكَ ۗ وَكَانَ اللَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ رَّقِيبًا

ከእነዚህ በኋላ እጅህ ከጨበጠቻቸው (ባሮች) በስተቀር ሴቶች ለአንተ አይፈቀዱልህም፡፡ ከሚስቶችም መልካቸው ቢደንቅህም እንኳ በእነርሱ ልታላውጥ (አይፈቀደልህም)፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ ተጠባባቂ ነው፡፡
(ሱረቱ አል- አሕዛብ - 52)

    ይህን የቁርአን አንቀፅ ልብ ብሎ ያስተዋለ ሰው የነብዩ  ﷺ ከአንድ በላይ
#የማግባታቸው_ጥበብ በትክክል ይረዳል። ነገር ግን የኢስላም ጠላቶች ከእውነት የራቀ ቅጥፈት በነብዩ  ﷺ ላይ ሲቀጥፉ መስማት ከህመም በላይ ህመም ነው።ከአንድ በላይ የሆኑ ሚስቶችን እንደ እነርሱ ቅጥፈት "ያገባው ስሜት ለመወጣት እንጂ ለሌላ አይደለም… ………"
እና ሌላም ሌላም በጣም አፀያፊ ዘለፋ መዘለፋቸው የተለመደ ነው።እነርሱ እንደሚሉት አይነት ሰው ቢሆኑ ኖሮ ያረጀች እና በ15 አመት የምትበልጣቸውን የአርባ አመት ሴት ማግባት ለምን አስፈለጋቸው??ከእናታችን ኸዲጃ ጋር 23 አመት አብረው ሲኖሩ ለምንስ ሌላ ወጣት ሴት አላገቡባትም?? ብዙ የማግባት ሱስ ያለበት ወንድ እድሜው እርጅና ደረጃ እስከሚደርስ ድረስ እንዴት ሊያስችለው ይችላል?? እናታችን ኸዲጃ  ሲሞቱ እርጅና ውስጥ ገብተው 63 አመት  ሞልቷቸው ነበር ።ነብዩ  ﷺ ያገቧቸውን ሴቶች ስንመለከት ከዘጠኙ ስምንቱ
#አግብተው_የፈቱ እና በእድሜ የገፉ አብዛኞቹ ከሀምሳ አመት በላይ የሆናቸው ነበሩ፣ ለስሜታቸው ብለው የሚያገቡ ቢሆኑ ኖሮ በእድሜ ወጣት እና አግብተው የማያውቁ ልጃ አገረዶችን ለምን ምርጫቸው አላደረጉም?? የሚስቶቻቸውን ዝርዝር ማንነት እና እያንዳዳቸውን በምን ምክንያት እንዳገቧቸው እንዲሁም የእድሜ ክልላቸውን እና መሰል ቁም ነገሮችን አላህ ከፈቀደው ወደፊት በሰፊው ይመጣል።

    ይህ በእንዲህ እንዳለ የቁረይሽ አለቆች ተሰብስበው ለነብዩ ሰአወ እንዲህ አሏቸው፣ "ንግስናን እናንግስህ ከሴቶች ቆንጆዎችን እየመረጥን እንዳርህ ይህን ወደኢስላም የምታደርገውን ጥሪህን ተው"ብለው ሲማፀኗቸው አላማቸው ሴቶችን መሰብሰብ ቢሆን ኖሮ ወይም ብዙ ሴቶች የማግባት ሱስ ያለባቸው ሰው ቢሆኑ በቀረበላቸው ግብዣ ተደስተው ከአንድ በላይ ቆነጃጅቶችን በሰበሰቡ ነበር!!!

     ⇧ ከላይ ለመጥቀስ እንደሞከርኩት የነብዩ ﷺ ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት ኡስላምን ከማስፋፋት ቀጥታ ቁርኝት ያለው
#ሂክማ_ጥበብ  ነበር።እያንዳዷ  ያገቧቸውን ሚስቶች የኒካህ አጋጣሚ ማንሳት ለግንዛቤ የሚበጅ ስለመሰለኝ በአጭሩ ለማንሳት ወደድኩ።አንባቢያንም ከታሪኩ በርካታ ትምህርቶችን እንደምታገኙ ተስፋ አለኝ።

1/
#እናታችን_ኸዲጃ_ረአ

     የእርሳቸው የትዳር አጋጣሚ ከላይ ለመጥቀስ ሞክሪያለሁ። እናታችን ኸዲጃ ሲያገቡ እድሜያቸው 40 አመት ቢሞላቸውም በእድሜ መለያየታቸው በፍቅር እና በመተሳሰብ ከመኖረወ አንዳችም ተፅዕኖ አልፈጠረባቸውም። ኸዲጃ ረአ ከዚህ አከም በሞት እስከተለዩ ድረስ በመካከላቸው አንዳችም እንከን ሳየከሰት ወርቃማ ጊዜን አሳልፈዋል።በዚህ የትዳር ህይወታቸው ነብዩ ሰአወ በኸዲጃ ላየወ አንዲትም ሴት ተጨማሪ አላገቡም!! እናታችን ኸዲጃ በሞቱበት አመት ትልቅ ድጋፍ እና እርዳታ ሲያደርጉላቸው የነበሩ አጎታቸው አቡ ጧሊብ የሞቱበት ነበር።ይህ ለነብዩ ሰአወ ትልቅ ፈተና ነበር።ያለረዳት እና አማካሪ ብቻቸውን ቀሩ።አመቱ የሀዘን አመት እየተባለ ይታወቃል።እናት የሌላቸውን ልጆች ታቅፈው ኸዲጃን ከጊናቸው አጡ።ከኢብራሂም በስተቀር ሁሉንም ልጆቻቸውን ያገኙት ከዚች ታላቅ ባለቤታቸው ነበር።

#ኢንሻአላህ_ይቀጥላል
            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam