الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
23.1K subscribers
351 photos
14 videos
7 files
905 links
﴿وَمِنْ آيَاتِهِ أَنْ خَلَقَ لَكُم مِّنْ أَنفُسِكُمْ أَزْوَاجًا لِّتَسْكُنُوا إِلَيْهَا وَجَعَلَ بَيْنَكُم مَّوَدَّةً وَرَحْمَةً﴾

ለማንኛዉም አስተያየት☞☞ @Tidarbaislam_bot
ለይ ያድርሱን

ለጥያቄ ☞☞ t.me/Hayatbintkedir
Download Telegram
☞ትዳር_በኢስላም☜

 
#ክፍል_አንድ/①

  
#ኹልዕን_በተመለከተ_በባል_እና_ሚስትመካከል_የሚፈፀሙ_ስህተቶች!!!!!

❗️
#በወንዶች_ላይ_የሚስተዋሉ_ጥፋቶች

    ኹልዕ በሸሪዓችን የተፈቀደ እና ሁሉም ሰው ያለጥላቻና ያለማመንታት ሊቀበለው ግድ ይለዋል።አንዳንድ
ወንዶች በዚህ ላይ የተለያዩ ስህተቶችን ሲፈፅሙ ይስተዋላሉ።ከፊሉ ስለዚህ ነገር ምንም እውቀቱ እና ግንዛቤው ስለሌለው ለሚስቱ ሳይመቻት ቀርቶ ሸሪዓው በሚፈቅደው መሰረት ማስለቀቂያ ከፍላ ኹልዕ ስትጠይቅ የታባሽ ብሎ ጨቁኖ ለማኖር የሚፈልግ አለ። ይቺ ሴት ችግር ኑሮባት ፍታኝ ብላ ብትጠይቀው ሸሪዓ እንደሚደግፋት ማወቅ ግድ ይለው ነበር። እያስፈራራ ሳትፈልግ በግዴታ ከኔ ጋር ኑሪ ማለት ከየት የተገኘ ሸሪዓ ነው? ይህን ቢያደርግ አላህ ፊት ተጠያቂ ነው።

     ☞ ሴቷ ወዳው እና አፍቅራው እንጂ ተገዳ እንድትኖር ኢስላም አያዝም።የሚሰራ ጉልበት አለኝ የሚናገር አንደበት አለኝ ብሎ ይቺን የአላህን ሴት ባሪያ ቢበድላት ነገ ሃያሉ ጌታችን ዚህ ትፋረደዋለች። ዛሬ ሰሚ አጥታ ብትጨቆን ነገ የፍትህ ባለቤት ናት።

    ከነብዩ( صلى الله عليه وسلم) ዘመን ጀምሮ ኢስላም ለሴቶች የሰጠው ክብር እና ዋስትና ከዚህ በፊት በነበሩት ሀይማኖቶች ያልተጠቀሰ ሆኖ እናገኘዋለን። ከነዚህ አንዱ ሴት ልጅ የማይመቻትን እና የማትወደውን ባል እርሷ  ከፈለገች ሸሪዓውን ሳትፃረር መፍታት መቻሏ ነው። ለዚህም ማስረጃው የሚከተለው አንቀፅ ነው፣

فَإِنْ خِفْتُمْ أَلَّا يُقِيمَا حُدُودَ اللَّهِ فَلَا جُنَاحَ عَلَيْهِمَا فِيمَا افْتَدَتْ بِهِ ۗ

የአላህንም ሕግጋት አለመጠበቃቸውን ብታውቁ በእርሱ (ነፍሷን) በተበዠችበት ነገር በሁለቱም ላይ ኃጢኣት የለም፡፡ (አል በቀራህ 229)

    ቡኻሪ ላይ በተዘገበው ሀዲስ የሳቢት ኢብኑ ቀይም ሚስት በማለዳ ወደ ነብዩ ሰአወ ዘንድ መጣችና እንዲህ አለች፣ "የአላህ መልክተኛ ሆይ ሳቢት በዲንም ሆነ ፀባዩ ሳካ አላወጣለትም ነገር ግን በራሴ ላይ ክህደትን እፈራለሁ(ስለምጠላው ሀቁን ባለመጠበቄ ዝቅተኛው ኩፍር ላይ ልወድቅ ስለምችል ይፍታኝ) አለች፣ የአላህ መልእክተኛ( صلى الله عليه وسلم)"
የአትክልት ቦታውን ተመልሽለታለች?" አሏት እሷም "አዎ" አለች ፣የአትክልቱንም ቦታ መለሰች።እንዲፈታትም አዘዙት።

     የቁርአን አንቀፁ እና ሀዲሱ እንደሚያስረዳው አንዲት ሴት ከባሏ ጋር እንዳትኖር የሚያግዳት በቂ ምክንያት ካላት በጉልበት አፍኖና ጨቁኖ ማኖር እንደማይቻል አበክሮ ያስተምራል።

    ☞ ❗️
#ወንዶች_አላህንፍሩ!! ኢስላም ለሰው ልጆች ሁሉ በቂ መፍትሄ የሚሰጠውን በእናንተ የግንዛቤ ችግር ሴት ልጅን የበታች አድርጎ እንደሚጨቁን አታስመስሉት።ከኢስላም ውጭ ያለው አካል ኢስላምን አያውቅም ኢስላምን የሚመዝነው በተከታዮቹ ነው። ወንዶች ሆይ፣ ዱኒያም አኼራም የተስተካከለ ይሆን ዘንድ #የነብዩ_(ሰለላሁ_ዓሌይሂ_ወሰለም) ፈለግ እግር በእግር በመከታተል ጥሩ ሞዴል ለመሆን ሞክሩ ።

ለ/
#በሴቶች_ላይ_የሚስተዋሉ ጥፋቶች❗️
   ❗️
#የሴት_ልጅ_ፍቺ_መጠየቅ የተፈቀደ ነው ሲባል ገደብ የሌለው አስመስለው እንደፈለጉ እየተነሱ #ፍታኝ_እሄደዳብላ እያሉ ባሎቻቸውን እና ቤታቸውን የሚያምሱ ሴት እህቶቻችን ቁጥራቸው እየተበራከተ መጥቷል።ከዚህም በባሰ ሁኔታ ኢስላም መፍትሄን አስቀምጦ እያለ በቁርአን መዳኘት ሲገባት አሻፈረኝ ብላ ባሏን በሌላ ህግ ለመዳኘት የማታደርገው ጥረት የለም።ለዚህ ተግባር  አላህ ፊት መልስ የለውም። ባልሽን መፍታት ስትፈልጊ በምን መልኩ መሆን እንዳለበት የአላህ መልክተኛ አሳምረው አስተካክለውልሽ አልፈዋል።ይህን አልፈሽ በሰው ሰራሽ ህግ እዳኛለሁ ብለሽ የምትፈልጊ ከሆነ የአላህ ቅጣት ከባድ መሆኑን ማወቅ ግድ ይልሻል። አላህ በቁርአኑ እንዲህ ብሏል፣👇

ۚ فَلَا تَخْشَوُا النَّاسَ وَاخْشَوْنِ وَلَا تَشْتَرُوا بِآيَاتِي ثَمَنًا قَلِيلًا ۚ وَمَن لَّمْ يَحْكُم بِمَا أَنزَلَ اللَّهُ فَأُولَـٰئِكَ هُمُ الْكَافِرُونَ
ሰዎችንም አትፍሩ፡፡ ፍሩኝም፡፡ በአንቀጾቼም አነስተኛን ዋጋ አትለውጡ፡፡ አላህም ባወረደው ነገር ያልፈረደ ሰው እነዚያ ከሓዲዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡(ሱረቱ አል-ማኢዳህ - 44)

    የቁርአኑ አንቀፅ እንደሚያስረዳው የአላህ ህግጋት እያለ ወደ ሌላ ሰው ሰራሽ ህግ ለመሄድ አስገዳ ጅ ነገር ሳይኖር በሸሪዓ ከመዳኘት ሰው ሰራሽ ህግ የበለጠ ይጠቅመኛል ብሎ አስበልጦ የሄደ በአላህ የካደ ነው ሲል አስግጧል።

#እህቴ_ሆይ_ኢስላም ያስቀመጠልሽን ፍትህ ትተሽ በሰው ሰራሽ ህግ ለጊዜው የተጠቀምሽ ሊመስልሽ ይችል ይሆናል በኃላ ግን ፀፀት ውስጥ ትወድቂያለሽ ለዱኒያም ሆነ ለአኼራ ትክክለኛ ፍትህ እና ጥቅም ያለው በኢስላም ውስጥ ብቻ ነው።
    አንዳንድ እህቶች በሰላም እየኖሩ በቤተሰብ ወይም በጓደኛ ግፊት ከሜዳ ተነስተው አምባጓሮ ፈጥረው ባላቸውን ፍቺ የሚጠይቁ አሉ።በጣም ይገርማል!! መጀመሪያ እነዚህ ቤተሰቦች በቅናተወ ወይም እሷ የምታመጣውን ሀብት ለመቀራመት በመፈለግ ወይም ባሏን በመጥላት እንዲፈታት ያግባቧታል።ይቺ የዋህ ሴት በሰላም ከምትኖርበት ቤት በክብር ከያዛት ባሏ ለመፈታት ዉሳኔ ላይ ትደርሳለች።ይህን ስትፈፅም ለህይወቷ ባታስብ እንኳን የነብዩ (ሰአወን) ሀዲስ ማክበር ግዴታ ይሆንባት ነበር። ይህን የነብዩን (ሰአወ) ማስጠንቀቂያ ወደ ጎን በመተው የምትጓዝ ከሆነ የሚጠብቃት ቅጣት ከባድ ለመሆኑ  የሚከተለው ሀዲስ ይጠቁማል ።

  ሶውባን ከነብዩ ሰአወ ሰምተው ባስተላለፉት ሀዲስ እንዲህ አሉ፣
#ማንኛዋም ሴት አስቸጋሪ ነገር ሳይገጥማት ባሏን ፍቺ የጠየቀች ከሆነ የጀነት ሽታ በእርሷ ላይ እርም ይሆናል። (አቡ ዳውድ፣ቲርሙዚይና ሌሎችም ዘግበውታል) #ይቀጥላል_ኢንሻአላህ_ቴሌግራማችን_ሼር_ያድርጉ👇👇

            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
#ወንዶች
ሚስቶቻቹ ለናንተ እንደሚዋቡት ሁሉ እናንተም ልትዋቡላቸው ይገባል።
እሷን በኒሳዕ ሳሙና ታጠቢ እያልክ አንተ በአጃክስ/ላርጎ እንድትታጠብ ማን ፈቀደልክ?!