The Christian News
5.36K subscribers
3.06K photos
27 videos
722 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
#የወንጌል ዘመቻ ሊካሄድ ነዉ።

ጋፕስ አለም አቀፍ አገልግሎት
አንጾኪያ የወንጌል እንቅስቃሴ

ጋፕስ ያለፉትን 14 ዓመታት የአገልጋዮችን የኑሮ ክፍተት መሙላት፡ የመንፈሳዊ ክፍተት መሙላት (ማጎልበት፡ ማስተማር) ላይ ሲሰራ ቆይቷል።

አንጾኪያ የወንጌል እንቅስቃሴ የ10 ቀናት የወንጌል ዘመቻ በነገው እለት ጀምሮ ከሚያዝያ 9-19 ድረስ ይካሄዳል።

ዘመቻው፡ የቡና #ሻይ ሰዓትን ለወንጌል፡ ሙስሊም ኢቫንጀሊዝም፡ የደም ልገሳ፡ የጎዳና ወንጌል፡ #አንድ #ሰው ለኢየሱስ፡ ማህበራዊ ሚድያን ከወንጌል፡ አርትን ለወንጌል፡ በመርዳት ወንጌል መስበክ፡ ሙዚቃን ለወንጌል፡ የርህራሄ አገልግሎት በዘመቻው በየእለቱ የሚሰሩ ስራዎች ናቸው።

የጋፕስ ሚኒስትሪ መስራችና መሪ መጋቢ ዳንኤል ዋለልኝ ሁሉም ሰው የተልዕኮ ሰራተኛ መሆኑን ማወቅ ይኖርበታል፡ በእነዚህ 10 ቀናት ሁሉም #ክርስቲያን አንጾኪያ በሚያደርገው የወንጌል ዘመቻ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

የክርስቲያን መገናኛ ብዙሃንም በዚህ የወንጌል ዘመቻ በትልቅ ተሳትፎ እንዲሰራ፡ የክርስቲያን ጋዜጠኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ዘሪሁን ግርማ ጥሪ አቅርበዋል።

አንጾኪያ ሙቭመንት #አዲስ የወንጌል ተኮር አገልግሎት ነው። አላማው በሐዋ ስራ 11 እንደተገለጸው፡ የአንጾኪያ ቤ/ክ የወንጌል አካሄድ መድገም ነው።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና መግለጫውን በስፍራዉ በመገኘት አሰናዳንላችሁ።