✞ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ነን✞
33.4K subscribers
90 photos
7 videos
52 links
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን::
➜ መዝሙር ➜የቅዱሳን ታሪኮች
➜ስብከት
✞ የሚለቀቅበት ቻናል ነው ወዳጅ ዘመድዎን ይጋብዙ
https://t.me/Orthodox_tewahdo_nen
Https://YouTube.com/tomi_8019
Https://www.tiktok.com/@tomi8019
Https://www.Instagram.com/@tomi801977
Download Telegram
ጥር 16/2016 #ቅድስት_ኪዳነ_ምህረት

👉በስመ #አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስን በምስጋና ከፍ ለምናደርግበት እናታችን #ኪዳነ_ምህረትን በቃል ኪዳኗ እንድትጠብቀን ለምንማፀንበት ወርሐዊ መታሠቢያ ክብረ በአል እንኳን አደረሰን

👉 #ኪዳነምህረት ስንል የምህረት ቃል ኪዳን ማለት ነው በዚህ ውስጥም ምህረት አድራጊው ጌታችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ምህረት ተቀባይም መላው የአዳም ዘር ነው

👉 #እናታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም በምድራዊ ቆይታዋ ዘውትር ወደ #ክርስቶስ_መካነ_መቃብር_ጎለጎታ እየሔደች ትፀልይ ነበር ልጇ እና ወዳጇ ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገችውን ልመናና ፀሎት ተመልክቶና ሰምቶ #የምህረት_ቃል_ኪዳንን ሰጣት

👉እንኳን የእናቱን ፀሎት እና ልመና ቀርቶ ዘውትር በሀጥያት የምንዘፈቀውን እኛን ክፉዎቹን የሚሰማ አምላክ ስለ አንቺ ስለ እናቴ ክብርና ፀጋ ስል ይኸው ቃሌ ብሎ #ቃል_ኪዳን አደረገ

👉"ከመረጥሁት ጋር #ቃል_ኪዳኔን አደረግሁ" መዝ፣89፦3

👉ስሟን ለሚጠሩ በእርሷ አማላጅነት ለሚታመኑ በምድር በረከትን በሰማይ የዘለዓለም መንግስትን እንደሚወርሱ የምህረት እና የቸርነት #ቃል_ኪዳን ሰጥቷታል

👉በታላቁም መፅሐፍ ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ ሁሉ መካከል ያለውን የዘላለም #ቃል_ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ ኦሪት ዘፍ፣9፣16

👉በዚህም መሠረት #ቃል_ኪዳኗን ምክንያት በማድረግ #ኪዳነ_ምህረት እያልን እንጠራታለን የከበረዉ ቃል ኪዳኗ ሀገራችንን ህዝባችንን ይጠብቅልን "አሜን" ✝️ 💒 ✝️

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                   •➢ ሼር // SHARE

     ✥••┈┈••●◉ ✞◉●••┈┈••✥
💚
@Orthodox_tewahdo_nen💚     
💛@Orthodox_tewahdo_nen💛
❤️
@Orthodox_tewahdo_nen❤️
      ✥••┈┈••●◉ ✞◉●••┈┈••✥
ጥር 18/2016 #ዝርወተ_አፅሙ_ለቅዱስ_ጊዮርጊስ

👉በስመ #አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስን በሰማእቱ ስም ለምናመሰግንበት ለሰማእቱ #ቅዱስ_ጊዮርጊስ አመታዊ ክብረ በአል እንኳን አደረሰን

👉ከሃዲው ንጉሥ ዱድያኖስ እጅግ አሠቃቂ በሆኑ ብዙ መከራዎች እያሠቃየ ሦስት ጊዜም ቢገድለው ጌታችን ግን ቅዱስ #ጊዮርጊስን ከሞት እያስነሣው ከሃድያንን ያሳፍራቸው ነበር

👉ንጉሥ ዱድያኖስ የሚያደርገው ቢያጣ ጭፍሮቹን በመንኰራኩር ፈጭታችሁ አጥንቱን ደብረ ይድራስ ተራራ ላይ ወስዳችሁ ዝሩት ብሎ አዘዛቸው ጭፍሮቹም የቅዱስ #ጊዮርጊስን ሥጋ በመንኰራኩር ፈጭተው ወስደው በተራራው ላይ ቢረጩት ሥጋው ያረፈበት ሳር፣ ቅጠሉ፣ ደንጊያው፣ እንጨቱ ሁሉ #ጊዮርጊስ_ቅዱሱ_ለእግዚአብሔር ጊዮርጊስ ሰማዕቱ ለእግዚአብሔር እያሉ አመስግነዋል

👉አሁንም ጌታችን ለሦስተኛ ጊዜ ከሞት አስነሣውና ሥጋውን
ፈጭተው በተራራም ላይ ሥጋውን በትነውት ወደ ንጉሡ የሚመለሱትን ወታደሮች በመንገድ ከኋላቸው ሄዶ ደረሰባቸውና #ቆዩኝ_ጠብቁኝ አላቸው እነርሱም እጅግ ደንግጠው ይህ
እንዴት እንደሆነ ሲጠይቁት #አምላኬ_ከሞት_አዳነኝ አላቸው

👉ጭፍሮቹም እጅግ ደንግጠው ከእግሩ ስር ወድቀው ‹‹ይቅር በለን›› ብለው በአምላኩ እንደሚያምኑ መሰከሩለት ቅዱስ #ጊዮርጊስም ከመሬት ላይ ውሃ አመንጭቶ በጸሎት ጌታችንን
ቢጠይቅ ቅዱስ ዮሐንስ መጥቶ አጥምቋቸዋል እነርሱም በንጉሣቸው ፊት ሄደው ስለጌታችን #በመመስከር በሰማዕትነት ዐርፈዋል

👉 #ሰማዕቱ_ቅዱስ_ጊዮርጊስ ዐፅሙ ተቃጥሎ አጥንቱ ተፈጭቶ #በደብረ_ይድራስ_ተራራ ላይ የተበተነው በዚህች በጥር 18 ዕለት ነው የእመቤታችን ቅድስት ድንግል #ማርያም
አገልጋይ ብርቱዉንም ደካማዉንም ፍጥረት ኹሉ ፈጥነህ የምትረዳ ሊቀ ሰማዕታት #ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ሆይ እንደ እመቤትህ ቅድስት ድንግል ማርያም አንተም ከበቀልና ቂም የተለየህ ርኅሩኅ ልብና ለሰዎች ኹሉ የምታዝን ደግ ሰማዕት ነኽ

👉አማላጅነትህን በመታመን ለሚጠራህ ኹሉ ከነፋስ ዐውሎ ይልቅ ፈጥነህ የምትደርስ ሊቀ ሰማዕታት #ቅዱስ_ጊዮርጊስ ሆይ የርሕሩሕ አምላክ #እግዚአብሔር ርህራሄን ተጎናጽፈኻልና በዚህ ሰአት በጭንቅ ያሉ የወዳጆችህን ልመና ስማ

👉ኅዘንን የምታረጋጋ አባቴ ፍጡነ ረድኤት ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ #ጊዮርጊስ ሆይ ለጠላት መሣቂያ ለጠላቶቻችን መዘባበቻ እናድንሆን በገዳም ያሉ የእናቶቻችንን የአባቶቻችንን የጩኸት ድምፅ ሰማ

👉ከሃዲው ንጉሥ ዱድያኖስ ሰባው ነገሥት ስለ #ክርስቶስ ሰለመሠከረ አካላቱ እየቆራረጡ በሥጋው የአሠቃዩት የልዑል #እግዚአብሔር ወታደር ፍጡነ ረድኤት ኃያል ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ እንሆ የተጋድሎ ዝናውን ስንሰማ ግርማ
ሞገስህ ከሰማዕታት ኹሉ ይበልጣል

👉ለሰባት ዓመታት ትእግሥትን በማዘወተር አስጨናቂዎች መከራዎችን ለተሸከመ ትከሻህ ሰላምታ የሚገባህ የአስጨናቂዎች የሥቃይ ሰባት ዓመታትን የታገሥህ ሊቀ ሰማዕታት #ቅዱስ_ጊዮርጊስ ሆይ የድል በተርህን ይዘህ ኹልጊዜ እደሚገሰግስ አርበኛ የኢትያጵያ ጠላቶች ትመታልን ዘንድ ፈጥነህ ገሥግሰህ ናልን

👉አቤቱ #የቅዱስ_ጊዮርጊስ አምላክ እዘንልን ራራልን ይቅርም በለን የሰማእቱ ረድኤትና በረከት አይለየን ምልጃ ፀሎቱ ይጠብቀን "አሜን" ✝️ 💒 ✝️

👉ገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                   •➢ ሼር // SHARE

     ✥••┈┈••●◉ ✞◉●••┈┈••✥
💚
@Orthodox_tewahdo_nen💚     
💛@Orthodox_tewahdo_nen💛
❤️
@Orthodox_tewahdo_nen❤️
      ✥••┈┈••●◉ ✞◉●••┈┈••✥