STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
40.8K subscribers
11K photos
271 videos
452 files
1.93K links
የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡
Download Telegram
ጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን እያስመረቀ ይገኛል!

ጅማ ዩኒቨርስቲ በቅድመና በድህረ ምረቃ ዘርፎች ያስተማራቸውን 3 ሺህ 139 ተማሪዎች ዛሬ እያስመረቀ ነው። ከእነዚህ ምሩቃን ውስጥም 237 የህክምና ዶክተሮች፣ 27 የጥርስ ህክምና ዶክተሮች 8ቱ ደግሞ የሶስተኛ ድግሪ ተመራቂዎች ናቸው፡፡ ከተመራቂዎች መካከልም 13ቱ ከሶማሊላንድና ከሩዋንዳ የመጡ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

Via #EPA

ለተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎች ቻናላችንን ተቀላቀሉን👇
@NATIONALEXAMSRESULT
@NATIONALEXAMSRESULT
@NATIONALEXAMSRESULT
የተማሪዎችን ቅበላ እና ድልደላ የሚያስተዳድርበት ሥርዓት ማዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ አስታውቋል !

የኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን ቅበላና ድልደላ የሚያስተዳድርበት ሥርዓት ማዘጋጅቱን ገልጿል።

የኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ ዋና ዳይሬክተር ተሻለ በሬቻ ለኢፕድ እንደገለፁት፣ ዩንቨርሲቲው የተማሪዎችን ቅበላና ድልደላ የሚያስተዳድርበት ሥርዓት አዘጋጀቶ ለኢፊድሪ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንዲፀድቅ አቅርቧል።

በዚህም በቅርቡ ፀድቆ ዩንቨርሲቲው ተማሪዎችን መቀበል እንደሚጀምር ገልጿል።

እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ፤ ዩንቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን መቀበል የሚጀምር ሲሆን ተማሪዎቹ በኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ የሚሰጥ የመግብያ ፈተናም እንደሚሰጣቸው ገልፀዋል።

በቀጣዩ ዓመት ጥቅምት ወር ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎችን ተቀብሎ በመጀመሪያ ዲግሪ እንደሚያስተምርም ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።

Via #EPA

#SHARE
መረጃው ለሌሎችም እንዲደርስ ያጋሩ

ለተጨማሪ ተማሪ ነክ ለሆኑ የተጣሩ መረጃዎች እና ዜናዎች የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
#MoE

"በአገር አቀፍ ደረጃ ያሉ 49 ሺ ትምህርት ቤቶችን የማሻሻል ዘመቻ ከአንድ ወር በኋላ ይጀመራል" - የትምህርት ሚኒስቴር፡፡

የትምህርት ምዘና ጥናት ውጤቶችን ለማስተዋወቅ የተዘጋጀ አውደ ጥናት በመካሄድ ላይ ነው፡፡ በመድረኩ የቅድመ አንደኛ ደረጃ የትምህርት ጥራት ውጤት ምዘና እንዲሁም የ4ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የትምህርት ምዘና ጥናት ይፋ ሆኗል።

በናሙና በተወሰዱ ትምህርት ቤቶች በተደረገው ምዘና ዝቅተኛ ውጤት መገኘቱን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡

የትምህርት ሥርዓቱን አሁን ባለበት ሁኔታ ይዞ መቀጠል አይቻልም ያሉት ሚኒስትሩ፤ በአገር አቀፍ ደረጃ ባሉት 49 ሺ ትምህርት ቤቶች የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

በመሆኑም ትምህርት ቤቶችን የማሻሻል ዘመቻ ከአንድ ወር በኋላ እንደሚጀመር ይፋ አድርገዋል፡፡ በዘመቻው ተማሪዎች፣ መምህራን፣ የቀድሞ ተማሪዎች እና ማህበረሰቡ ተሳታፊ እንደሚሆኑ አመልክተዋል፡፡

ርዕሰ መምህራንን ለማብቃት የሚያስችል ማዕከል እየተቋቋመ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡ #EPA #MoE



የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot