STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
40.7K subscribers
11K photos
272 videos
452 files
1.94K links
የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡
Download Telegram
* Congratulations !

በዛሬው ዕለት ብቻ ከተለያዩት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 23,192 ተማሪዎች ተመርቀዋል።

የትኞቹ ዩኒቨርሲቲዎች ምን ያህል ተማሪ ? በምን ደረጃ እና የትምህርት ዘረፍ አስመረቁ ? ለጥያቄዎቹ መልስ ይህን አጭር ቁጥራዊ መረጃ አስቀምጠናል።

#HawassaUniversity

- አጠቃላይ 6 ሺህ 793 ተማሪዎችን አስመርቋል።
- ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 2 ሺህ 158ቱ ወይም 32 በመቶ ሴቶች ናቸው።
- ተመራቂዎቹ በመጀመሪያ፣ በ2ኛ እና በ3ኛ ዲግሪ በመደበኛና ተከታታይ መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

#BahirdarUniversity

- አጠቃላይ 5 ሺህ 586 ተማሪዎች አስመርቋል።
- ከተመራቂዎቹ 1 ሺህ 714ቱ ሴቶች ናቸው።
- በመጀመሪያ፣ በ2ኛ እና በ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናሰቁ ናቸው።

#JimmaUniversity

- አጠቃላይ 696 ተማሪዎች አሰመርቋል።
- 450 ወንድ እና 246 ሴት ተማሪዎች ናቸው።
- በቅድመ ምረቃና በድህረ ምረቃ መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።
- ከተመራቂዎቹ 252 ተማሪዎች በአጠቃላይ ሕክምናና በጥርስ ሕክምና የሰለጠኑ ናቸው።
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ በሶማሊላንድ ሀርጌሳ ካምፓሱ በ 'ኒውትሬሽን' የትምህርት ዘርፍ ያስተማራቸውን 19 የ2ኛ ዲግሪ ተማሪዎችንም አስመርቋል።

#AdamaScience_and_TechnologyUniversity (ASTU)

- አጠቃላይ 1 ሺህ 298 ተማሪዎች አስመርቋል።
- ሰባቱ በሦሥተኛ ዲግሪ (ፒኤችዲ) ተመራቂዎች ናቸው።
- 215ቱ በሁለተኛ ዲግሪ የተመረቁ ናቸው።
- 1 ሺህ 76 ተማሪዎች በመጀመረያ ዲግሪ የተመረቁ ናቸው።

#MettuUniversity

- አጠቃላይ 2 ሺህ 262 ተማሪዎች አስመርቋል።
- 116ቱ በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።
- ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ ግብሮች በመቱ እና በበደሌ ካምፓሶች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።

#ArsiUniversity

- አጠቃላይ 831 ተማሪዎችን አስመርቋል።
- በበቆጂ ካምፓስ የሰለጠኑ ናቸው።
- ተመራቂዎቹ በማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ በመደበኛና በተከታታይ መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።
- በመጀመሪያ እና በ2ኛ ዲግሪ ከተመረቁት መካከል 392ቱ ሴቶች ናቸው።

#AmboUniversity

- አጠቃላይ 4 ሺህ 524 ተማሪዎች አስመርቋል።
- በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ የሰለጠኑ ናቸው።
- ከተመራቂዎቹ 1 ሺህ 980ዎቹ ሴት ተማሪዎች ናቸው።
- ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 450 የሚሆኑት የሁለተኛ ዲግሪ ተመራቂ ሲሆኑ 11 የደቡብ ሱዳን ስደተኛ ተማሪዎች ይገኙበታል።

#JigjigaUniversity

- አጠቃላይ 1 ሺህ 202 ተማሪዎችን አስመርቋል።
- ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 336ቱ ሴት ተማሪዎች ናቸው።
- 233ቱ በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ሲሆን ቀሪዎቹ 969ኙ በመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።

መረጃውን በማጋራት ላልሰሙ እናሰማ


ለበለጠ ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
#MettuUniversity

መቱ ዩኒቨርሲቲ ከወልዲያ እና አክሱም ዩኒቨርሲቲዎች ወደ ተቋሙ የተመደቡ ተማሪዎች ምዝገባ ታህሳስ 04 እና 05/2014 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

ተማሪዎች ለምዝገባ ሊይዟቸው የሚገቡ፦

• የነበሩበት ዩኒቨርሲቲ የተማሪነት መታወቂያ ካርድ
• የነበሩበት ዩኒቨርሲቲ የምዝገባ ስሊፕ
• የነበሩበት ዩኒቨርሲቲ ግሬድ ሪፖርት
• የ8ኛ፣ 10ኛ እና የ12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕቶች
• የሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ሰርቴፊኬት (3 ኮፒ)
• 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ (8)
@NATIONALEXAMSRESULT
#MettuUniversity

በወልድያ ዩኒቨርሲቲ ያስተምሩ የነበሩና በትምህርት ሚኒስቴር በጊዚያዊነት ወደ መቱ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ #መምህራን ሪፖርት እንዲያደርጉ ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

መቱ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ሚኒስቴር በጊዚያዊነት የተመደቡለትን የ106 መምህራን ዝርዝር በይፋዊ ድረ-ገጽ አድራሻውና በማህበራዊ ሚዲያ አካውንቶቹ ይፋ አድርጓል።

መምህራኑ ከየካቲት 04/2014 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት አስር (10) የሥራ ቀናት ውስጥ በመቱ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ በመገኘት ሪፖርት እንዲያደርጉ አሳስቧል፡፡

ተማሪ ነክ መረጃዎችን እንዘግባለን
@NATIONALEXAMSRESULT
#MettuUniversity

በ #2014 የዩንቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አስመዝግባቹህ በትምህርት ሚኒስቴር ወደ መቱ ዩኒቨርሲቲ የተመደባቹህ ተማሪዎች የመግቢያ ቀን ግንቦት 03-04/2014 መሆኑን ዩንቨርሲቲው አሳውቋል ።

📌የስማቹህ ቀዳሚ ፊደል A-D ለናቹራል ሳይንስ እና A ለሶሻል ሳይንስ ተማሪዎች ብቻ ምዝገባ የሚከናወነው በበደሌ ካምፓስ መሆኑን ዩንቨርሲቲው አሳስቧል።

፨ተጨማሪ መረጃ ከማስታወቂያው ያንብቡ

ተማሪ ነክ መረጃዎችን እንዘግባለን
@NATIONALEXAMSRESULT
#MettuUniversity

መቱ ዩኒቨርሲቲ የነባር የክረምት ተማሪዎች ቲቶርያል ትምህርት ከሐምሌ 07 እስከ 09/2014 ዓ.ም እንደሚሰጥ አሳውቋል።

የ2014 ዓ.ም የክረምት ትምህርት በመቱ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ብቻ እንደሚሰጥ ተቋሙ ገልጿል።

(ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል።)


ተማሪ ነክ መረጃ እንዘግባለን
@NATIONALEXAMSRESULT
#MettuUniversity

መቱ ዩኒቨርሲቲ በ2014 ዓ.ም በክረምት መርሃ ግብር በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ለመማር አመልክታችሁ የመግቢያ ፈተና ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና የሚሰጠው ሐምሌ 06/2014 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ላይ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ተፈታኞች በተባለው ቀንና ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ በመያዝ በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ በመገኘት ፈተናውን እንድትወስዱ ተብሏል፡፡

ተማሪ ነክ መረጃ እንዘግባለን
@NATIONALEXAMSRESULT
#MettuUniversity

በመቱ ዩኒቨርሲቲ በክረምት እረፍት ላይ የነበሩ መደበኛ (Regular) ፤ የሳምንት ዕረፍት ቀናት (Weekend ) እንዲሁም የማታ ( Evening) የመጀመሪያ ዲግሪ እና የድህረ ምረቃ ነባር ተማሪዎች በሙሉ የ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የምዝገባ ቀን ህዳር 1-2/2015 ዓ.ም እንዲሁም በቅጣት ህዳር 03/2015 ዓ.ም እንደሚካሄድ ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ተማሪዎች በተጠቀሰው ፕሮግራም በአካል በመቅረብ ተመዝገቡ፤ ትምህርት የሚጀምረው ህዳር 05/2015 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።

(መቱ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር ዳይሬክቶሬት)

ተማሪ ነክ መረጃዎችን ያግኙ
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#MettuUniversity


በ2016 ዓ.ም በሬሚድያል ትምህርት መረሃ ግብር በትምህርት ሚኒስቴር ወደ መቱ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ (Remedial Students) ተማሪዎች፤ የምዝገባ ጊዜ ጥር 20-21/2016ዓ.ም መሆኑን አዉቃችሁ በአካል በመቅረብ እንድትመዘገቡ ዩንቨርሲቲው አሳስቧል።

ማሳሰቢያ፤
 የስማችሁ ቀዳሚ ፊደል A- B #ለተፈጥሮ ሳይንስ ስትሪም እና ለማህበራዊ ሳይንስ ስትሪም የሚጀምር ተማሪዎች ፤ ምዝገባችሁ የሚሆነው በበደሌ ካምፓስ መሆኑን እናሳስባለን፡፡


📌ተማሪዎች ለምዝገባ ስትሄዱ
ብርድ ልብስ፤ አንሶላና ትራስ ጨርቅ፤ የስፖርት ልብስ
ከ8-12ተኛ ክፍል ያሉ የት\ት ማስረጃዎች ኦረጂናልና ኮፒ ኢንድሁም
አራት(4) ጉርድ ፎቶ ግራፍ ይዛችሁ ረፖርት እንድታደርጉ ዩንቨርሲቲው ጨምሮ አሳስቧል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot