STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
40.9K subscribers
11K photos
271 videos
452 files
1.93K links
የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡
Download Telegram
የኦሮሚያ ክልል በ80 ሚሊየን ብር ወጪ በጉራጌ ዞን ያስገነባውን ትምህርት ቤት አስመረቀ
*****
(ኢ ፕ ድ)


የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸውዛሬ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን በእኖር ወረዳ የጉስባጃይ ኢፈ ቦሩ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት አስመርቀናል ብለዋል።

የጉስባጃይ ኢፋ ቦሩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፕሮጀክት መንግስታችን በክልላችን ህዝብና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝቦች መካከል እውነተኛ ህዝብ ለህዝብ ግኑኙነትና ወንድማማችነትን ለማስፈን ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።

ክልሉ በቅርቡ የተዋቀረ አዲስ ክልል እንደመሆኑ የተለያዩ የልማት ጥያቄዎችን ለመመለስና የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የክልሉ መንግስት በሚሰራቸው ስራዎች ውስጥ እንደ የክልላችን መንግስት የበኩላችንን ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆናችንን ዳግም ያረጋገጥንበት ነውም ብለዋል።

በዛሬው እለት የተመረቀው ትምህርት ቤት በክልላችን መንግስት ለአጎራባች ክልሎች ተገንብቶ የተከፈተው አራተኛው ትምህርት ቤት ሲሆን በሌሎችም የሀገሪቱ ክልሎች የህዝቦችን ወንድማማችነት እና አንድነት የሚያጎለብቱ ትምህርት ቤቶችን እየገነባን ነው።

በአንድ በኩል የክልላችን መንግስት በአገር አቀፍ ደረጃ እየተሰራ ባለው የትምህርት ተደራሽነት ስራ ውስጥ የራሱን ሚና እየተወጣ መሆኑን የሚያሳይ ሲሆን በሌላ በኩል በክልሎችና ህዝቦች መካከል ግንኙነት በጋራ ልማትና ብልፅግና እንደሚኖረው እናምናለን ሲሉም ገልጸዋል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
ከተማሪዋ ያረገዘችው መምህር በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ተከሰሰች።

የ33 ዓመት እድሜ አላት የተባለችው መምህር አሜሪካዊ ስትሆን ከተማሪዋ ልጅ መውለዷ ተገልጿል።

መምህር ሞርጋን ፍሬች የ17 ዓመት እድሜ ካለው ተማሪዋ ጋር ጾታዊ ግንኙነት ፈጽማለች የተባለ ሲሆን ይህም የሀገሪቱን ህግ ተላልፋ ተገኝታለች ተብሏል።

መምህርቷ 18 ዓመት ባልሞላው ተማሪዋ ላይ አስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈጽማለች የተባለ ሲሆን ተማሪው የስነ ልቦና ድጋፍ እየተደረገለት እንደሆነ ፎክስ ኒውስ ዘግቧል።

ፖሊስ ጥቆማው ከሁለት ዓመት በፊት እንደደረሰው ገልጾ ምርመራው ጥንቃቄ እና ጊዜ የሚፈልግ በመሆኑ በድብቅ ምርመራ ሲካሄድ መቆየቱን አስታውቋል።

ጥቆማው ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮም መምህርቷ በትምህርት ቤቱ የነበራትን ስራ በራሷ ፈቃድ መልቀቋም ተገልጿል።
የተማሪው ወላጆች በበኩላቸው ትምህርት ቤቱ በልጃቸው ጉዳይ ሀላፊነቱን እንዳልተወጣ መናገራቸው ተገልጿል።

ይሁንና ትምህርት ቤቱ ከህግ እና ከሙያ ስነ ምግባር ውጪ የሆኑ መምህራንን እንደማይታገስ ገልጾ መሰል ድርጊቶች ጥንቃቄ የሚጠይቁ መሆናቸውን አስታውቋል ሲል ፎክስ ኒውስን ጠቅሶ አል ዓይን አስነብቧል።
የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
በናይጀሪያ ግማሽ ያህሉ የመንግስት ዩንቨርስቲ መመህራን ለተሻለ ደሞዝ ፍለጋ ስራ መልቀቃቸውን ዘ ጋርዲያን የተባለው የሀገሪቱ ጋዜጣ ዘግቧል።

በቅርቡ ለመምህራኑ የ35% የደሞዝ ጭማሪ ቢደረግም ይሄ በቂ አይደለም የሚል ትችት በመምህራኑ ቀርቧል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
Nottingham Research Fellowship Program 2024 in UK | Fully Funded

Link: https://scholarshipscorner.website/nottingham-research-fellowship-program/

Benefits:

1) Three years’ independent research funding, covering salary costs at c. £43,155 to £54,421
2) the link to a permanent academic post, subject to performance
3) additional funding for research expenses totaling £75,000
childcare costs of up to £15,000
4) access to mentoring, career development, and networking with the wider fellowship community

Deadline:Friday 6 October 2023.

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#TVTI

የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የመውጫ ፈተና ከወሰዱ 1,343 የተቋሙ ተመራቂ ተማሪዎች 985 ተመራቂዎች የማለፊያ ነጥብ ማምጣታቸውን ገልጿል።

በነሐሴ መጨረሻ የተሰጠውን ፈተና ከወሰዱ ተመራቂዎች 74.34 በመቶ የሚሆኑት ማለፋቸውን ኢንስቲትዩቱ አሳውቋል።

የመውጫ ፈተናው የኢንስቲትዩቱ የስልጠና ማዕከልን ጨምሮ በስምነት የፈተና ጣቢያዎች ተሰጥቷል።

በመጀመሪያ ዲግሪ (ደረጃ ስድስት) ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች በሁለት የስልጠና መስኮች የመውጫ ፈተናውን መውሰዳቸው ተገልጿል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ASTU

አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለቅድመ እና ድህረ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎቹ አድርጎት የነበረውን ጥሪ አራዝሟል።

ዩኒቨርሲቲው የ4ኛ ዓመትና ከዚያ በላይ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች እንዲሁም የ2ኛ ዓመትና ከዚያ በላይ የድህረ ምረቃ ተማሪዎች ምዝገባ መስከረም 28 እና 29/2016 ዓ.ም ይከናወናል ብሎ የነበረ ሲሆን ይህም በአንድ ሳምንት የተራዘመ መሆኑን አሳውቋል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#Update

ብሔራዊ የድህረ ምረቃ ትምህርት የመግቢያ ፈተና (GAT) ምዝገባ ያደረጉ የተወሰኑ አመልካቾች ክፍያ ፈፅመው የማመልከቻ ሒደታቸውን ቢያጠናቅቁም የAdmission ቲኬት በመጠባበቅ ላይ (pending) እንደሆኑ ማወቁን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው ችግሩን ለመፍታት ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ጠቁሟል።

አመልካቾች የAdmission ቲኬታቸውን ማግኘት የሚችሉበትን መፍትሔም እንደሚያመቻች አሳውቋል።

የተወሰኑ አመልካቾች Username and Password በኢሜይል እንዳልደረሳቸው መገንዘቡንም ዩኒቨርሲቲው አረጋግጧል።

በዚህም ዩኒቨርሲቲው የአመልካቾችን Username and Password በቀጥታ ለፈተና አስተባባሪዎች እንደሚልክና ተፈታኞች እንዲወስዱ ይደረጋል ተብሏል።

አመልካቾች Username and Password እንዲላክላቸው በመመዝገቢያው ፖርታል አማካኝነት ኢሜይል በማድረግ በመጠቀየቅ መውሰድ እንደሚችሉም ተመላክቷል።

የተሳሳተ ፎቶግራፍ በተወሰኑ አመልካቾች የAdmission ቲኬት ላይ መውጣቱን የገለጸው ዩኒቨርሲቲው፤ እነዚህ አመልካቾች የAdmission ቲኬታቸው እንዲታደስላቸው በመጠየቅ ማስተካከል እንደሚችሉ ገልጿል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
አዲስ ምዝገባ ለ2016 የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች (ገርጂ)

የማካካሻ ትምህርት ተፈትናችሁ 50 እና 50% በላይ ያመጣችሁ ተማሪወች እንኳን ደስ አላችሁ እያልን፣ ዩኒቨርስቲያችን ባሉት መርሀግብሮች፣ መስፈርቱን የሚያሟሉ አዳዲስ አመልካቾችን ለመቀበል ሙሉ ዝግጅቱን ያጠናቀቀ መሆኑን ስንገልፅ በደስታ ነው።

ስለሆነም በምናሳውቃችሁ የኦንላይን ዌብሳይ መመዝገብ እንድትችሉ፣ ከዚህ ልጥፍ ጋር  የተያያዙትን መረጃዎች በማሟላት እንድትጠብቁን እናሳውቃለን።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#የምስራች @#Exitexam Tutorial
🥇 ለአካውንቲንግ
🥇 ለማኔጅመንት
🥇 ለቢዝነስ ማኔጅመንት
🥇ለማርኬቲንግ ማኔጅመንት
🥇ለሲቪል ምህንድስና
🥇ለኮምፒውተር ሳይንስ
#የመውጫ ፈተና መዘጋጃ #ልዩ ትምህርት
➾  በአንጋፋ ፕሮፌሰሮችና የዪኒቨርስቲ
      መምህራን
➾ በት/ት ሚ/ር ለፈተና በተመረጡ ኮርሶች
      ላይ ብቻ: የፈተና ጥያቄዎች ላይ በማተኮር
➾ በቂ የጥናት ሞጁሎች
➾ ሞዴል የመለማመጃ ፈተናዎች ከሙሉ
      መልስና ማብራሪያ  ጋር
➾ የኦንላየን መለማመጃ   ሲስተም
➾ ውጤታማ የፈተና አሰራር ሥልጠና
***
💥 እጅግ በተመጣጣኝ ክፍያ 

🛎 በየማዕከላቱ ያሉ ውስን ቦታዎች ቀድመው
      ይያዙ
🔔 ሙሉ  ስምዎን  : የስልክ ቁጥርዎንና
     ዲፓርትመንትዎን 0908-198-786 
      ላይ ቴክስት በማድረግ ይመዝገቡ ።
➾➾➾➾➾➾
ለበለጠ መረጃ
➧ 0908198786 ማነጋገር ይቻላል።

➧➧     #Joinus @ t.me/aec_ethiopia

አድቫንስድ የት/ት ማማከር ማዕከል
           ከፍላጎትዎ ባሻገር !!!
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የመንግስት እና የግል ትምህርት ቤቶች በነገው ዕለት ማለትም መስከረም 25/2016 ትምህርት እንደሌለ ለተማሪዎቻቸው አሳውቀዋል።

@NATIONALEXAMSRESULT
#AmboUniversity

አምቦ ዩኒቨርሲቲ የመደበኛ ተማሪዎች የ2016 ትምህርት ዘመን ምዝገባ ጥቅምት 05 እና 06/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

ትምህርት ጥቅምት 07/2016 ይጀምራል ተብሏል።

የማካካሻ (ሬሜዲያል) ፕሮግራም በአምቦ ዩኒቨርሲቲ ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች በሌላ ማስታወቂያ ጥሪ እንደሚደረግላችሁ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

(የዩኒቨርሲቲው መልዕክት ከላይ ተያይዟል።)

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ይፋዊ የምስረታ መርሐግብር አካሒዷል።

የ60 ዓመታት የማስተማር ልምድ ያለው ተቋሙ፤ በአዲስ መልክ በትምህርት ዩኒቨርሲቲነት መደራጀቱን ተከትሎ የምስረታ በዓል ማከናወኑ ተመላክቷል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)፣ የተቋሙ ፕሬዝዳንት ብርሃነመስቀል ጠና (ዶ/ር)፣ የመንግሥት ከፍተኛ አመራሮች እና ሌሎች የዘርፉ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የተቋሙ የምስረታ በዓል ተከናውኗል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ብቁ መምህራንን በማፍራት የሀገሪቱን የትምህርት ጥራት የማሻሻል ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለበት የትምህርት ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

በመስከረም 2014 ዓ.ም በአዋጅ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ሆኖ የተቋቋመው ተቋሙ፤ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከማስተማር ጎን ለጎን ራሱን የማደራጀት ሥራ ሲያከናውን መቆየቱ በመድረኩ ተገልጿል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot