STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
40.7K subscribers
11K photos
272 videos
452 files
1.94K links
የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡
Download Telegram
#የትምህርትና_ስልጠና_ባለሥልጣን

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን መረጃ አሟልተው የላኩ 158 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ዝርዝር ይፋ አድርጓል።

እስካሁን የተሟላ ዝርዝር ከላኩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል አምስት ዩኒቨርሲቲዎች ማለትም ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ፣ ሐራምቤ ዩኒቨርሲቲ፣ አድማስ ዩኒቨርሲቲ፣ ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ እና ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ይገኙበታል።

በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና እንዲወስዱ ከግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተላኩ ተማሪዎችን መረጃ እያጣራ መሆኑን የገለጸው ባለሥልጣኑ፤ የተማሪዎችን መረጃ አጣርቶ እንደጨረሰ ለመውጫ ፈተና የሚቀመጡ ተማሪዎችን ዝርዝር እንደሚያሳውቅ ገልጿል፡፡

(የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን የተሟላ መረጃ የላኩ 158 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ዝርዝር ከላይ ከተያያዘው ምስል ይመልከቱ።)

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
Defence Vs Exit Exam

ብዙ ቤተሰቦቻችን ዘንድሮ ከሚሰጠው የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ጋር ተያይዞ Defence ቀርቶልናል በpaper ብቻ ነው Grade የሚያዝልን የሚሉ መልዕክቶችን ከተለያዩ ጊቢዎች እየላኩልን ይገኛሉ።

እናንተስ ጋር እንዴት ነው? ጊቢያችሁንም ጥቀሱልን🤔

በተለይ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የምትገኙ ቤተሰቦቻችን ይህን መረጃ አረጋግጡልን

@NATIONALEXAMSRESULT
#ዝርፊያ #ጥቆማ #አስተያየት

ሰላም SNCዎች በቅድሚያ ስለምትሰጡን መረጃዎች ከልብ አመሰግናለሁ።

ስሜ ይቆይ
የምማረው በኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ ሲሆን የ4ኛ ዓመት ተመራቂ የሳይኮሎጂ ተማሪ ነኝ።

በኛ ትምህርት ክፍል በየዓመቱ ሁለተኛ ሴሚስተር ላይ የተግባር ልምምድ እንወጣለን። እና ከዚህም በፊት አንደኛ ዓመት እያለን ጭራሽ ሳያስወጡን ቀሩ። ከዚያ በኋላ ባሉት ዓመታት ስንወጣ ደግሞ ለሻይ ተብሎ የሚሰጠን ከትክክለኛው ክፍያ ያነሰ እና እንኳን ለሻይ ቀርቶ ለአንድ መደበኛ ቀን ውሎም የማይበቃ ነው።

ይህ በኛ ዲፓርትመንት ብቻ ሳይሆን ለምሳሌ ሶሻል ወርክ ዲፓርትመንትም አይከፈላቸውም። ጊቢው በጣም ቢሮክራሲ የሚያበዛ እና ሌቦች ተጠራርተው የተሰባሰቡበት የሚመስል የነውረኞች ጊቢ ነው።

ታድያ ያልተከፈለንን እና ያልተሰጠንን ነው ከተመረቅን በኋላ ኮስት ሼሪንግ ላይ ታስቦ የምንከፍለው? እኛ ለጋሽ ሆነን ማለት ነው?

ድምጽ ሁኑን።

ጥቆማና አስተያየት ካለዎት
@SNC1BOT ላይ ማድረስ ይችላሉ።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
#ዝርፊያ #ጥቆማ #አስተያየት ሰላም SNCዎች በቅድሚያ ስለምትሰጡን መረጃዎች ከልብ አመሰግናለሁ። ስሜ ይቆይ የምማረው በኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ ሲሆን የ4ኛ ዓመት ተመራቂ የሳይኮሎጂ ተማሪ ነኝ። በኛ ትምህርት ክፍል በየዓመቱ ሁለተኛ ሴሚስተር ላይ የተግባር ልምምድ እንወጣለን። እና ከዚህም በፊት አንደኛ ዓመት እያለን ጭራሽ ሳያስወጡን ቀሩ። ከዚያ በኋላ ባሉት ዓመታት ስንወጣ ደግሞ ለሻይ…
ሰላሞ ስሜ ይቆይ
በዋቻሞ ዩንቨርስቲ  የ2ኛ አመት ኢንጂነሪንግ ተማሪ ነኝ
ዲፓርትመት ሰንመርጥ በዱራሜ ካምፓስ ደረሰን
ከዛንም ከዋናው ግቢ ጋር በጣም በትልቅ  ደረጃ ልዩነት አለው
1ሜን ገቢ በሳምንት 5 አይነት ምግብ አለ
2:ላይብረሪ በበቂ አለ
3:የሚጠጣ ውሀ አለ ሁሌም
4: የመማር ማስተማር ሂደቱ ሁሌም ክላስ አለ
5:የኔትወርክ አገልግሎት በደብ አለ
6:በተ ሙከራዎች አሉ
ከብዙ በጥቂቱ
    



👉ዱራሜ ካምፖስ
1:   ሁሌም አንድ አይነት ምግብ (ሽሮ)ከእሩዝ፣ዜርፎር ፣ዳቦ ቀንውጪ
2:  የሚጠጣ ውሀ በሳምት ሁለት ቀን ለ20 ደቂቃ ለ4000ተማሪ
3:  ላይብረሪ 1ለ 4000ተማሪ
እሱም ዝናብ ሲዘንብ ግራውዱ ውሀ ይሞላል
4:ሁለት መማሪያ ብሎክ 4000ተማሪ
አንዱ ብሎክ 40room አለው ሁሉም ሲያዝ ግማሹ አይማርም
5:    wi-fi አገልግሎት የለም ተማሪ እደገና ወደ 1980 ያለ ዩንቨርሲቲ ነው በዚ 2021 century
6:  የኮፒ ችግር one paper copy 5birr
6: የመታጠቢያ ውሀ ከጉድጓድ  የረጋ ውሀ ነው (ውሀው ምንም አይታከምም)
የውሀ ወለድ በሽታዎች ከመብዛቱ የተነሳ ተማሪ ለበሽታ ተጋለጡዋል
8:  ዘረፋ የጊቢው መገለጫ ነው
9:  አንድ ዲፓርትመን ከበዛ 1ዐ ተማሪ ካነሰ 3 ተማሪ የሚማርት ጊቢ ነው
በብዛት ሁሉም ዲፖርትመንት 7 ተማሪ ነው ያለው 
🙏እባካቹ
🎓የዉሀ ችግር
🎓የwifi አገልግሎት
🎓የላይብረሪ
🎓ዘረፍ
🎓የኮፒ
እዲፈቱልን ድምፅ ሁኑን
እናመሰግናለን

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
ሰላምታዬ ይድረሳችሁ

እኔ የጅግጅጋ ዩንቨርስቲ ተማሪ ነኝ ስሜ ለጊዜው ይቆይ ጅግጅጋ ዩንቨርስቲ ለተማሪ በጣም አስቸጋሪ ሆኗል ብሎክ33 መብራት ከጠፋ፣ከተበላሸ አንድ ወር አልፎታል ፣ሌሎችም አንዳድ ብሎኮች መብራት ከጠፋ አንድ ወር አለፋቸው የሚመለከታቸውን አካል ስንጠይቅ ጠብቁ ነው የሚሉት መፍትሄ ግን የለም በጨለማ ውስጥ እያደርን👉pc፡ስልክ ቻርጅ ፣ማግኘት አልቻልንም ስልካችንም class room እየፈለግን ነው ቻርጅ የምናደርገው እና እንዴት ነው ለexit exam ልንዘጋጅ የምንችለው፣ ግቢው ውስጥ ስልክ wi-fi መጠቀም አይቻልም ምንም የለም ይህን ሁሉ ነው ተገድበን እየኖርን ያለንው አጠቃላይ ግቢው መረጃ እንዲወጣበት አይፈልግም መረጃ የሚያወጣበትን ተማሪ አፈላልጎ ያባርራል please ድምፃችንን አሰሙልን🙏🙏🙏


ጥቆማና አስተያየት ካለዎት
@SNC1BOT ላይ ማድረስ ይችላሉ።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
#MoE

"በአገር አቀፍ ደረጃ ያሉ 49 ሺ ትምህርት ቤቶችን የማሻሻል ዘመቻ ከአንድ ወር በኋላ ይጀመራል" - የትምህርት ሚኒስቴር፡፡

የትምህርት ምዘና ጥናት ውጤቶችን ለማስተዋወቅ የተዘጋጀ አውደ ጥናት በመካሄድ ላይ ነው፡፡ በመድረኩ የቅድመ አንደኛ ደረጃ የትምህርት ጥራት ውጤት ምዘና እንዲሁም የ4ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የትምህርት ምዘና ጥናት ይፋ ሆኗል።

በናሙና በተወሰዱ ትምህርት ቤቶች በተደረገው ምዘና ዝቅተኛ ውጤት መገኘቱን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡

የትምህርት ሥርዓቱን አሁን ባለበት ሁኔታ ይዞ መቀጠል አይቻልም ያሉት ሚኒስትሩ፤ በአገር አቀፍ ደረጃ ባሉት 49 ሺ ትምህርት ቤቶች የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

በመሆኑም ትምህርት ቤቶችን የማሻሻል ዘመቻ ከአንድ ወር በኋላ እንደሚጀመር ይፋ አድርገዋል፡፡ በዘመቻው ተማሪዎች፣ መምህራን፣ የቀድሞ ተማሪዎች እና ማህበረሰቡ ተሳታፊ እንደሚሆኑ አመልክተዋል፡፡

ርዕሰ መምህራንን ለማብቃት የሚያስችል ማዕከል እየተቋቋመ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡ #EPA #MoE



የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#WolloUniversity
New #Updated Academic Calendar

ወሎ ዩኒቨርሲቲ በሪሚዲያል፣ በ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና እና በመውጫ ፈተና ምክንያት የ2015 ዓ.ም አካዳሚክ ካሌንደርን ማሻሻያ አድርጓል።

በተሻሻለው አዲስ ካሌንደር መሰረት 👇

፨ከሰኔ 10-15/2015 ድረስ የሪሚዲያል ፈተና ይሰጣል።(Tentative)

፨ሰኔ 29 እና 30 የዩንቨርሲቲው መደበኛ ተማሪዎች ለኢንትራንስ ፈተና ሲባል ግቢው ለቀው እንዲወጡ ይደረጋል።

፨ከሀምሌ 05-14/2015 ድረስ የዩንቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ይሰጣል።(Tentative)

፨ሀምሌ 15 እና 16/2015 የግቢው ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ለመውሰድ ወደ ግቢ ይገባሉ።

፨ከሀምሌ 17-27/2015 ድረስ የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ይሰጣል።

📌 በዚህ አካዳሚክ ካሌንደር መሰረት የወሎ ዩኒቨርስቲ የተመራቂ ተማሪዎች የመመረቂያ ቀን 👉መስከረም 19-20/2016 እንደሆነ ተገልጿል።


⭕️ዝርዝር መረጃ ለምትፈልጉ ከላይ የተያያዘውን ምስል ይመልከቱ።


የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#MoE

" የትምህርት ሥርአቱን አሁን ባለበት ሁኔታ ይዞ መቀጠል አይቻልም " - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘና ውጤትና የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ጥራትና ውጤት የጥናት ውጤት ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

በዚሁ መድረክ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ " በትምህርት ዘርፉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በርካታ የለውጥ ስራዎች እየተሠሩ ነው ፤ በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ፈጥኖ ማረም ይገባል " ብለዋል።

" የትምህርት ሥርአቱን አሁን ባለበት ሁኔታ ይዞ መቀጠል አይቻልም " ያሉት ሚኒስትሩ " በሚታዩት ውጤቶች ሳንደናገጥ ዘርፉን ለመለወጥ ጠንክሮ መሥራት ይገባል " ሲሉ ተናግረዋል።

👉 የተማሪዎች የትምህርት ፍላጎት ማነስ ፣
👉 ተስፋ መቁረጥ፣
👉 የመምህራን እጥረትና ተነሳሽነት አለመኖር፣
👉 የትምህርት ቤቶች መሠረተልማት መጓደልና ለመማር ማስተማር ምቹ ያለመሆን
👉 የትምህርት ቤቶች አመራር መጓደል #ለውጤቱ_መውደቅ ምክኒያቶች መሆናቸው በጥናቱ ተመላክቷል።

የትምህርት ጥራቱን ለማረጋገጥም የትምህርት ዘርፍ ችግሮችን ፈጥኖ  ማረም እንደሚገባም ተገልጿል።

የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል በቀጣይ ወር የሚጀመር ሀገራዊ  ንቅናቄ እንደሚኖር እና ማህበረሰቡን በማስተባበር ትምህርት ቤቶችን የማሻሻል ሥራ እንደሚሰራ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል።

በዚህ ሂደት ወላጆች የትምህርት ቤቶች ባለቤቶች መሆናቸውን እያረጋገጡ መሄድ እንደሚገባቸውና  ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

በመድረኩ ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘና ውጤት(NLA)  እና የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ጥራትና ውጤት በባለሙያዎች ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ይገኛል።

ምንጭ፦ የትምህርት ሚኒስቴር


@NATIONALEXAMSRESULT
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መቼ ይሰጣል?

በርካታ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ከፈተና ቀን ጋር በተያያዘ ተመሳሳይ ጥያቄዎችን እየላኩልን ይገኛሉ።

ፈተናው በመጪው ሐምሌ ይሰጣል ተብሎ የነበረ ቢሆንም፤ እስከአሁን የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ትክክለኛና ቁርጥ ያለ ቀን ይፋ አልተደረገም።

የፈተናው ቀን ይፋ የሚደረገው በማዕከል በኩል ከትምህርት ሚኒስቴር / ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ሲሆን ይህም ለህዝብ በይፋ በመገናኛ ብዙኃን ይነገራል።

በመሆኑም የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ተማሪዎች ለፈተናው ጥቂት ጊዜ የቀረው መሆኑን በመገንዘብ ዝግጅት ማድረጋችሁን እንድትቀጥሉ እንላለልን።

በሌላ በኩል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና የተፈታኞች የበይነ መረብ ምዝገባ /online Registration/ አፈጻጸም ግምግማ ባለፈው ሳምንት አካሂዷል፡፡

በተጨማሪም በተዘጋጀው የፈተና አስተዳደር መመሪያ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን የበይነ መረብ ምዝገባው ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ የተደረገበትና ስኬትማ መሆኑ ተገልጿል።

በመድረኩ የፈተና አስተዳደር መመሪያ ለተሳታፊዎች ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ ከውይይቱ የተገኙ ሀሳቦችም በሰነዱ ተካተው በድጋሚ ለውይይት እንደሚቀርብና ሲጸድቅ ተግባራዊ እንደሚሆን ተነግሯል።

የመውጫ ፈተና

ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና በተመሳሳይ በማዕከል ተዘጋጅቶ በኦንላይን የሚሰጥ መሆኑ ይታወቃል።

ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጠው አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ከዚህ ቀደም በመጪው ሐምሌ ይሰጣል ተብሎ በመንግሥት ኃላፊዎች መገለጹ ይታወሳል።
ይህም ፈተና የሚሰጥበትን ቀን በተመለከተ ትምህርት ሚኒስቴር ዝርዝር መረጃ የሚያወጣ በመሆኑ፤ እስከዛው ዝግጅታችሁን አጠናክሩ።
@NATIONALEXAMSRESULT
የድሬደዋ ዩንቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት ከትምህርት ሚኒስቴር የተሠጡ አቅጣጫዎች በሚል ያጋራው መረጃ 👇

1, የሬሜድያል ተማሪዎች ፈተና 👉ሰኔ መጨረሻውዎቹ የሚሠጥ ይሆናል።

2, የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና 👉ሀምሌ የመጀመሪያዎቹ ሁለት ሳምንት ውስጥ የሚሠጥ ይሆናል።

3, በ2ተኛ ወሰነ ትምህርት ያልተመዘገቡ እና ለምርቃት ብቁ ያልሆኑ የመጨረሻ ዓመት ተማሪዎች ቀጣይ አመት ፈተናው የሚወስዱ ይሆናል።(የዓመቱ መጀመሪያ ላይ)

4, የምርቃት ፕሮግራም በተመለከተ በተቋማት የሴኔት ውሳኔ ማድረግ የሚቻል ይሆናል።

5,  የፈተናው አጠቃላይ የጥያቄ መጠን እንደ ትምህርት አይነቱ  ከ 100-150 ነው።

6, ማለፊያ ነጥብ 50% እና ከዚያ በላይ ነው።

7, ፈተናው የሚሠጠው በ online  ነው።

8,  የፈተናው ይዘት ሙሉ ምርጫ ነው።


የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ማጣራት እንዲደረግባቸው በተለያዩ ተቋማት ከቀረቡለት የትምህርት ማስረጃዎች ውስጥ እስካሁን 21 ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎች ማግኘቱን አሳውቋል።

ዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ ተቋማት የግለሰቦች የትምህርት ማስረጃ ተገቢነት ተጣርቶ እና ተረጋግጦ እንዲገለጽ በቀረበለት ጥያቄ መሰረት በ42 የትምህርት ማስረጃዎች ላይ በሁለት ዙር ባካሄደው የህጋዊነት ማረጋገጫ ሥራ 21ዱ ሐሰተኛ ሆነው መገኘታቸውን የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር አሳውቋል።

ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃው በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ስም ተጭበርብሮ በተሰራ ማሕተም፣ በአመራር የስምና የማዕረግ ቲተር እንዲሁም በሐሰተኛ ፊርማ ተመሳስሎ የተሠራ መሆኑ ተመላክቷል።

ግለሰቦቹ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ በመጠቀም በተለያዩ ትምህርት ቤቶች በመምህርነት ተቀጥረው በመስራት የማይገባቸውን ጥቅም እያገኙ መሆኑም ተገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው የሐሰተኛ ትምህርት አጣሪ ግብረ ኃይል አቋቁሞ ሰፊ የማጣራት ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጿል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#AAU

ዩኒቨርሲቲው በመውጫ ፈተና የጊዜ ሰሌዳ ምክንያት የ2015 የምረቃ በዓሉን ቀየረ።

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ2015 ተመራቂ ተማሪዎቹን ሐምሌ 08/2015 ለማስመረቅ በማቀድ የሚሊኒየም አዳራሽን ትብብር ጠይቆ ፈቃድ አግኝቶ የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ የመውጫ ፈተና መስጫን አስመልክቶ በትምህርት ሚኒስቴር በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የምረቃ በዓሉን በአንድ ሳምንት ቀደም ብሎ ማለትም ሐምሌ 01/2015 ለማከናወን የሚሊኒየም አዳራሽን የተለመደ ትብብር ጠይቋል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
ዛሬ ከትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና ለክልል ትምህርት ቢሮዎች ከተላከ ደብዳቤ ያገኘነው መረጃ👇

1) በ2014 የ12ኛ ክፍል አጠናቀው ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ የሬሜዲያል ኘሮግራም ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎች ለአንድ ሴሚስተር የተሰጠው ትምህርት በማዕከል የጋራ ፈተና ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ፤ ተቋማት ፈተናውን የማስተዳደር ውጤት የመግለፅና በ2016 ፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ ሆነው የተገኙት (ማለትም በተቋማት የውስጥ ፈተና 50 ከመቶ፣ በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና 50 ከመቶ) ተደምሮ በድምሩ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡቱን እንዲያሳወቁ፣ ይህ አጠቃላይ ሂደት እስከ 👉ሰኔ 30 ቀን ድረስ እንዲጠናቀቅ።


2) በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃንና ባለፉት ዓመታት የህግ መውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡት ተማሪዎች የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የመፈተኛ ማዕከላት ውስጥ ፈተናው 👉ከሐምሌ 3 እስከ 13 ባሉት ቀናት ተሰጥቶ እንዲጠናቀቅ።


3) የ2015 የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና 👉ከሐምሌ 19 እስከ 30 የሚሰጥ ሆኖ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከሐምሌ 15 ቀን ጀምሮ ለዚሁ ሥራ ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ።


የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
፨ለሁሉም የመንግስት ዩንቨርስቲዎች
፨ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
፨ለሁሉም የክልል ትምህርት ቢሮዎች

ጉዳዩ፡ የአገር አቀፍ ፈተና ቀናትን ስለማሳወቅ

1) በ2014 የ12ኛ ክፍል አጠናቀው ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ የሬሜዲያል ኘሮግራም ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎች ለአንድ ሴሚስተር የተሰጠው ትምህርት በማዕከል የጋራ ፈተና ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ፤ ተቋማት ፈተናውን የማስተዳደር ውጤት የመግለፅና በ2016 ፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ ሆነው የተገኙት (ማለትም በተቋማት የውስጥ ፈተና 50 ከመቶ፣ በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና 50 ከመቶ) ተደምሮ በድምሩ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡቱን እንዲያሳወቁ፣ ይህ አጠቃላይ ሂደት እስከ 👉ሰኔ 30 ቀን ድረስ እንዲጠናቀቅ።


2) በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃንና ባለፉት ዓመታት የህግ መውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡት ተማሪዎች የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የመፈተኛ ማዕከላት ውስጥ ፈተናው 👉ከሐምሌ 3 እስከ 13 ባሉት ቀናት ተሰጥቶ እንዲጠናቀቅ።


3) የ2015 የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና 👉ከሐምሌ 19 እስከ 30 የሚሰጥ ሆኖ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከሐምሌ 15 ቀን ጀምሮ ለዚሁ ሥራ ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ።

በመጨረሻም ከ2016 ጀምሮ የትምህርት ካላንደሩን ሁሉም ተቋማት ፕሮግራሞቻቸውን በዚህ ማዕቀፍ ያስተካክሉ ዘንድ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አሳስበዋል።


የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot