STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
40.7K subscribers
11K photos
272 videos
452 files
1.94K links
የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡
Download Telegram
#AddisAbabaEducationBureau
#MinistryOfEducation

"ተማሪዎች ዘንድሮ በያላችሁበት ክፍል ትደግማላቸሁ" በሚል የሚናፈሰው ወሬ ከእውነት የራቀ መሆኑን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

ተማሪዎች የ2014 የትምህርት ዘመን የማጠቃለያ ፈተና ለመውሰድ እየተዘጋጁ መሆኑን የገለጸው ቢሮው፤ ኃላፊነት የጎደላቸው አካላት ሆን ብለው ተማሪዎችን ለማዘናጋት ዘንድሮ ከክፍል ወደ ክፍል መዘዋወር የለም የሚል ሀሰት መረጃ እያሰራጩ መሆኑን ገልጿል።

መረጃው ፍጹም ከእውነት የራቀ እንዲሁም ከዚህ ጋር የተያያዘ ከትምህርት ሚኒስቴር የወረደ አቅጣጫ የሌለ መሆኑን ቢሮው አረጋግጧል።

በተመሳሳይ "ሁሉም የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ባሉበት የትምህርት ደረጃ እንዲቀጥሉ ተወስኗል" በሚል የሚዘዋወረው መረጃ የተሳሳተ እና ከእውነት የራቀ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

የተቋሙን ስም እና አርማ በመጠቀም የተሳሳቱ እና የተዛቡ መረጃዎችን በመልቀቅ ውዥንብር እየፈጠሩ ያሉ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ማየቱን ሚኒስቴሩ ጠቁሟል።

በመሆኑም ተማሪዎች የሚሰራጩት መረጃዎች የተሳሳቱ እና ከእውነት የራቁ መሆናቸውን አውቀው ትኩረታቸውን ትምህርታቸው ላይ ብቻ እንዲያደርጉ ሚኒስቴሩ ጠይቋል።

ተማሪ ነክ መረጃዎችን እንዘግባለን
@NATIONALEXAMSRESULT
#AddisAbabaEducationBureau

የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በሰርተፍኬት ሲያስተምሩ የነበሩ 4 ሺህ የቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራንን በዲፕሎማ ሊያሠለጥን መሆኑን አስታውቋል፡፡

የቅድመ አንደኛ ደረጃ (ሙዓለ ህፃናት) መምህራኑ ከሐምሌ 01/2014 ዓ.ም ጀምሮ ለቀጣይ ሦሥት ዓመታት በዲፕሎማ እንደሚሠለጥኑ ተገልጿል፡፡

ከግልና ከመንግሥት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ 2 ሺህ 500 መምህራንን በደብረ ብርሃን መምህራን ኮሌጅ እንዲሁም 1 ሺህ 500 መምህራን በአሰላ መምህራን ኮሌጅ የሚማሩ ይሆናል፡፡

ቢሮው ከደብረ ብርሃን መምህራን ኮሌጅ እና ከአሰላ መምህራን ኮሌጅ ጋር ለቀጣይ ሦሥት ዓመታት አብሮ ለመስራት ሰኔ 20/2014 ዓ.ም ስምምነት አድርጓል።

ለስልጠናው ከተመዘገቡ ከ5 ሺህ 600 በላይ መምህራን ኮሌጆቹ ያስቀመጡትን የመግቢያ ነጥብ ያሟሉት 4 ሺህ ብቻ በመሆናቸው ትምህርት ቢሮው ሁሉንም መምህራን ወደ ኮሌጆቹ ለማስገባት መወሰኑ ታውቋል፡፡

ትምህርቱ በክረምት እና በቅዳሜና እሁድ ለሦሦት ዓመታት የሚሰጥ ሲሆን ለዚህም ቢሮው ከ80 እስከ 90 ሚሊዮን ብር መመደቡ ተገልጿል። #ሪፖርተር

ተማሪ ነክ መረጃ እንዘግባለን
@NATIONALEXAMSRESULT
#AddisAbabaEducationBureau

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሞዴል ፈተና ለ6ኛ፣ 8ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች እየሰጠ ነው።

ሞዴል ፈተናው ዛሬ መጋቢት 29/2015 ዓ.ም ይጠናቀቃል፡፡

በከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ የተዘጋጀው ሞዴል ፈተናው፤ ተማሪዎች ራሳቸውን ለዋናው ፈተና ዝግጁ እንዲያደርጉ ያስችላል ተብሏል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot