መዝገበ ቅዱሳን
22.8K subscribers
1.93K photos
9 videos
6 files
27 links
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው! መ/ሳ 1÷7
Bewust mesimer lemanegager
@Yesadkusitota
የሰማነውን እንናገራለን
ያየነውን እንመሰክራለን
Download Telegram
ሁሉ በእጅጉ ሲገረምና ‹‹በአምላከ ታዴዎስ ስም አምናለሁ›› ሲል የባለጸጋው ልጅ ሙሳ ግን ‹‹በምትሃት አሳይቶን ነው እንጂ የእውነት አይደለም›› በማለት አባቱንም እንዳያምን ይናገር ጀመር፡፡ ይህንንም ሲናገር በመጀመሪያ ያለፈችው እናቲቱ ግመል እረግጣ ገደለችው፡፡

አቡነ ታዴዎስም ንጉሡን፣ አባቱን አፍጃልንና ሕዝቡን የሞተ እንደሚነሣ ሲያስምሯቸው ‹‹የሞተ ይነሣልን? እስኪ ይህ የሞተው ልጅ ይነሳና ሁሉም አይቶ ይመን›› አሏቸው፡፡ እሳቸውም ‹‹ዛሬ ተቀብሮ ይዋልና ነገ በሦስተኛው ይነሣል›› ብለዋቸው ተቀብሮ ዋለ፡፡ በማግሥቱም አፍጃልን ጠርተው ‹‹‹አልዓዛርን ከሞት ባስነሣው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ልጄ ሆይ ና ውጣ› ብለህ ከልጅህ መቃብር ላይ አኑረው› ብለው ዘንጋቸውን ሰጡት፡፡ ሄዶም እንዳሉት ቢያደርግ ልጁ አፈፍ ብሎ ተነሥቷል፡፡ ይህንን ያዩ የሀገሩ ሰዎች ሁሉም አምነው ተጠምቀዋል፡፡ እሳቸውም 12 አብያተ ክርስቲያናትን አሳንጸው ሞቶ የተነሳውን ሙሳን ሙሴ ብለው ሰይመው አስተምረው ሊቀ ካህናት አድርገው ሾመውት አቡነ አኖሬዮስን ይዘው ወደ ጽላልሽ ዞረሬ ተመልሰዋል፡፡

አቡነ ተክለ ሃይማኖት ካረፉ በኋላ አባ ያዕቆብ የተባሉ ጳጳስ ከግብፅ መጡ፡፡ የአቡነ ታዴዎስን ዜና ሲሰሙ ተደስተው ከአቡነ ፊሊጶስ ጋር ሆነው አስጠርተዋቸው ‹‹የአባታችሁን ዜና ገድል ንገሩኝ›› አላቸው፡፡ አቡነ ታዴዎስም ‹‹ጨዋታ በአስተርጓሚ አይሰምርም›› ብለው ወደ ጌታችን ቢጸልዩ የጳጳሱ ቋንቋ ለታዴዎስ፣ የታዴዎስም ቋንቋ ለጳጳሱ ተገልጦላቸው የመሸ የነጋ ሳይመስላቸው 40 ጾምን ሲጨዋወቱ ቆይተዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ጳጳሱ ከንጉሡ ተማክረው ‹‹ሊቀ ካህናት ዘጽላልሽ›› ብለው ሾመዋቸዋል፡፡

በነግህና በሰርክ ቤተ ክርስቲያንን እያገለገሉ፣ ቀን ወንጌልን እየሰበኩ፣ ሌሊት ከባሕር ገብተው ሲጸልዩ እያደሩ በታላቅ ተጋድሎ እየኖሩ ሳለ ከ10 ዓመት በኋላ ሰይጣን በንጉሡ በዓምደ ጽዮን ፍቅረ ዝሙት አሳድሮበት በክፉዎችም ምክር አታሎት የአባቱን ቅምጥ አገባ፡፡ አቡነ ታዴዎስም ይህን ሲሰሙ እንደ ነቢዩ ኤልያስና እንደ መጥምቁ ዮሐንስ በቀጥታ ሄደው ንጉሡን ገሥጸው አወገዙት፡፡ ገሥጸውና አውግዘው አቡነ ማትያስን አስከትለው ሲመለሱ ቅምጧ የንጉሡ ሚስት በፈረስ ተከትላ ደርሳ የኋሊት አሳስራ ዛሬ ‹‹ማርያም ገዳም›› ከሚባለው ቦታ ፊት ለፊት ካለው ትልቅ ገደል ውስጥ ሁለቱንም ጣለቻቸውና ጥር 29 ቀን በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡

በሰማዕትነት ዐርፈው ደማቸው ከፈሰሰበት ከገደሉ ስር በፈለቀው ጸበላቸው ‹‹ታዴዎስ ወማትያስ›› እያለ ሦስት ጊዜ ብቅ ጥልቅ እያለ የተጠመቀ ሰው እንደ 40 ቀን ሕፃን እንደሚሆን ጌታችን ቃልኪዳን ገብቶላቷቸዋል፡፡ ይህ ሰማዕትነት በተቀበሉበት አካባቢ የተሠራው ቤተ ክርስቲያናቸው በጠላት ወረራ ጊዜ ፈርሶ ቦታው ጠፍ ሆኖ የኖረ ቢሆንም የአካባቢው ሕዝብ ቦታውን ከልሎ በክብር ሲጠብቀው ስለኖረ ፈቃደ እግዚአብሔር ሆኖ የአቡነ ታዴዎስ ታቦታቸው በ2005 ዓ.ም ከኢቲሣ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ወጥቶ ጻድቁ ሰማዕትነት በተቀበሉበት አካባቢ በተሠራው መቃኞ ቤተ ክርስቲያናቸው በታላቅ ክብር ገብቷል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑም ከኢቲሣ በእግር የአንድ ሰዓት ተኩል ርቀት ላይ ይገኛል፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ጻድቃን_ቅዱሳን_ማሕበረ_ዶጌ (ዴጌ ጻድቃን)

በዚህች እለት የጻድቃን ቅዱሳን ማኅበረ ዶጌ አክሱም አካባቢ በቁጥር ወደ 3000 የሚሆኑ ከመድኃኔዓለም ጋር ማኅበር ይጠጡ የነበሩ በአንድ ላይ የተሰወሩ ቅዱሳን መታሰቢቸው ነው፡፡ እነዚህም ጌታችን መድኃኔዓለም ክርስቶስ በመካከላቸው ተገኝቶ የጽዋ ማኅበራቸውን አብሯቸው የጠጣ ሦስት ሺህ ቅዱሳን ‹‹ማኅበረ ጻድቃን ወይም ማኅበረ ደጌ›› እየተባሉ ይጠራሉ፡፡ ማኅበሩን ያቋቋመው ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ነው፡፡ በኋላም ከመድኃኔዓለም ክርስቶስ ጋር አብረው ማኅበር የጠጡ እነዚህ ሦስት ሺህ ቅዱሳን አክሱም አካባቢ ባለው በአቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ገዳም ጥር 29 ቀን በዓመታዊ መታሰቢያ በዓላቸው ይከብራሉ፡፡ ማኅበረ ዴጌ ማለት የደጋጎች ሀገር ማለት ነው፡፡ የደጋጎች ሀገር የተባለበት ምክንያት ብዙ ሺህ ቅዱሳን ተሰብስበው ስለሚኖሩበት ነው፡፡ ገዳሙ የሚገኘው በትግራይ ክልል በአክሱም አውራጃ ከአክሱም ከተማ ወደ ደቡብ ምዕራብ በሚወስደው መንገድ አስራ ሁለት ኪሎሜትር ያህል ርቀት ላይ ነው፡፡

በቦታው ላይ ጥንት መሥዋዕተ ኦሪት ይሠዋበት ነበር፡፡ በኋላም በ40 ዓ.ም ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ወደ አገራችን በመጣ ጊዜ በቦታው ላይ ወንጌልን ሰብኮ ብዙዎችን አጥምቋል፡፡ በወቅቱ የነበረችው ንግሥትም በቅዱስ ማቴዎስ እጅ ተጠምቃለች፡፡ ቅዱስ ማቴዎስም ንግስቲቱን ካጠመቀ በኋላ ቀጥሎ መኳንንቱን፣ መሳፍንቱንና የጦር ሠራዊቱን ሁሉ አጥምቋቸዋል፡፡ ከዚህም በኋላ የጻድቃንን ማህበር አቋቁሞ በጌታችን ስም በየወሩ በ29 ቀን እየተሰበሰቡ ጽዋ እንዲጠጡ አድርጓቸው ወደ ኢየሩሳሌም ሄዷል፡፡

በ365 ዓ.ም በአስፍሕ ወልደ አብርሃም ንጉሰ ነገስት ዘኢትዮጵያ ዘመነ መንግስት ‹‹ሮምያ›› ከምትባል መንደር ቅዱሳን ‹‹ስለ ጽድቅ ብለው የሚሰደዱ ብፁአን ናቸው መንግስተ ሰማያት የነርሱ ናትና›› ያለውን ዳግመኛም ‹‹አባቱንና እናቱን ሚስቱንና ልጆቹን ያልተወ ሊያገለግለኝ አይችልም›› ብሎ ጌታችን የተናገረውን አስበው ቅዱሳን የዚህም ዓለም ጣዕም ጥቅም ንቀው ሀገራቸውን ትተው መንነው ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ነበሩ፡፡ እነዚህም ቅዱሳን በአክሱም ከተማ በስተሰሜን በሐውልቱ ጀርባ ቤተ ቀጠንት በሚባል ስፍራ አንድ ዓመት ከስድስት ወር ያህል እንደ ተቀመጡ በዚያም ምቾትና ድሎት ስለተሰማባቸው ‹‹ለዚሁ ለዚሁማ ሀገራችንን ለምን ትተን መጣን? ስለዚህ ሱባዔ ገብተን በጾም በጸሎት ተወስነን የምንሄድበትን ቦታ በረከተ ነፍስ የምናገኝበትን ስፍራ እግዚአብሔር እንዲያሳየን እናመልክት›› ብለው ሱባዔ ገቡ ጾም ያዙ፡፡

ከሱባዔውም በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተገልጻላቸው ግማሾቹን እያንዳንዳቸው የሚኖሩበትን በዓት አመልክታቸው፣ በዚያም በጾምና በጸሎት ጸንተው እንዲኖሩ ነገረቻቸው፡፡ ሦስት ሺህ ያህሉን ደግሞ ከላይ ወደጠቀስነው ሥፍ ሄዱ፡፡ ከእነርሱ የተቀሩት ደግሞ ወደ ቆየፃ ሓባር፣ ተድባ፣ አኮርየን፣ ተንስሓ፣ ደብረ አንሳ ወደ ተባሉ ቦታዎች ሄደዋል፡፡ ተጨማሪ ሥስት ሺህ የሚሆኑት ደግሞ እዚያ ከነበሩት ጋር ተደመሩ፡፡ ከዚህም በኋላ እነዚህ ቅዱሳን ‹‹ከሁሉ ፍቅር ይበልጣል›› የሚለውን ጠብቀው በእምነት በፍቅር በአንድነት ጸንተው በየሳምንቱ እሁድ እሁድ ተዝካረ ሰንበትን ጠብቀው ማኅበር ይጠጡ ጀመር፡፡ በዚህም ጊዜ የማኅበረ ዴጌ ታሪክ ተቀየረ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአምሳለ ነዳይ ድሀ መስሎ በመካከላቸው ተገኘ፡፡ ግን ማንም አላወቀውም ነበር፡፡ ጌታችንም ከእነርሱ ጋር አንድ ማኅበርተኛ ሁኖ እንዲታወቅ ጠየቃችው፣ እነርሱም ፈቀዱለትና አንዱ የማኅበሩ አባል ሆነ፡፡ አንድ ዓመት ከስድስት ወር ያህልም ከእነርሱ ጋር ሳይለይ ቆየ፡፡ በዚሁ ጊዜ ‹‹እስቲ ለእኔም ተራ ስጡኝ እንደአቅሜ ዝክር ላውጣ›› አላቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ግን ድህነቱን አይተው ‹‹አይሆንም አንተ ድሀ ነህ፣ ከኛ ጋር ሁነህ በዓሉን አክብር እንጂ ምን አለህና ነው የምትደግሰው? ይቅርብህ›› አሉት፡፡ እርሱም ‹‹አይሆንም ስጡኝ እንጂ›› ብሎ ግድ አላቸው፡፡ እነርሱም ካልክማ ብለው ቀን ወስነው ሰጡት፡፡ ቀኑም ጥር 29 ነበር፡፡